ሐዋሳ ከተማ አስተዳደር የአዲስ ከተማ ክ/ከ/አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን

  • Home
  • Ethiopia
  • Awassa
  • ሐዋሳ ከተማ አስተዳደር የአዲስ ከተማ ክ/ከ/አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን

ሐዋሳ ከተማ አስተዳደር የአዲስ ከተማ ክ/ከ/አስተዳደር  መንግስት ኮሙኒኬሽን Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ሐዋሳ ከተማ አስተዳደር የአዲስ ከተማ ክ/ከ/አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን, Government Organization, Awassa.

ሲዳማ ክልል የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊና ተአማኒ እንዲሆን በጋራ ለመስራት ቃል ገቡ በሲዳማ ክልል ውስጥ የሚገኙ 23 ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ምክር ቤት...
27/05/2026

ሲዳማ ክልል የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊና ተአማኒ እንዲሆን በጋራ ለመስራት ቃል ገቡ


በሲዳማ ክልል ውስጥ የሚገኙ 23 ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ምክር ቤት የተዘጋጀ ውይይት በማካሄድ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ተአማኒ፣ ነጻ እና ቅቡልነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ በትብብር ለመስራት ቃል ገብተዋል።

የውይይት መድረኩ በክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ደስታ ሌዳሞ፣ በክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋንታዬ ከበደ እና በተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ በለጠ ሰጌቦ መሪነት ተካሂዷል። በመድረኩ የተለያዩ ፓርቲ ተወካዮች ተሳትፈው ሰፊ ውይይት አካሂደዋል።

በውይይቱ ዋና ትኩረት የፖለቲካ ተፎካካሪዎች መካከል መተማመንን ማጠናከር፣ የምርጫ ሂደትን ማሻሻል እና ከቀድሞ ምርጫዎች በተሻለ መልኩ ለማስፈጸም ሁሉም በትብብር መስራት እንደሚገባ ተገልጿል።

ተሳታፊዎቹ በምርጫ ወቅት ሊነሱ የሚችሉ ችግሮችን በቅድሚያ ለመለየት፣ የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከል እና ሰላማዊ የፖለቲካ ተወዳዳሪነትን ለማጠናከር በጋራ መሥራት እንዳለባቸው በአጽንኦት አንስተው ልዩነቶች በግጭት ሳይሆን በውይይት እንዲፈቱ አሳስበዋል።

በመድረኩ ውስጥ የምርጫ ሕጋዊ ሂደቶችን ማክበር፣ የምርጫ ደንቦችን በትክክል መፈጸም እና ሕዝቡ ፍላጎቱን በነጻነት እንዲገልጽ ማስቻል የሁሉም ኃላፊነት መሆኑን በመግለጽ የፖለቲካ ውድድር በኃይል ሳይሆን በሐሳብ መሆን እንደሚገባም በግልጽ ተነስቷል።

በምርጫ ሂደት ግልጽነት፣ ተጠያቂነት እና ሕጋዊ አሰራር እንዲጠናከር ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቶ የምርጫ መርሆዎች በጥብቅ እንዲከበሩ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

በመጨረሻም ተሳታፊ ፓርቲዎች 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለህዝብ ተአማኒ፣ ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን በቀጣይ በትብብር ለመስራት ቃል በመግባት ምርጫው ለሀገራዊ ሰላም ወሳኝ እንደሆነ አስረግጠዋል።

ዘገባው ፦ሲዳማ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ፣ግንቦት 19/2018

ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በሀዋሳ በ2 ቢሊዮን ብር በጀት ግንባታቸው የተጠናቀቁ 6 ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አደረጉየሀ/ከ/አስ/የመ/ኮሙ/መምሪያሀዋሳ፣ግንቦት 19/2018 ዓ...
27/05/2026

ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በሀዋሳ በ2 ቢሊዮን ብር በጀት ግንባታቸው የተጠናቀቁ 6 ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ

የሀ/ከ/አስ/የመ/ኮሙ/መምሪያ
ሀዋሳ፣
ግንቦት 19/2018 ዓ.ም

በምርቃቱ የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ክብርት ወ/ሮ ፋንታዬ ከበደ፣ የኢፌዴሪ ፕላንና ልማት ሚንስቴር ሚንስትር ክብርት ዶ/ር ፍፁም አሰፋ፣ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ እንዲሁም የክልሉና የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።

የፕሮጀክቶቹ በከተማዋ እያደገ የመጣው የማስፈፀም አቅምና አዲስ የተለወጠ የስራ ባህል ውጤት ስለመሆናቸውም ተጠቁሟል።

በምርቃቱ ወቅት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ እንደተናገሩት ሀገራችን ኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የታሪክ ባለቤት ብትሆንም እርስ በርስ የነበረባትን የውጭና የውስጥ መገፋፋት የሚፈለገውን ያለውን ያህል ለውጥ እና ፈጣን ዕድገትን ማምጣት የተቻበት አጋጣሚ አልነበረም ብለዋል።

ይህ ስብራት ግን አሁን ላይ ታሪክ ሆኖ ፈጣን እድገት እያስመዘገብን ሲሆን የዚህ ማሳያ ደግሞ የሀዋሳ ከተማ አንዷ ናት ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የከተማዋ ውበትና ሳቢነት በርካቶች ወደ ከተማዋ በመምጣት ኢንቨስት እስከማድረግ ፍላጎት እያሳዩ ይገኛሉ በማለት ተናግረዋል።

ዛሬ የተመረቁ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ደግሞ ይበልጥ የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡና የከተማዋን ከፍታ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሻግሩ ሆነው ይገኛል ብለዋል።

ከዚህ በተጓዳኝ በስፋት በከተማዋ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ስራና በአገልግሎት ረገድም የህዝብን እንግልት የሚቀንሱ እና እርካታ ያለው አገልግሎትን ተደራሽ ማድረግ የሚያስችሉ ስራዎች የሀዋሳን ተመራጭነት አሳድጎታል ሲሉ ገልፀዋል።

ለተገኘው ውጤት የከተማዋ አመራር ቁርጠኝነትና በተለወጠ የስራ ባህል 24/7 በትጋት በመስራት እውን ማድረግ በመቻላቸው ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ለዚህም ሊመሰገኑ እንደሚገባ ተናግረዋል።

የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ዛሬ የተመረቁት ፕሮጀክቶች የከተማዋን ውበት ማራኪ ከማድረግና የቱሪዝምና የኢንዱስትሪ ማዕከልነት ከማሳደግ ባሻገር የነዋሪውን የኑሮ ደረጃ ከፍ የሚያደርጉ ናቸው ብለዋል።

የፕሮጀክቶቹ መጠናቀቅ ሀዋሳን የስራ ትጋትና የፈጣን ዕድገት ተምሳሌት እያደረጋት ይገኛል ያሉት ከንቲባው ይህም በየቀኑ ለውጥ የሚስተዋልባት የኢትዮጵያ የብልጽግና ተምሳሌት ሆና እንድትታይ አቅም የፈጠረ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ዛሬ የተመረቁት 6 ግዙፍ ፕሮጀክቶችም በድምሩ ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸውና ሙሉ ለሙሉ ግንባታቸው ተጠናቆ ለህዝብ አገልግሎት ክፍት የሚሆኑ ናቸው ሲሉም ነው ከንቲባ ጥራቱ በየነ ያስረዱት።

ከፕሮጀክቶች መካከል በአገልግሎት አሰጣጥ ዘርፉ ትኩረት የተሰጠውና በ55 ቀናት ውስጥ ግንባታው የተጠናቀቀው የሀዋሳ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን ከዳር ለማድረስ አስተዳደሩ ለስራው 500 ሚሊዮን ብር ወጪ ስለማደረጉ ተናግረዋል።

