Benishangul people Libration Movement

Benishangul people Libration Movement Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Benishangul people Libration Movement, Political organisation, Asossa Town Adminstration, Stadium Highway, next to Hilal Mosque, on Asossa high school and preparatory junction, Asosa.

07/07/2024

ከቤህነን ማዕከላዊ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ
የተከበራችሁ የድርድታችን አባላት እና ደጋፊዎች
የተከበራችሁ መላው ሕዝባችን
ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ም በክልላችን የተካሄደው ድጋሜ እና ጠቅላላ ምርጫ የቤኒሻንጉል ህዝብ ነፃነት ንቅናቄ (ቤህነን) የተፈጠረዉ ውስጣዊ ችግሩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባልፈታበት ድርጅቱ እንደ ድርጅት ሙሉ ቁመና ይዞ ባልተገኘበት እና ዕጩ ተወዳዳሪዎች ታፍነው በታስሩበት የድርጅቱ ሊቀመንበር ጨምሮ ህዝባችን አምኖ የሰጧቸው ኃላፊነቶችና አደራ ወደ ግል ጥቅማቸው አዙሮ በመሸጥ ድርጅቱን አሳልፎ ለክልሉ መንግስት በሰጡ እና በሆድ ተገዝቶ ከክልሉ መንግስት ጋር በተጣበቁ አፈንጋጭ ግለሰቦች (አንጃ) እና ከክልሉ መንግስት የሚደርሱ ጫናዎች እንግልትና አስራት ባለበት እንዲሁም እንደ ድርጅት ምንም ዓይነት የይምረጡኝ ቅስቀሳ እና የተሟላ ዝግጅት ባልተደረገበት ድርጅቱን ለማዳን ሲባል የገባንበት ምርጫ ነው፡፡
ከምርጫው በፊት የድርጅቱ ሊቀመንበር እና ውስን ግብረ አበሮቹ የተላላኪነት ተልዕኮአቸውን ለመፈጸምና የተሰጣቸውን ሥልጣን ለማስጠበቅ የድርጅቱን መተዳደሪያ ደንብ በመተላለፍ ለክልሉ መንግስት ታማኝና አመቻች ተወዳዳሪ ለመሆን ከዚህ በፊት በ2013 ዓ.ም የፓርቲው ዕጩ ተወዳዳሪ የነበሩ ዕጩዎች በመሰረዝ ያለ ምንም የማዕከላዊ ኮሚቴ ዉሳኔ ከግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን ሌሎች ግለሰቦች እጩ ተወዳዳሪ አድርጎ በመመልመል ለምርጫው ለማቅረብ ሙከራ አድርጎ ነበር፡፡ ይህ ሙከራው ግን ግቡን ሳይመታ እንዲከሽፍና የቀረቡ ግለሰቦች በህጉ መሠረት ከምርጫ እንዲሰረዙ እና የ2013 ዓ.ም ዕጩዎች በውድድሩ እንዲቀጥሉ ቦርዱ መወሰኑ የሚታወስ ነዉ ፡፡ ይሁን እንጂ ይህ ተላላኪ አንጃ ከክልሉ መንግስት ጋር በመጣበቁ ምክንያት የክልሉ የፍትህ ተቋም ሊያግዘን ይችላል ብሎ በማሰብ የተከበረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሰጠውን ውሳኔ ለማሻር በክልሉ ላይ ክስ ቢመሰርትም ፍርድ ቤቱ የቀረበለትን ክስ መርምሮ ከምርጫ ሕግ ጋር በማገናዘብ የቀረበውን ጥያቄ ውድቅ በማድረግ አንጃው የሽንፈት ቅሌቱን መከናነቡ የሚናስታዉሰዉ ጉዳይ ነዉ ፡፡ በዚህ ረገድ ይህ ደካማና