የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ

  • Home
  • Ethiopia
  • Asosa
  • የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ Benishangul-Gumuz Region Government Communication Affairs Bureau. It is a government organization You can follow us on: telegram: https://t.me/Bgcommn

This is the official Benishangul gumuz region communication affairs office page - where you can get all the latest news in Amharic.

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝቡ ሀገራዊ ኃላፊነቱን በተግባር አሳይቷል፦ የአሶሳ ከተማ ነዋሪዎች******************ባለፈው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ፤...
04/06/2026

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝቡ ሀገራዊ ኃላፊነቱን በተግባር አሳይቷል፦ የአሶሳ ከተማ ነዋሪዎች
******************

ባለፈው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ፤ ኢትዮጵያውያን በነቂስ ወጥተው ድምፅ በመስጠት ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን በታሪካዊ መልኩ የተወጡበት ዕለት እንደነበር የአሶሳ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልም በሁሉም አካባቢዎች ምርጫው በሕዝቡ ንቁ ተሳትፎና ደማቅ አጋርነት የተከናወነ ሲሆን፤ የአሶሳ ከተማ ነዋሪዎችም በዕለቱ የነበረውን ዝናብና ፀሐይ ሳይበግራቸው፣ ዲሞክራሲ መብታቸውን በመጠቀም ይበጀናል ላሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምፃቸውን በነፃነት መስጠታቸውን ተናግረዋል።

ነዋሪዎቹ ከኢቲቪ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ረጃጅም ሰልፎችን በትዕግሥት በመጠበቅ ከንጋት እስከ ምሽት በትጋት ድምፅ ሲሰጡ መዋላቸው ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት መሥረታና ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ፅኑ ፍላጎት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።

ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ የድምፅ መስጫውን ዕለት በከፍተኛ ጉጉት ሲጠብቁ እንደነበር ያወሱት ነዋሪዎቹ፥ በዕለቱ በላቀ የሀገራዊ ኃላፊነት ስሜት ድምፃቸውን ማሳረፋቸውን ተናግረዋል።

አያይዘውም በምርጫው አሸናፊ በመሆን በቀጣይ ሕዝቡን የሚያስተዳድረው አካል የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማሻሻልና ጥያቄዎችን ለመመለስ በትጋት መሥራት እንደሚጠበቅበት አስገንዝበዋል።

ኢቢሲ

በክልሉ ምርጫው ያለምንም ችግር በሰላም እንዲጠናቀቅ ዘብ ለቆሙና ሌሊት ከቀን ለደከሙ አካላት ምስጋና ይገባል፡- ምክትል ርዕሰ-መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ*********************...
04/06/2026

በክልሉ ምርጫው ያለምንም ችግር በሰላም እንዲጠናቀቅ ዘብ ለቆሙና ሌሊት ከቀን ለደከሙ አካላት ምስጋና ይገባል፡- ምክትል ርዕሰ-መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ
*********************

(አሶሳ፤ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክትል ርዕሰ-መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ በክልሉ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለምንም የጸጥታ መስተጓጎል በሰላም እንዲጠናቀቅ ዘብ ለቆሙና ሌሊት ከቀን ለደከሙ አካላት ምስጋና አቀረቡ፡፡

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝቡ የነገውን ተስፋና ዕድል ለሚወስንለት ፓርቲ በሰለጠነና እጅግ በሚያኮራ ሁኔታ ድምፁን መስጠቱንም አቶ ጌታሁን ገልጸዋል፡፡

ምክትል ርዕሰ-መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ 7ተኛዉ ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ስኬታማ በሆነ መንገድ በመጠናቀቁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

የምርጫ በሰላም መጠናቀቅ የክልሉን መንግስት ብስለት፣ ሕዝቡ ለሰላም ያለውን ፅኑ ፍላጎት እና የአንድነታችንን ጥንካሬ ያስመሰከረ ታላቅ ነው ያሉት አቶ ጌታሁን፣ ሕዝቡ በሰለጠነና እጅግ በሚያኮራ ሁኔታ ድምፁን በመስጠት የነገውን ተስፋና ዕድል በገዛ እጁ መመስረቱን ተናረዋል።

በየደረጃው የሚገኙ ጸጥታ አካላት በየአካባቢው ሙሉ በሙሉ ሰላማዊና አስተማማኝ ሁኔታ በመፍጠር ዜጎች ያለስጋት ድምጻቸውን እንዲሰጡ በማድረግ ላበረከቱት ትልቅ አስተዋጽዖ ያላቸውን አክበሮት ገልጸዋል፡፡