ይህ ፕሮጀክት እንደ ከተማ በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ የሚስተዋሉ የህዝብ ጥያቄዎችን ከጊዜና ከወጪ ረገድ ያሉ ክፍተቶችን በማስቀረት ሁሉንም የመንግስትና የግል አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል ለህዝብ ተደራሽ እንዲሆኑ አቅም የሚፈጥር ነወሰ ብለዋል።

በተያያዘም በትምህርት ዘርፉ ያለ ስብራትን ለመጠገን እንደ ሀዋሳ ከተማ ባለሶስት ወለል ህንጻ በሐይቅ ዳር ትምህርት ቤት 180 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ ማጠናቀቅ ተችሏል።

በተመሳሳይም በጤናው ዘርፍ የከተማዋን የሕክምና ደረጃን የሚቀይርና 975 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገበት ዘመናዊው አዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል የሀዋሳ እና የአካባቢዉን

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የሚገኘው የሐይቅ ዳር አንደኛና መለስተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ማስፋፊያ ፕሮጀክት  ተመረቀ።
27/05/2026

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የሚገኘው የሐይቅ ዳር አንደኛና መለስተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ማስፋፊያ ፕሮጀክት ተመረቀ።

‎7ኛው ዙር ሀገራዊና ክልላዊ ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የድጋፍ ሰልፍ ላይ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች በዚህ መልክ ድጋፈቸውን አሳይተዋል።‎‎‎‎‎
26/05/2026

‎7ኛው ዙር ሀገራዊና ክልላዊ ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የድጋፍ ሰልፍ ላይ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች በዚህ መልክ ድጋፈቸውን አሳይተዋል።




የሀዋሳ ከተማን በመወከል ለብልፅግና ፓርቲ ዕጩ ሆነው የቀረቡ ተወዳዳሪዎች በተሽከርካሪ የታገዘ የምርጫ ቅስቀሳ በከተማው ዋና ዋና ጎዳናዎች ላይ አካሄዱ ።ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሀዋሳ ምርጫ ...
25/05/2026

የሀዋሳ ከተማን በመወከል ለብልፅግና ፓርቲ ዕጩ ሆነው የቀረቡ ተወዳዳሪዎች በተሽከርካሪ የታገዘ የምርጫ ቅስቀሳ በከተማው ዋና ዋና ጎዳናዎች ላይ አካሄዱ ።

ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሀዋሳ ምርጫ ክልል የሚወዳደሩ ዕጩዎችን ነው ዛሬ የሀዋሳ ብልፅግና ፓርቲ በከተማዋ ዋና ዋና ጎዳናዎች ላይ ለህዝብ የምረጡኝ ቅስቀሳ ያደረገው።

በምረጡኝ ቅስቀሳው የምርጫ ጣቢያውን በመወከል የፕላንና ልማት ሚንስትር ዶ/ር ፍፁም አስፋው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተወዳዳሪ ሆነው በተሽከርካሪ የታገዘ የምረጡኝ ቅስቀሳ አድርገዋል።

ለክልል ምክር ቤት በምርጫ ክልሉ ተወዳዳሪ እጩ ሆነው የቀረቡት አቶ ጥራቱ በየነ፣ አቶ ማራዶና ዘለቀ፣ ወ/ሮ ይመኙሻል ታደሰ፣ አቶ ደምሴ ዳንጊሶ፣ ዶክተር ፍትህ ወ/ሰንበት፣ ወ/ሮ ሲፊ ኑሪ፣ ወ/ሮ ካሰች ተፈራ፣ አቶ ወለሳ ሂንዲጋ እና አቶ ተስፋዬ ሾንዶላ የተካተቱበት ደማቅ የተሽከርካሪ ላይ የምረጡኝ ቅስቀሳና ትውውቅ በከተማዋ ጎዳናዎች ላይ ተካሂዷል።

እጩዎቹ ብልፅግናን የሚገልፁ መሪ ቃልና መፈክሮችን በማንገብ ቅስቀሳውን በማድረግ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ዘገባው ፦የሀ/ከ/አስ/የመ/ኮሙ/መምሪያ
ሀዋሳ፣
ግንቦት 17/2018 ዓ.ም

