29/05/2026
የሲዳማ ከልል ገንዘብ ቢሮ የፕሮግራም በጀት አዘገጃጀት እና አስተዳደር ሥርዓት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬ - ሀዋሳ
የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ገንዘብ ቢሮ ከክልሉ ፕላን ቢሮ ጋር በመቀናጀት ለክልል ማዕከል ለባለበጀት መስሪያ ቤቶች እና ተጠሪ ተቋማት በዕቅድ፣ በጀት ዝግ/ዳይሬክቶሬቶችና ለበጀት ቡድን መሪዎች የፕሮግራም በጀት አዘገጃጀትእና አስተዳደር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ።
በስልጠና መድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የሲዳማ ክልል ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሌ ሀርሲሳ ዕቅድ ማለት አንድን ግብ ወይም ራዕይ ለማሳካት አስቀድሞ የሚዘጋጅ ዝርዝር የድርጊት መርሃ ግብር ሲሆን፤ ተግባሮችን በዘመናዊ መንገድ ለመስራት፣ ጊዜን በአግባቡ ለመጠቀም፣ ውሳኔዎችን ለማሳለጥ እና ስኬትን ለመለካት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሰነድ ወይም አቅጣጫ ነው ሲሉ ገልፀዋል።
አክለውም የፕሮግራም በጀት ዋና ዓላማው ያለንን ውስን ሀብት ውጤት በሚያመጡ ጉዳዮች ላይ ማዋልን እና ዕቅድን ከበጀት ጋር ማስተሳሰር መሆኑን ገልፀዋል።
የስልጠና መድረኩ ዋና ዓላማ የፕሮግራም በጀት ውጤታማ ለማድረግ የልማት ዕቅድ ባለሙያዎች እና አስተባባሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎችን በመስጠት የመፈጸም አቅማቸውን ለማጎልበት ታስቦ መሆኑን የቢሮው ኃላፊ አስገንዝበዋል።
በስልጠና መድረኩ ላይ የፕሮግራም በጀት የሚያመላክት የመወያያ ሠነድ የቀረበ ሲሆን፤ በቀረበው ስነድ ላይ የፕሮግራም በጀት ዝግጅት እና አስተዳደር፣ የፕሮግራም በጀት አሰራር፣ የበጀት ምንነት፣ የበጀት አይነቶች፣ የገቢ እና ወጪ በጀት አይነቶች፣ የበጀት ሚና፣ የዕቅድ ዝግጅት እና አጠቃላይ የፕሮግራም በጀት ፅንሰሃሳብን በሚመለከት በዝርዝር ቀርበው ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጓል።
የሰልጠና ተሳታፊዎች ከስልጠናው ጠቃሚ ሀሳቦች ማግኘታቸውን ጠቅሰው የተሰጣቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ተግተው እንደሚሠሩ ከሰጡት አስተያዬት ለመረዳት ተችሏል ።
በመጨረሻም ከቀረበው ሰነድ በመነሳት ከመድረኩ ተሳታፊዎች በኩል ጥያቄዎችና አስተያየቶች ቀርበው በቢሮው ኃላፊ አቶ ኃይሌ ሀርሲሳ እና የሲዳማ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ በዶ/ር ዮሐንስ ዮና መልስና ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቶበት፤ ለቀጣይ ከክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ጋር በቅንጅት ለመስራት የጋራ መግባባት ላይ ተደርሶ ስልጠና መድረኩ ተጠናቋል፡፡
ግንቦት 19/2018 ዓ.ም
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት:-
ፌስ ቡክ፦ https://www.facebook.com/profile.php?id=100067066834036
Telegram: https://t.me/+ou6fpnGJwUEwNmM0
Whats App:https://chat.whatsapp.com/BwVha2qdJYkK1WhdgCjffr?mode=wwt
Tik tok: 335?
Emial: Fananice bureaus @ gmail.com
You tube: Sidama Region Fanance Bureau
Follow, Share, Like, በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።