ምክትል ርዕሰ-መስተዳድሩ ምርጫው ያለምንም የጸጥታ መስተጓጎል በሰላም እንዲጠናቀቅ ዘብ ለቆሙና ሌሊት ከቀን ለደከሙ አካላት በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

የምርጫው በሰላም መጠናቀቅ የትልቅ ጉዞ መጀመሪያ እንጂ ማብቂያ አይደለም ያሉት አቶ ጌታሁን፣ አሁን በጋራ የገነባነው ሰላም ይበልጥ እንዲጸና፣ የክልላችን ልማትና መልካም አስተዳደር እንዲፋጠን እና የወጣቶቻችን የወደፊት ዕድል እንዲያብብ ሁላችንም እጅ ለእጅ ተያይዘን የምንሰራበት ጊዜ ላይ እንገኛለን ብለዋል።

በአሶሳ ከተማ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የከተማዋን እንቅስቃሴ አቀላጥፏል***********************(አሶሳ፤ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም) በአሶሳ ከተማ እየተከናወነ የሚገ...
04/06/2026

በአሶሳ ከተማ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የከተማዋን እንቅስቃሴ አቀላጥፏል
***********************

(አሶሳ፤ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም) በአሶሳ ከተማ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የከተማዋን የትራፊክ ፍሰትና አጠቃላይ እንቅስቃሴ ለማቀላጠፍ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ።

በአሶሳ ከተማ እየተካሄደ ያለው የኮሪደር ልማት፤ የከተማዋን መሠረተ ልማት ለማዘመን፣ የነዋሪዎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻልና ከተማዋን ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ሳቢ ለማድረግ ታስቦ የተጀመረ ሰፊ መርሃ ግብር ነው።

በአንደኛው ዙር የተከናወኑት ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ተከትሎ፣ አሁን ላይ ትኩረቱን የንግድና ማህበራዊ አገልግሎት ማዕከላትን ማዘመን ላይ ያደረገው ሁለተኛው ዙር ስራ በስፋት እየተገነባ ይገኛል።

የሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት፣ ዘመናዊ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላትን ብቻ ሳይሆን ምቹ የእግረኛና የተሽከርካሪ መንገዶችንም በማካተት የከተማዋን ገጽታ እየቀየረ ይገኛል።

አስተያየታቸውን የሰጡን የከተማዋ ነዋሪዎች እንደገለጹት፣ የእግረኛ እና የተሽከርካሪ መንገዱ ተለይቶ መሰራቱ የትራፊክ ፍሰቱን በእጅጉ አቅልሎታል።

ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ማስረሻው አራጌ እንዳሉት፣ ከዚህ ቀደም የነበረው መንገድ ጠባብ ከመሆኑ የተነሳ ለተሽከርካሪም ሆነ ለእግረኞች ምቹ እንዳልነበር አስታውሰዋል።

በአሁኑ ወቅት ግን በኮሪደር ልማቱ ለሁሉም ምቹ መንገድ በመፈጠሩ፣ የትራፊክ እንቅስቃሴው መሳለጡን አቶ ማስረሻው ተናግረዋል።

ሌላዋ የከተማዋ ነዋሪ የሺወርቅ ንብረት፤ የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን በሁሉም መስክ ለነዋሪዎቿ ምቹ እንድትሆን አድርጓታል ብለዋል።

በተለይም በሁለተኛው ዙር እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት፣ በእግረኞች ላይ ይደርስ የነበረውን የትራፊክ አደጋ በመቀነስ ረገድ አይነተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።

በከተማዋ የባጃጅ አሽከርካሪ የሆነው አህመድ ሰኢድ በበኩሉ የኮሪደር ልማቱ ለአሸከርካሪዎች ነፃነትን የሰጠ እና ለተሽከርካሪዎችም ምቹ መሆኑን ተናግሯል።

የኮሪደር ልማቱ ለአሸከርካሪዎች እና እግረኞች የፈጠረው ምቹ ሁኔታ የትራፊክ አደጋን ከመቀነስ አንፃር ትልቅ ትርጉም አለው ያሉት ደግሞ በአሶሳ ከተማ የትራፊክ ተቆጣጣሪ ምክትል ሳጅን ኢዘዲን አልበሽር ናቸው።

የኮሪደር ልማቱ የትራፊክ ተቆጣጣሪዎችን የሥራ ጫና የቀነሰ እና የተቀላጠፈ የትራፊክ እንቅሰቃሴ እንዲፈጠር አይነተኛ ሚና ያበረከተ መሆኑን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያን ዴሞክራሲ ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረው ምርጫ ************7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የዴሞክራሲና የሀገረ መንግሥት ግንባታ ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ነው አሉ የህ...
03/06/2026

