በካማሽ ዞን የምዥጋ ወረዳ መንግስት ኮሙንኬሽን ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Asosa
  • በካማሽ ዞን የምዥጋ ወረዳ መንግስት ኮሙንኬሽን ጽ/ቤት

በካማሽ ዞን የምዥጋ ወረዳ መንግስት ኮሙንኬሽን ጽ/ቤት ወቅታዊና ፈጣን መረጃዎችን ለወረዳው ህዝብና መንግስት እናደርሳለን።

24/10/2025

የመንግስት ሠራተኞች ተሻሽሎ የወጣው #አዋጅ 1353/2017 ስለደሞዝ ስኬል ምን ይላል?For your understanding.
www.csc.gov.et
++++++++++++++++++++++++++
ክፍል ሶስት አንቀፅ 9 የደሞዝ ስኬል ማስተካከያ
1. የደሞዝ ስኬል ማስተካከያ ዓላማ ከፍተኛ እውቀትና ችሎታ ያለውን ባለሙያ ለመሳብ፣ለማቆየትና ሠራተኛውን ለማትጋት የሥራ ውጤቱን ለማሻሻል የሚያስችል የደሞዝ አከፋፈል ሥርዓት ለመወሰን ነው፡።

2. ኮሚሽኑ የመንግስት ሰራተኞች የደሞዝ ሰኬል ማስተካከያ የመንግስትን የፋይናስ አቅም ፣የሕዝቡን አጠቃላይ የኑሮ ሁኔታ፣የዋጋ ደረጃዎችና ግሽበት እና አግብብነት ያለውን ሌሎች ሁኔታዎች ባገናዘበ መንገድ በየጊዜው እያጠና ለሚኒስትሮች ምክር ቤት አቅርቦ ያስወስናል ፣መመሪያ በማውጣት አፈፃፀሙን ይቆጣጠራል፡፡

3. የደመወዝ ስኬል ለያንዳንዱ የሥራ ደረጃ መነሻ እና ከፍተኛ መድረሻ ደመወዝ እንዲሁም በየጊዜው የሚደረገውን የደመወዝ ጭማሪ የሚያመለክቱ እርከኖች ይኖሩታል፡፡

4. ኮሚሽኑ የሥራ ደረጃ ዝቅተኛ ደመወዝ እና ከፍተኛ ደመወዝ ጣሪያ በየአራት አመቱ አጥንቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት አቅርቦ ያስወስናል፣አፈፃፀሙን ይቆጣጠራል፡፡

አዲሱ የ- #ገቢዎች የደመወዝ ስኬት ይፋ ሆነመንግሥት በቅርቡ ተግባራዊ እያደረገ ያለውን የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን በላቀ ደረጃ ለማስፈጸም ለመንግሥት ሠራተኞች እና አመራሮች...
24/10/2025

አዲሱ የ- #ገቢዎች የደመወዝ ስኬት ይፋ ሆነ

መንግሥት በቅርቡ ተግባራዊ እያደረገ ያለውን የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን በላቀ ደረጃ ለማስፈጸም ለመንግሥት ሠራተኞች እና አመራሮች የደመወዝ ማስተካከያ እንዲደረግ ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ጥናቱ ለመንግሥት ቀርቦ ተወስኗል፡፡

በዚሁ መሠረት ከመስከረም 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ሰመንግሥት ሠራተኞች፣ ተሿሚዎች እና
የህዝብ ተመራጮች ተግባራዊ እንዲደረግ የገንዘብ ሚኒስቴር መስከረም 20 ቀን 2018 ዓ.ም. በቁጥር በበ18/6/134 በተጻፈ ደብዳቤ ገልጾልናል፡፡

ውሳኔውን ለማስፈጸም የተዘጋጀው የደመወዝ ማስተካከያ መመሪያ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የኮሚሽነሮች ጉባኤ ታይቶ ከመስከረም 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የጸደቀ ሲሆን፣ በፍትህ ሚኒስቴርም መመሪያ ቁጥር 1110/2018 ተብሎ የተመዘገበና በሚኒስቴሩ ድረ-ገጽ መጫኑን አስታውቆናል፡፡

የመንግሥት ሠራተኞችን የደመወዝ ማስተካከያ መጠን መሠረት በማድረግ የልዩ የደመወዝ ስኬል ተጠቃሚዎችን የደመወዝ ማሻሻያ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አዘጋጅቶ ለየተቋማቱ እንዲያስተላልፍ በመንግሥት በተወሰነው መሠረት-

