01/06/2026
አትሌት ሰለሞን ባረጋ በእንግሊዝ የግሬት ማንቸስተር 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ድንቅ ብቃቱን በማሳየት በድጋሚ አሸነፈ
ግንቦት 23/2018 ዓ.ም
አትሌት ሰለሞን ባረጋ ፈታኝ የነበረውን የግሬት ማንቸስተር የ10 ኪሎ ሜትር ውድድር በ27 ደቂቃ ከ37 ሰከንድ በማጠናቀቅ አሸንፏል ።
አትሌት ሰለሞን ባረጋ ዘንድሮ ያስመዘገበው የ27 ደቂቃ ከ37 ሰከንድ ሰዓት፣ ባለፈው ዓመት በተመሳሳይ ውድድር ላይ ካስመዘገበው ሰዓት ጋር ሲነጻጸር ከ10 ሰከንድ በላይ መሻሻል ማሳየቱ የዘንድሮውን ድል ልዩ ያደርገዋል።
አትሌት ሰለሞን በአምናው የ2025 የግሬት ማንቸስተር ውድድር ላይ 27 ደቂቃ ከ49 ሰከንድ በሆነ አስገራሚ ፍጥነት በመግባት የራሱን ምርጥ ሰዓት አስመዝግቦ በአንደኝነት ማጠናቀቁ ይታወሳል ።
ዘንድሮ ደግሞ ያንን የራሱን የላቀ ሰዓት በማሻሻል በውድድሩ ላይ ያለውን የበላይነት በድጋሚ አረጋግጧል ።
ምንጭ :-AMN