የኢትዮጵያን ዴሞክራሲ ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረው ምርጫ
************

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የዴሞክራሲና የሀገረ መንግሥት ግንባታ ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ነው አሉ የህግና ፌደራሊዝም ባለሙያ በላይ ወዲሻ።

ባለሙያው ከፋና ፖድካስት ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ዜጎች ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 6 ሰዓት በሰላማዊ መንገድ ድምፅ መስጠታቸውን አስታውሰዋል።

ይህም በሀገሪቱ የፖለቲካ ንቃትና የዴሞክራሲ ባህል መዳበሩን የሚያሳይ ነው ብለዋል።

የዘንድሮው የፖለቲካ ፓርቲዎች ቅስቀሳ፣ የምርጫ ቦርድ ዝግጅትና በዕለቱ የምርጫ ሂደት የታየው መነቃቃት የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት ረገድ አዎንታዊ ሚና እንደነበረው ጠቅሰዋል።

የመገናኛ ብዙሃን እና የሲቪክ ማህበራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ገልጸው፤ ጠቅላላ ውጤቱ ይፋ እስኪሆን መጠበቅ የሁሉም ፖለቲካ ፓርቲዎች እና የዜጎች ቀጥተኛ ኃላፊነት ነው ብለዋል።

ፓርቲዎች ውጤቱ ይፋ ሳይሆን ከመገመት ተቆጥበው ሂደቱን በትዕግስት መጠበቅ እስኪገለጽ መጠበቅ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

በውጤቱ ፓርቲ ሳይሆን ኢትዮጵያ ናት የምታሸንፈው ያሉት ባለሙያው፤ ፓርቲዎች ውጤቱን በፀጋ ተቀብለው በሀገር ልማት እና ግንባታ ላይ በንቃት መሳተፍ ይገባቸዋል ሲሉ ገልጸዋል።

የምርጫው በሰላም መጠናቀቅ ለሀገር ግንባታ ዋስትና መሆኑን ጠቅሰው፤ በህዝብ ድምፅ የበላይነት ያገኘው ፓርቲ ለሕዝብ የገባውን ቃል በታማኝነት የመፈጸም ኃላፊነት እንዳለበትም ጠቁመዋል።

ምርጫው የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ፣ ተዓማኒነትን ለመገንባት እና የኢትዮጵያን የሀገር ግንባታ ጉዞ ለማፅናት ትልቅ ስኬት መሆኑንም አንስተዋል።

ኤፍ ኤም ሲ

የህግና ፌደራሊዝም ባለሞያ በላይ ወዲሻ
ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትንን ቆይታ ማስፈንጠሪያውን ተጭነው መከታተል ይችላሉ!
https://youtu.be/jUX8tmYTsbg?si=gPK-NLi5ZS9_is6X

በምርጫ ክልል ደረጃ የድምፅ ማዳመር ሥራ እየተከናወነ ነው - ምርጫ ቦርድ****************** የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በወቅታዊ የምርጫው ሂደት ዙሪያ...
03/06/2026

በምርጫ ክልል ደረጃ የድምፅ ማዳመር ሥራ እየተከናወነ ነው - ምርጫ ቦርድ
******************

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በወቅታዊ የምርጫው ሂደት ዙሪያ በሰጡት መግለጫ፣ በየምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ ቆጠራ ተጠናቅቆ ውጤት መለጠፉን እና አሁን ላይ በምርጫ ክልል ደረጃ የማዳመር ሥራ በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

ሰብሳቢዋ በመግለጫቸው እንዳብራሩት፣ በልዩ ልዩ ምክንያቶች ዘግይተው የነበሩ የምርጫ ጣቢያዎችን የድምፅ ቆጠራ ሂደት ትናንት ማጠናቀቅ የተቻለ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች የተመዘገቡ ውጤቶች ለሕዝብ ዕይታ ክፍት ሆነው ተለጥፈዋል።

ሂደቱን ተከትሎም በምርጫ ክልል ደረጃ የማዳመር ሥራ እየተሠራ እንደሚገኝ እና የምርጫ ክልል ውጤቶችም ወደ ዋናው የምርጫ ማዕከል መምጣት መጀመራቸውን ሰብሳቢዋ ገልጸዋል።

በዚህም መሠረት በውጤት ማመሳከሪያ እና መሙያ ቅጾች ላይ የሰፈሩት መረጃዎች ከየምርጫ ጣቢያው ወደ ምርጫ ክልል እየመጡ መሆኑን ጠቁመዋል።