1. የተሻሻለውን የተቋሙ የደመወዝ ስኬል ሠንጠረዥ፣
2. የደመወዝ ስኬል መሸጋገሪያ ሠንጠረዥ እና
3. የደመወዝ ስኬል ዝርዝር የአፈጻጸም መመሪያ ቁጥር
1110/2018፣

ከዚህ ደብዳቤ ጋር አያይዘን እየላክን፣ በጀቱን ከገንዘብ ሚኒስቴር በመጠየቅ ክፍያውን መፈፀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ በተጨማሪም ውሳኔውን በፍጥነት በማስፈጸም ውጤቱን እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ እንድታስታውቁን እናሳስባለን፡፡

ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን

24/10/2025
የመንግስት ሰራተኞች አዲሱ አዋጅ  ቁጥር 1353/2017 ምን ይላል? For your understanding.ከባድ የዲሲፕሊን ቅጣት የሚያስከትሉ ጥፋቶች አንቀፅ 69/5 አዋጁ እንዲህ አስቀምጦታ...
23/10/2025

የመንግስት ሰራተኞች አዲሱ አዋጅ ቁጥር 1353/2017 ምን ይላል? For your understanding.
ከባድ የዲሲፕሊን ቅጣት የሚያስከትሉ ጥፋቶች አንቀፅ 69/5 አዋጁ እንዲህ አስቀምጦታል።
+++++++++++++++++++++++++
1.ሕጋዊ_ትእዛዝን ባለማክበር፣ በቸልተኝነት፣ በመልገም፣ ወይም ሆነ ብሎ የአሠራር ሥነ-ሥርዓት ወይም የመንግስትን ፖሊሲ ባለመከተል በሥራ ላይ በደል ማድረስ፤‎‎
2. ጉዳዮችን ሆን ብሎ ማዘግየት ወይም ባለጉዳዮችን ማጉላላት፤
‎‎3. ሥራ እንዳይሠራ ሆን ብሎ ማወክ ወይም ከሚያውኩት ጋር መተባበር፤‎‎
4. በቀላል የዲስፕሊን ቅጣት እርምጃዎች ባለመታረም ያለበቂ ምክንያት በተደጋጋሚ ከሥራ መቅረት ወይም የሥራ ሰዓት አለማክበር፤
‎‎5. በሥራ ቦታ በጠብ አጫሪነትን መደባደብ፤
‎‎6. በልማዳዊ ስካር ወይም በአደንዛዥ ዕፅ ሱስ በመመረዝ ሥራን መበደል፤
‎‎7. ጉቦ መቀበል ወይም እንዲሰጠው መጠየቅ፤
‎‎8. በሥራ ቦታ ለሕዝብ ሞራል ተቃራኒ የሆነ ድርጊት መፈጸም፤
‎‎9. የሌብነት ወይም የእምነት ማጉደል ድርጊት መፈጸም፤‎‎
10.የማታለል ወይም የማጭበርበር ድርጊት መፈጸም፤‎‎
11. በመሥሪያ ቤቱ ንብረት ላይ ሆን ብሎ ወይም በቸልተኝነት ጉዳት ማድረስ፤
‎‎12. በሥልጣን አለአግባብ መጠቀም፤‎‎
13. በሥራ ቦታ ላይ ፆታዊ ትንኮሳ ወይም ጥቃት መፈፀም እና
14.በዚህ አንቀፅ ከተዘረዘሩት ጋር ተመሳሳይ ክብደት ያለው ሌላ የዲሲፕሊን ጉድለት መፈፀም ።
++++++++++++++++++++++++++

አንቀፅ 72/1 እና 2
ሠራተኛን ከሥራ አግዶ ስለማቆየት

1.ማንኛውም የመንግስት ሠራተኛ ከሥራ አግዶ ማቆየት የሚቻለው
(ሀ)ከተጠረጠረበት ጉዳይ ጋር አግባብነት ያላቸውን ማስረጃዎች በማበላሸት:በመደበቅ ወይም በማጥፋት ምርመራውን ያሰናክላል
(ለ)በመንግስት ንብረት ላይ ተጨማሪ ጉዳት ያደርሳል
(ሐ)ከተከሰሰበት ጥፋት ክብደት አንፃር የሌሎችን ሰራተኞች ሞራል የሚነካ ወይም የተገልጋዩን ሕዝብ በመሥሪያ ቤቱ ላይ ሊኖረው የሚገባውን እምነት ያዛባል
(መ)ተፈፀመ የሚባለው ጥፋት ከሥራ ያስወጣል ተብሎ ሲገመት ነው
2.በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ (1) መሰረት አንድ ሠራተኛ ከሥራና ከደሞዝ ታግዶ ሊቆይ የሚችለው ከሁለት ወር ለማይበልጥ ጊዜ ይሆናል።

