11/07/2026
✴️ በቴህራን የሚገኘው የተግባራዊ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር የሆኑት ሞስታፋ ኾሽቼሽም ለአልጀዚራ እንደተናገሩት በቀድሞው ጠቅላይ መሪ አሊ ኻሜኒ ላይ የተፈጸመውን ግድያ ተከትሎ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢራናውያን የበቀል እርምጃ እንዲወሰድ አጥብቀው እየጠየቁ ይገኛሉ። ፕሮፌሰሩ ይህን ያሉት የቀድሞው መሪ የሽኝት ስነ-ስርዓት ከመካሄዱ በፊትም ህዝቡ ቁጣውን ሲገልጽ እንደነበር በማስታወስ ነው።
አዲሱ ጠቅላይ መሪ ሞጅታባ ኻሜኒ የአባታቸውን ግድያ ለመበቀል የገቡትን ቃል በተመለከተ ፕሮፌሰሩ ሲያብራሩ፣ ኢራናውያን በየምሽቱ አደባባይ በመውጣት እያሰሙ ያሉት ድምጽ እያደገ ለመጣው የህዝብ የበቀል ጥያቄ ትክክለኛ ምላሽ መሆኑን ገልጸዋል።
"አሜሪካውያን የኢራንን መሪ እና ከፍተኛ ጄኔራሎች መግደላቸው ትክክል ነው፣ ኢራናውያንም ይህን አምነው ዝም ብለው መቀመጥ አለባቸው የሚል ማንም ሰው በዓለም ላይ ይኖራል ብዬ አላምንም" ያሉት ኾሽቼሽም፣ አሜሪካውያን ለፈጸሙት ጥቃት ተገቢውን ዋጋ ካልከፈሉ፣ በአደባባይ እያስጠነቀቁ እንዳሉት አዲሱንም ጠቅላይ መሪ ከመግደል ወደኋላ እንደማይሉ ስጋታቸውን አስቀምጠዋል።
አሜሪካውያን ከኢራን ጋር ለሚደረግ ለማንኛውም ዓይነት ስምምነት ታማኝ ሆነው ስለማያውቁ፣ በቀጣይ ቀናት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግጭት እና ወታደራዊ ውጥረት መባባሱ ፈጽሞ የማይቀር ጉዳይ መሆኑን ምሁሩ አክለው አስጠንቅቀዋል" ስል የዘገበው አልጀዚራ ነው
صالح عبد الله
Salih Abdella