እነዚህ መረጃዎች ወደ ምርጫ ክልሉ ሲደርሱም በጣቢያዎቹ በአካል ከተሰጠው ድምፅ አንጻር ትክክለኛነታቸው በጥብቅ እየተመሳከረ ርክክብ እየተፈጸመ እንደሚገኝ የቦርዱ ሰብሳቢ አብራርተዋል።

በተጨማሪም የድምፅ ቆጠራ እና ማዳመር ሂደቱን ትክክለኛነት የሚያረጋግጡ የምርጫ ጣቢያ አረጋጋጮች ሥልጠና ከዛሬ ጀምሮ መሰጠት መጀመሩን በመግለጫው ተመላክቷል።

ኢቢሲ

03/06/2026

ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን በአቡራሞ ወረዳ ቡልድግሉ ቀበሌ ከ24,500 ሄ/ር ኩታ-ገጠም ማሣ ላይ ያደረጉት የሜካናይዜሽን እርሻ ዝግጅት ጉብኝት!

‎በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝቡ ያለምንም ችግር በሰላማዊና በፍትሃዊ መንገድ ድምጹን ሰጥቷል፦ የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክርቤት‎**************‎‎(አሶሳ፣ ግንቦት 26/2018 ...
03/06/2026

‎በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝቡ ያለምንም ችግር በሰላማዊና በፍትሃዊ መንገድ ድምጹን ሰጥቷል፦ የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክርቤት
‎**************

‎(አሶሳ፣ ግንቦት 26/2018 ዓ.ም) የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ሕዝቡ ያለምንም ችግር በሰላማዊና በፍትሃዊ መንገድ ድምጹን እንዲሰጥ ያስቻለ መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክርቤት አስታወቀ።

‎የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክርቤት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በተመለከተ ለሚዲያ መግለጫ ሰጥቷል።

‎የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ እና የቤኒሻንጉል ህዝብ ነፃነት ንቅናቄ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ አብዱሰላም ሸንገል እንደገለጹት፣ የዘንድሮው የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከዝግጅት ጀምሮ የተሻለ ሂደት ያለው ነው።

‎የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክርቤት ከዝግጅት ጀምሮ ትኩረት ሰጥቶ የበኩሉን ድርሻ ሲወጣ እንደነበርም አንስተዋል።

‎እንደሀገርም ሆነ እንደክልል በተለያዩ ሁኔታዎች ውስጥ በመሆን የተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለምንም ችግር በሰላም መጠናቀቁ የሚያስደስት ነው ብለዋል።

‎ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ህብረተሰቡ ከማለዳ ጀምሮ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ ድምጹን በመስጠት ያሳየው ጽናት የሚደነቅ መሆኑን አንስተው፣ ሂደቱም ያለምንም ችግር በሰላማዊ መንገድ መጠናቀቁን ተናግረዋል።

‎በክልሉ ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ለተወጡ ለህብተተሰቡ፣ ለጸጥታ፣ ለፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ለሲቪክ ማኅበራት፣ ለምርጫ አስፈጻሚዎች ምስጋና አቅርበው፣ የምርጫው ሰላማዊነት የመተባበር ውጤት መሆኑን ገልጸዋል።

‎7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝቡ ተሳትፎ ጎልቶ የታየበት መሆኑን የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁሩ ገለጹ‎**********‎‎(አሶሳ፣ ግንቦት 26/2018 ዓ.ም) 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ አሳታፊነት...
03/06/2026

‎7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝቡ ተሳትፎ ጎልቶ የታየበት መሆኑን የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁሩ ገለጹ
‎**********

‎(አሶሳ፣ ግንቦት 26/2018 ዓ.ም) 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ አሳታፊነት እና አካታችነት ጎልቶ የታየበት ነው ሲሉ በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ትስስርና ሽግግር ዳይሬክተር ደስታ እጄታ (ዶ/ር) ብለዋለ።

‎በምርጫው የታየው የሕዝቡ ተሳትፎ ለሀገር መንግስት ግንባታ ያለው ድርሻ የጎላ እንደሆነም ገልጸዋል።

‎ከቅድመ ምርጫ እስከ ድህረ ምርጫ ያለው ጤናማ የፖለቲካ ውድድር የታየበት ነው ያሉት ምሁሩ፤ ዴሞክራሲ አስተዳደርን ለማስፈን እና አካታች የአስተዳደር ስርዓትን ለመዘርጋት መሰረት የጣለ እንደነበርም ዶ/ር ደስታ ተናግረዋል።

‎ተፎካካሪ ፓርቲዎች በመላው ሀገሪቱ በነፃነት ተንቀሳቅሰው የራሳቸውን ርዕዮተ ዓለም ማስተዋወቅ መቻላቸው የዳበረ የፖለቲካ ባህልን ያሳያል ብለዋል።