የወረዳው አመራሮች የስራ ርክክብ አደረጉ።(ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም❨ምዥጋ❩)በወረዳው በተካሄደው 44ኛው አስቸኳይ ጉባኤ የአመራሮች ሽግሽግና አዲስ ሹመቶች በም/ቤቱ ተሰጥተዋል።በዚህም መሠረ...
22/10/2025

የወረዳው አመራሮች የስራ ርክክብ አደረጉ።

(ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም❨ምዥጋ❩)በወረዳው በተካሄደው 44ኛው አስቸኳይ ጉባኤ የአመራሮች ሽግሽግና አዲስ ሹመቶች በም/ቤቱ ተሰጥተዋል።

በዚህም መሠረት የወረዳው ም/አስተዳዳሪ ሆነው ሲሰሩ የነበሩት አቶ ታምሩ ሠንበታ በወረዳው ም/ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ሆነው ሲያገለግሉ ለነበሩትና ም/አስተዳዳሪ ሆነው ለተሾሙት ወ/ሮ የሹሜ አቦሴ የስራ ርክክብ አድርገዋል።

በተመሳሳይ በወረዳው ም/አስተዳዳሪ ማዕረግ የስነ-ምግባርና ኢንስፔክሽን ጽ/ቤት ኃላፊ የነበሩት አቶ አምባ ድጉማ በአዲስ ለተሾሙት የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ሠንበታ ኢቱ የስራ ርክክብ አድርገዋል።

በክልሉ 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓልን በድምቀት ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ ነው፡- የተከበሩ አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ(ጥቅምት 12/2018 ዓ/ም❨ምዥ...
22/10/2025

በክልሉ 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓልን በድምቀት ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ ነው፡- የተከበሩ አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ

(ጥቅምት 12/2018 ዓ/ም❨ምዥጋ❩) ‎በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓልን በደማቅ ሁኔታ ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ ተናገሩ፡፡

የክልሉ ምክር ቤት ጽ/ቤት የበዓሉን አከባበር አስመልክቶ ከበዓሉ ዐቢይ ኮሚቴ፣ ከብሔረሰብ ምክር ቤቶች እና በየደረጃው ከሚገኙ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤዎች እንዲሁም የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አመራሮች ጋር ውይይት አድርጓል።

‎የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፣ በክልሉ ባለፉት ዓመታት የብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓል በተለያዩ ሁነቶች በድምቀት ሲከበር መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡

የዘንድሮውን 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓልን በልዩ ድምቀት ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረው፣ ክልላዊ ዐቢይ እና ንኡሳን ኮሚቴዎች ተቋቁመው ወደሥራ መግባታቸውን ገልጸዋል፡፡

‎በዓሉን ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ማክበር ይገባል ያሉት ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ፣ ለዚህም ሁሉም የባለቤትነት ድርሻውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

‎የዘንድሮው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓልን ትልልቅ ስኬቶችን ካገኘንብት ማግስት መከበሩ ልዩ እንደሚያደርገው ገልጸው፣ በክልሉ በየደረጃው ያለውን የበዓል አከባበር ሂደት በሚዲያና ኮሙኒኬሽን ማጀብ እንደሚገባ ጠቅሰዋል፡፡

የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ መለሰ ኪዊ፣ በክልሉ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓል በሁሉም አካባቢዎች እንደሚከበር ጠቁመው፣ በክልል ደረጃ በካማሺ ከተማ እንደሚከበር ገልጸዋል፡፡

‎የበዓሉን ሂደት በሚዲያ ማጀብ መረጃዎችን በወቅቱ ለሕዝቡ ማድረስ እንደሚገባም አቶ መለሰ ተናግረዋል፡፡
‌‎
የዘንድሮው 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን “ዴሞክራሴያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ በሆሳዕና ከተማ በድምቀት ይከበራል።

‌‎የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ

20/10/2025
የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት በወረዳው ስር ለሚገኙ አምስት ትምህርት ቤቶች የማስተማሪያና የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።(ጥቅምት፦ 10/2018ዓ.ም ❨ምዥጋ❩) ድጋፉ ከካማሽ ዞን አስተዳደር ለ...
20/10/2025

የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት በወረዳው ስር ለሚገኙ አምስት ትምህርት ቤቶች የማስተማሪያና የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

(ጥቅምት፦ 10/2018ዓ.ም ❨ምዥጋ❩) ድጋፉ ከካማሽ ዞን አስተዳደር ለወረዳው የተበረከተ መሆኑን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ምትኩ ናኖ ገልፀው በትምህርት ዘርፉ አፈጻጸም 96% ላይ እንደሆነና በቀጣይም ከዚህ በላይ መስራትና በተለይም በአንዳንድ ትምህርት ቤቶች የሚስተዋሉ የተማሪዎች መውደቅ በጥልቀት ታይቶ ሊሰራበት ይገባል ብለዋል።

በአንዳን ትምህርት ቤቶች የሚያስተምሩ መምህራን ስነ-ምግባርና በወቅቱ በመማር መስተማር ስራቸው ላይ በማይገኙትም ላይ የቀበሌ አመራሮችና የትምርት ቤት ርዕሳነ መምህራን የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡና መምህራን የመማር ማስተማር ስራቸውን በአግባቡ እንዲወጡ መደረግ እንደሚገባም አስተዳዳሪው አሳስበዋል።

ትምህርት ቤቶች ከውስጥ ገቢም ቢሆን አቅመ ደካማ የሆኑትንና ድጋፍ የሚሹ ተማሪዎችን መደገፍና መከታተልም አስፈላጊና የትምህርት ስርዓቱን ከነአፈፃፀሙ እንዲሻሻል ያደርጋልም ሲሉ አቶ ምትኩ ናኖ አክለዋል።

20/10/2025
የምዥጋ ወረዳ በ44ኛ አስቸኳይ ጉባኤው የተለያዩ ሹመቶችን አፀደቀ።(ጥቅምት 10/2018 ዓ.ም❨ምዥጋ❩)የወረዳው ምክር ቤት 44ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ያካሄደ ሲሆን የተለያዩ ሹመቶችንም ሰጥቷል። ...
20/10/2025

የምዥጋ ወረዳ በ44ኛ አስቸኳይ ጉባኤው የተለያዩ ሹመቶችን አፀደቀ።

(ጥቅምት 10/2018 ዓ.ም❨ምዥጋ❩)የወረዳው ምክር ቤት 44ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ያካሄደ ሲሆን የተለያዩ ሹመቶችንም ሰጥቷል። በዚህም መሰረት፦
1ኛ. አቶ ቦጂ አልሞሳ የምዥጋ ወረዳ ዋና አፈ-ጉባኤ
2ኛ. አቶ ዋቡሾ ትሊንቲ የምዥጋ ወረዳ ም/አፈ-ጉባኤ
3ኛ. ወ/ሮ የሹሜ አቦሴ የም/ወረዳ ም/አስተዳዳሪ
4ኛ. አቶ ታምሩ ሠንበታ የም/ወ/ሠ/ማ/ጉ/ስራ ዕድል ፈጠራ ጽ/ቤት ኃላፊ
5ኛ. አቶ ገዛኸኝ መኮንን የም/ወረዳ ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ጽ/ቤት ኃላፊ
6ኛ. አቶ ጥበቡ ታምሩ የም/ወረዳ ንግድ መንገድና ትራንስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ
7ኛ. አቶ ገለታ መኮንን የም/ወረዳ አካባቢ ደን መሬት ማህበራት ማደራጃ ጽ/ቤት
8ኛ. አቶ ታመነ ሃምቢሳ የም/ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ
9ኛ. አቶ አብረሃም አዳል የም/ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ
10ኛ. ወ/ሮ ናስሬ ዘነበ የም/ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ም/ኃላፊ
11ኛ. አቶ ሠንበታ ኢቱ በወረዳው ም/አስተዳዳሪ ማዕረግ የስነ-ምግባርና ኢንስፔክሽን ጽ/ቤት ኃላፊ አድርጎ በምክር ቤት አባላቱ ፊት አፅድቋል።

በመጨረሻም ባለ 3 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ጉባኤው ተጠናቋል።

19/10/2025

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
********************

የቀድሞው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ባጋጠማቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የፕሬዝደንቱ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ለኢቢሲ አስታውቀዋል፡፡

Address

Asosa

Telephone

+251980248886

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በካማሽ ዞን የምዥጋ ወረዳ መንግስት ኮሙንኬሽን ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share