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አስተዳደር  በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ፅ/ቤት ለህብረተሰብ ልማትና ተሳትፎ ስልጠና ተሰጠ።
25/05/2026

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ፅ/ቤት ለህብረተሰብ ልማትና ተሳትፎ ስልጠና ተሰጠ።

በ2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 7ተኛ ዙር ሀገራዊ ምርጫን አስመልክቶ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን በመገምገም ለቀጣይ ተግባራት አቅጣጫ ተቀመጠ።የግምገማ መድረኩም የሀዋሳ  ከተማ ደጋፊ አመራር  እንዲሁ...
25/05/2026

በ2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 7ተኛ ዙር ሀገራዊ ምርጫን አስመልክቶ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን በመገምገም ለቀጣይ ተግባራት አቅጣጫ ተቀመጠ።

የግምገማ መድረኩም የሀዋሳ ከተማ ደጋፊ አመራር እንዲሁም የሀዋሳ ከተማ ብ/ፓ/ቅ/ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መስፍን አየለ ባሉበት ተካሂዷል ።

የ ‎7ኛው ዙር ሀገራዊና ክልላዊ ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተቀመጠው ጊዜ ሰሌዳ መሰረት እንዲሁም የብልጽግና ፖርቲ ባስቀመጠው ሁለት መንታ ግቦችን በመያዝ በሰላማዊና ፍፁም ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የተለያዩ ቅድመ ዝግጅት ላይ ከክፍለ ከተማዎና ከቀበሌ አመራሩ ጋር እየተሰሩ በሉ ተግባራት ላይ በጥልቀት በመገምገም በነገው እለት ለሚደረገው የድጋፍ ሰልፍ እና ለቀጣይ ስራዎች አቅጣጫ ተቀምጧል።





የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ  አዛዥ ኮማንደር ተስፋዬ ሌዳሞ በከተማ እየተካሄደ ያለውን አርሰናል የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን መሆኑን አስከትሎ የእግር ኳስ የደጋፊዎች ድባብ ሰላማዊና ያለምን...
24/05/2026

የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ተስፋዬ ሌዳሞ በከተማ እየተካሄደ ያለውን አርሰናል የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን መሆኑን አስከትሎ የእግር ኳስ የደጋፊዎች ድባብ ሰላማዊና ያለምንም ሁከት እንዲከናወን ከ10:00 ሰዓት ጀምሮ የሞተር ሰይክል እንቅስቃሴዎችን የተከለከለ መሆንን የገለፁ ሲሆን አንዳንድ አላሳፈላጊ ጭወትና የመንገድ ላይ ረብሻን በህግ የተከለከለ እንደሆነ ገልፀዋል ።

18/05/2026
በሀዋሳ ከተማ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ አባላት እና ደጋፊዎች ''ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር'' በሚል መሪቃል ክፍለ ከተማዊ የጎዳና ላይ የምረጡኝ ቅስቀሳ አከናወኑ። በመርሃ...
16/05/2026

በሀዋሳ ከተማ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ አባላት እና ደጋፊዎች ''ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር'' በሚል መሪቃል ክፍለ ከተማዊ የጎዳና ላይ የምረጡኝ ቅስቀሳ አከናወኑ።

በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙ የፓርቲ አመራሮች ብልፅግና ፓርቲ ህዝብን መሰረት ያደረገ የፖለቲካ እና የልማት ጉዞ እያካሄደ መሆኑን ገልፀው፣ የህዝቡ ንቁ ተሳትፎ የሀገሪቱን የወደፊት ስኬት እንደሚወስን አስታውቀዋል። በመጪው ምርጫም ህብረተሰቡ በንቃት በመሳተፍ ለሀገር እድገትና መረጋጋት የሚበጅ ውሳኔ እንዲያሳልፍ ጥሪ አቅርበዋል።

Address

Awassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሐዋሳ ከተማ አስተዳደር የአዲስ ከተማ ክ/ከ/አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share