‎መራጩ ህዝብ ለቀጣይ "ይመራኛል፣ የሆነኛል" ብሎ የተመረጠውን የህዝቡን ድምጽ ማክበር እንደሚገባ ጠቁመው፣ የሚያሸንፈው ፓርቲም በቅድመ ምርጫ ለሕዝቡ የገባውን ቃል ለመፈጸም ከምንጊዜው በላይ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ ገልጸዋል።

‎የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ አሰጣጥ ሂደት ፍትሃዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተዓማኒነት ሆኖ መጠናቀቁ ተናግረው፣ ለዚህም የህዝቡ ሚና የጎላ መሆኑን አንስተዋል።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 23ኛ መደበኛ ስብሰባ ነገ ይካሄዳል***********6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ 23ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ግንቦት 27 ቀን 2...
03/06/2026

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 23ኛ መደበኛ ስብሰባ ነገ ይካሄዳል
***********

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ 23ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ያካሂዳል።

ምክር ቤቱ በነገው ስብሰባው በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ልማት ባንክ እንዲሁም በኢትዮጵያ እና በዓለም አቀፍ የልማት ማኅበር መካከል የተደረጉ የብድር ስምምነቶችን ለማጽደቅ የወጡ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

በሌላ በኩል ምክር ቤቱ በኢፌዴሪ መንግሥት እና በሴራሊዮን ሪፐብሊክ መንግሥት፤ በኢፌዴሪ መንግሥት እና በአንጎላ ሪፐብሊክ መንግሥት፤ በኢፌዴሪ መንግሥት እና በባንግላዲሽ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ መንግሥት፤ እንዲሁም በኢፌዴሪ መንግሥት እና በኢስዋቲኒ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት መካከል የተፈረመውን የሁለትዮሽ የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ረቂቅ አዋጁን የሚያጸድቅ ይሆናል።

በተጨማሪም ምክር ቤቱ በኢፌዴሪ መንግሥት እና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል የጋራ የባዮሎጂ ምርምር ማዕከል ለማቋቋም የተፈረመውን ስምምነት ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ረቂቅ አዋጁን እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል።

በተያያዘም በኢፌዴሪ መንግሥት እና በቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የዲፕሎማቲክ ወይም ኦፊሴላዊ የአገልግሎት ፓስፖርት ለያዙ ሰዎች ቪዛን ለማስቀረት የተፈረመ ስምምነት ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ረቂቅ አዋጁን ያጸድቃል።

በመጨረሻም ምክር ቤቱ የፌዴራል ታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅን፣ የግብርና ቢዝነስ ኩባንያ ረቂቅ አዋጅን፣ የምግብ ሥርዓትና ሥርዓተ ምግብ ረቂቅ አዋጅን፣ የኢትዮጵያ የካርበን ገበያ ረቂቅ አዋጅን እና የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች የሚመራ መሆኑን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

‎በምርት ዘመኑ በመኸር እርሻ የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት ርብርብ ማድረግ ይገባል፦ አቶ አሻድሊ ሀሰን‎*************‎‎(አሶሳ፣ግንቦት 26/2018 ዓ/ም) በክልሉ በ2018/19 የምርት...
03/06/2026

‎በምርት ዘመኑ በመኸር እርሻ የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት ርብርብ ማድረግ ይገባል፦ አቶ አሻድሊ ሀሰን
‎*************

‎(አሶሳ፣ግንቦት 26/2018 ዓ/ም) በክልሉ በ2018/19 የምርት ዘመን በመኸር እርሻ የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።

‎ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን በዛሬው ዕለት በአሶሳ ዞን አቡራሃሞ ወረዳ ቡልዲግሉ የገጠር ቀበሌ ከ24,500 ሄ/ር በላይ ኩታ-ገጠም ማሣ ላይ የተጀመረውን የመኸር እርሻ ዝግጅት ተመልክተዋል።

‎አቶ አሻድሊ ሀሰን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት፣ በተለያዩ ምክንያቶች ዘግይቶ የተጀመረውን የሜካናይዜሽን እርሻ ዝግጅት የበለጠ አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።

‎የሜካናይዜሽን እርሻን ጨምሮ የተለያዩ አማራጮችን በሙሉ በመጠቀም አንድም ማሣ ጦሙን እንዳያድር ለማድረግና በምርት ዘመኑ የተቀመጥውን ግብ ለማሳካት ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ርብርብ እንደሚደረግ ተናግረዋል።

Address

Asosa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ:

Share