የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ግብርናና መምሪያ

  • Home
  • Ethiopia
  • Asosa
  • የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ግብርናና መምሪያ

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ግብርናና መምሪያ የከተማዉ ህብረተሰብ የተፈጥሮ ሀብቱን፣የሰዉ ሃይሉንና ካፒታሉን በመጠቀም የከተማ ግብርናን ከግብ ማድረስ

በአሶሳ ከተማ የአንድ ጀምበር አረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ተካሄዴ፡፡ ***************************************ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም አሶሳ፡- የአሶሳ ከተማ አስተዳደር...
31/07/2025

በአሶሳ ከተማ የአንድ ጀምበር አረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ተካሄዴ፡፡
***************************************
ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም አሶሳ፡-

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር የአንድ ጀምበር አረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አካሄደ፡፡

እንደ ሀገር 700 ሚሊዮን እንደ ክልል 15 ሚሊዮን እንደ ከተማ አስተዳደር 250 ሺ ችግኞችን በአንድ ጀምበር ለመትከል በተያዘው ዕቅድ መሰረት በአምባ 8 እና ኢንዚ ተራራ ላይ የተለያዩ ሀገር በቀልና የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተተክለዋል፡፡

በችግኝ ተከላው የአሶሳ ከተማ ከንቲባና ም/ከንቲባ እንዲሁም የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ኃላፊ፣የየሴክተር መምሪያ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣የወረዳ 1 እና የወረዳ 2 ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች፣በጎ አድራጎት ወጣቶች፣የጸጥታ አካላት እንዲሁም የኦሎምፒክ ጂም ስፖርተኞች ተሳትፈዋል፡፡

በመትከል ማንሰራራት መሪ ቃል እየተከናወነ የሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዛሬ ከ8፡00 ሰዓት ጀምሮ በአጤጦ ሰልጋ የሚቀጥል በመሆኑ ሁሉም አካላት አሻራውን እንዲያሳርፍ መልዕት ተላልፏል፡፡

‎በከተማችን በአንድ ጀምበር 250,000 ሽህ ችግኞችን ለመትከል የሚያስችል ዝግጅት ተደርጓል‎****‎‎(አሶሳ፣ ሐምሌ 23/2017 ዓ.ም) በከተማ አስተዳዳራችን ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም በአ...
30/07/2025

‎በከተማችን በአንድ ጀምበር 250,000 ሽህ ችግኞችን ለመትከል የሚያስችል ዝግጅት ተደርጓል
‎****

‎(አሶሳ፣ ሐምሌ 23/2017 ዓ.ም) በከተማ አስተዳዳራችን ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም በአንድ ጀምበር 250,000 ሽህ ችግኞችን ለመትከል የሚያስችል ዝግጅት መጠናቀቁን የከተማ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

‎የከተማ ግብርና መምሪያ ወ/ሮ ዉቢት አድሱ በሰጡት መግለጫ፣ በከተማችን በተያዘው ክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 750,000 ሽህ ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።

‎በከተማችን የዘንድሮው የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ከተጀመረ ወዲህ እስካሁን ከ380,000 በላይ ለአካባቢ ጥበቃ እና ለኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መተከላቸውን ኃላፊዋ ገልጸዋል።

‎ነገ ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄደው የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በከተማ 250,000 ሽህ ችግኞች እንደሚተከሉ ተናግረዋል።

‎ለአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላው አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን የተናገሩት ወ/ሮ ውቢት ፣ የችግኝ መትከያ ቦታዎች የተዘጋጁ ሲሆን ችግኞችን የማጓጓዝ ሥራ እየተከናወነ ነው ብለዋል።

‎መላው የከተማችን ሕብረተሰብ ከማለዳው 12:00 ጀምሮ በአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላው ላይ በመሳተፍ አሻራውን እንዲያሳርፍም ወ/ሮ ውቢት ጥሪ አቅርበዋል።

‎ #የአሶሳ _ከተማ_ አስተዳደር _ ግብርና መምሪያ
‎***

የመምሪያችን የስራ ባልደረባ የሆነችው ወ/ሮ ፈንታ ፈለቀ መርጊያው በደረሰባት ድንገተኛ ህመም በአሶሳ ዳዋ_ሊዳ ክሊኒክና በኦዞን ክሊኒክ ህክምናዋን ስትከታተል ቆይታ ወደ በአዲስ አበባ በጳውሎ...
28/02/2025

የመምሪያችን የስራ ባልደረባ የሆነችው ወ/ሮ ፈንታ ፈለቀ መርጊያው በደረሰባት ድንገተኛ ህመም በአሶሳ ዳዋ_ሊዳ ክሊኒክና በኦዞን ክሊኒክ ህክምናዋን ስትከታተል ቆይታ ወደ በአዲስ አበባ በጳውሎስ ሆስፒታል ህክምናዋን እየተከታተለች ቆይታ በቀን_20/06/2017 ዓ.ም በተወለደች በ49 አመቷ ይህችን አለም በሞት ተለየች የቀብር ስነ_ስርአቷም ወዳጅ ዘመዶቿና ቤተሰቦቿ በተገኙበት ዛሬ በቀን_21/06/2017 ዓ.ም በኡራ ወረዳ አምባ አንድ ቀበሌ ቅ/አርሴማ ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል።

ወ/ሮ ፈንታ ፈለቀ መርጊያው የአንድ ወንድ ልጅ እና የሁለት ሴት ልጆች እናት ስትሆን እጅግ ሰው አክባሪ፣ ቅን፣ ታዛዢ ፣ ከሁሉ ጋር ተግባቢ ነበረች ፣ እሷን በቅርብ ለሚያውቋት፣ ለወዳጂ ዘመጆቿ እንዲሁም ለቤተሰቦቿ መፅናናትን እየተመኘው ነፍሷን ከደጋጎች ጎን እግዚአብሔር ያሳርፍልን።

