31/05/2026
በአሶሳ ሆሃ እና አሶሳ መገሌ የምርጫ ክልሎች ለድምጽ መስጫ የሚሆኑ የቁሳቁስ ስርጭት ተጠናቋል
አሶሳ፤ ግንቦት 23/2018(ኢዜአ)፦ በአሶሳ ሆሃ እና አሶሳ መገሌ የምርጫ ክልሎች ስር በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ለድምጽ መስጫ የሚሆኑ የቁሳቁስ ስርጭት መጠናቀቁን የምርጫ ክልሎቹ አስተባባሪዎች ተናገሩ።
የአሶሳ መገሌ ምርጫ ክልል አስተባባሪ ሀብታሙ ተስፋዬ እንደገለፁት፤ በምርጫ ክልሉ በሚገኙ 48 የምርጫ ጣቢያዎች ላለፉት ሁለት ቀናት የምርጫ ቁሳቁስ ስርጭት ሲካሄድ ቆይቷል።
በአሁኑ ሰዓት በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች መድረሱን ገልፀው፥ ቁሶቹ አስፈላጊውን ጥበቃ እየተደረገላቸው መሆኑንም ተናግረዋል።
የአሶሳ መገሌ ምርጫ ክልል አስተባባሪ እሱባለው ንጋቱ በኩላቸው፤ በምርጫ ክልሉ በሚገኙ 68 የምርጫ ጣቢያዎች ሲከናወን የቆየው የቁሳቁስ ስርጭት መጠናቀቁን ገልጸዋል።
በአሶሳ ከተማ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ባደረግነው ቅኝት የድምጽ መስጫ ሳጥን፣ የመራጮች ድምጽ መስጫ መከለያ እና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች በወቅቱ ደርሰዋል።
#ኢዜአ