በአሶሳ ከተማ አስ/ር ወረዳ 2 ቀበሌ 4 እየለማ ያለ የበጋ መስኖ ልማት።
27/02/2025

በአሶሳ ከተማ አስ/ር ወረዳ 2 ቀበሌ 4 እየለማ ያለ የበጋ መስኖ ልማት።

በኸልዋ አግሮ ኢንዱስትሪ የእንስሳት የተቀነባበረ መኖ ዋጋ ዝርዝር**** ቀን_19/06/2017 ዓ.ም # የወተት ላም መኖ....በኩንታል 3500 ብር # የበግ ማድለቢያ መኖ....በኩንታል 35...
27/02/2025

በኸልዋ አግሮ ኢንዱስትሪ የእንስሳት የተቀነባበረ መኖ ዋጋ ዝርዝር
**** ቀን_19/06/2017 ዓ.ም
# የወተት ላም መኖ....በኩንታል 3500 ብር
# የበግ ማድለቢያ መኖ....በኩንታል 3500 ብር
#የበሬ ማድለቢያ መኖ....በኩንታል 3500 ብር
******************
#የእንቁላል ጣይ ዶሮ መኖ....በኩንታል 4600 ብር
#የቄብ ዶሮ መኖ....በኩንታል 4600 ብር
#የጫጩት መኖ....በኩንታል 4700 ብር
መሆኑን እንገልፃለን::

ይምጡ ይጎብኙን!!!

አድራሻ:_ ኡራ ወረዳ አምባ አንድ ቀበሌ የማህበረሰብ አቀፍ ፕሮጀክት

የመምሪያችን የስራ ባልደረባ የሆነችው ወ/ሮ ብርቱካን  ፈለቀ በደረሰባት ድንገተኛ ህመም በአሶሳ ሆስፒታል ህክምናዋን ስትከታተል ቆይታ ወደ በአዲስ አበባ በጳውሎስ ሆስፒታል ህክምናዋን ስትታከ...
25/02/2025

የመምሪያችን የስራ ባልደረባ የሆነችው ወ/ሮ ብርቱካን ፈለቀ በደረሰባት ድንገተኛ ህመም በአሶሳ ሆስፒታል ህክምናዋን ስትከታተል ቆይታ ወደ በአዲስ አበባ በጳውሎስ ሆስፒታል ህክምናዋን ስትታከም ቆይታ ዛሬ እችን አለም በሞት ተለየች ።

ወ/ሮ ብርቱካን ፈለቀ የአንድ ወንድ ልጅ እናት ስትሆን እጅግ ሰው አክባሪ፣ ቅን፣ ታዛዢ ፣ ከሁሉ ጋር ተግባቢ ነበረች ፣ እሷን በቅርብ ለሚያውቋት፣ ለወዳጂ ዘመጆቿ እንዲሁም ለቤተሰቦቿ መፅናናትን እየተመኘው ነፍሷን ከደጋጎች ጎን እግዚአብሔር ያሳርፍልን።

የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት /የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ/  በአሶሳ ከተማ ላይ አመራሮች በተገኙበት ተጀመረ ፡፡*****(የካቲት 13/06/2017 ዓ/ም )የአሶሳ ከተማ አስ/ር ብልጽግና ፓርቲ ጽ/...
20/02/2025

የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት /የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ/ በአሶሳ ከተማ ላይ አመራሮች በተገኙበት ተጀመረ ፡፡
*****(የካቲት 13/06/2017 ዓ/ም )
የአሶሳ ከተማ አስ/ር ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሉቁማን ሂድር፣ የአሶሳ ከተማ አስ/ር፣ የወረዳ 2 እና የወረዳ 2 ቀበሌ 1 አመራሮች በተገኙበት የ2017 ዓ.ም የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት /የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ/ በአሶሳ ከተማ ወረዳ 2 ቀበሌ 1 ላይ በይፋ አስጀምረዋል ፡፡

በአሶሳ ከተማ ማረሚያ ጀርባ ሞዴል የሌማት ትሩፋት መንደር የመንገድ ከፈታና የውስጥ ለውስጥ ጥርጊያ  ዛሬ ሰርተናል።ቀን- 08/06/2017 ዓ.ም
15/02/2025

በአሶሳ ከተማ ማረሚያ ጀርባ ሞዴል የሌማት ትሩፋት መንደር የመንገድ ከፈታና የውስጥ ለውስጥ ጥርጊያ ዛሬ ሰርተናል።
ቀን- 08/06/2017 ዓ.ም

13/02/2025
የአሶሳ ከተማ አስ/ር ግብርና መምሪያ በ30 ቀናት በስምሪት የተሰሩ የግብርና ስራዎች ሪፖርት ግምገማ በማድረግ ለቀጣይ የስራ አቅጣጫ በማስቀመጥ ውይይቱ አጠናቀናል።የካቲት 03/06/2017 ዓ...
10/02/2025

የአሶሳ ከተማ አስ/ር ግብርና መምሪያ በ30 ቀናት በስምሪት የተሰሩ የግብርና ስራዎች ሪፖርት ግምገማ በማድረግ ለቀጣይ የስራ አቅጣጫ በማስቀመጥ ውይይቱ አጠናቀናል።

የካቲት 03/06/2017 ዓ.ም
አሶሳ፤

Address

Asosa

Telephone

+251577752961

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ግብርናና መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share