ተላላኪ ግለሰብ ለክልሉ መንግስት ታማኝ ተወዳዳሪ በመሆን እራሱ የሚወዳደርበትን የመንጌ ወረዳ ምርጫ ክልል ጨምሮ የኦዳ ቡልዲግሉ ወረዳ ምርጫ ክልል የይስሙላ ታዛቢዎች በመመልመልና በመመደብ የክልሉ መንግስት ብቻውን እንደፈለገ እንዲፈነጭ እንድሁም ማጭበርበርና ስርቆት እንዲፈጽም በማድረግ የህዝባችን ድምፅ አሳልፎ ለክልሉ መንግስት ሰጥቷል፡፡ በመሆኑ ቤህነን በዚህ አስቸጋሪ ሁኔታ ዉስጥ ሆነ በምርጫዉ ሲወዳደር በሶስቱም የወረዳ ምርጫ ክልሎች በአብዛኛዉ የምርጫ ጣቢያዎች ታዛቢዎቹ የታሰሩበትና የተባረሩበት በመሆኑ የክልሉ መንግስት ካድሬዎች ; አመራሮች እና ሚሊሽያዎች በፈጠሩት ከፍተኛ ጫናና ማስፈራራት መራጩ ሕዝብ በነፃነት የሚፈልገዉ አካል ወይም ፓርቲ ሊመርጥ አልቻለም በዚህ ሁኔታ የመንግስት አካላት በምርጫዉ እንደፈለጉ እንድሆኑ አንዳንድ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎች መንግስት ከማጭበርበር አልፎ የድምፅ መስጫ ወርቀት መራጩ ሕዝብ በተሰለፈበት ቦታ ላይ ተለጥፎ ሕዝቡ ተገዶ የብልፅግና ፓርቲ እንዲመርጥ ተባባሪ ሆኗል ፡፡ ስለዚህ በዚህ ዓይነት ሁኔታ በክልሉ የተካሄደዉ ምርጫ ፍተሐዊ ተዓማኒና ዴሞክራሲያዊ አይደለም ብሎ ቤህነን አቋሙን ይገልጻል ፡፡የተከበራችሁ የድርጅታችን አባላትና ደጋፊዎች እንዲሁም መላው ሕዝባችን ይህ ተላላኪ ግለሰብና አንጃ የሰሯቸው አስነዋሪ ተግባራት እና የክልሉ የብልፅግና መንግስት የሚፈጽማቸዉ ጫናዎች፣እስራትና እንግልት ሳትበገሩ በአሶሳ ወረዳ ምርጫ ክልል ለተወዳደርን የድርጅታችን ዕጩ ተወዳዳሪዎች ከ46ቱ የኢንዲጅነሱ የምርጫ ጣቢያዎች 75 በመቶ ዉጤት እንዲናገኝ አክብራችሁን በሰጣችሁን ድምፅ የብልፅግና ዕጩዎች ማሸነፋችን እኛ ብቻ ሳይሆን ብልፅግና እራሱ የሚመሰክረው ጉዳይ ሲሆን ከዚህ ሁሉ ጫናና ትንቅንቅ በአሶሳ ወረዳ ምርጫ ክልል ብልፅግና ሊያሸንፍ የቻለው በሌላ አካል ታዝሎና ታክኮ መሆኑ የምርጫ ዉጤቱ ያረጋገጠዉ ጉዳይ ነዉ ፡፡ ይህ ለእኛ ትልቅ የሞራል ስንቅ ሲሆን ሕዝባችን በዚህ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ለድርጅታችን ቤህነን ያለው ታማኝነትና ጥንካሬ ያስመሰከረበት ምርጫ በመሆኑ የበለጠ ሞራልና ብርታት የሚሰጠን ስለሆነ ለቀጣዩ ዝግጅታችን የደውል ምልክት ነው፡፡
የተከበራችሁ የድርጅታችን አባላትና ደጋፊዎች እንዲሁም መላው ሕዝባችን ማንኛውም አካል ወይም ቡድን የፈለገውን አካል ወይም ፓርቲ የመምረጥ ሕገ-መንግስታዊ መብቱ የተጠበቀ በመሆኑ ምንም ዓይነት የጥላቻ ስሜት ሳይኖራችሁ የመረጠንና ያልመረጠንን አካል ሁሉ ሙሉ ክብር ያለን መሆኑ አዉቃቹ ከወትሮው የበለጠ በትጋት፣በቁርጠኝነትና በታማኝነት ሥራችሁን አጠናክራችሁ ትቀጥሉ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ.ም አሶሳ

22/06/2024

ይድረስ ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እንዲሁም ለሚመለከተዉ ሁሉ
በኦሶሳ ዞን በአሶሳ፣ በመንጌ እና በኦዳ ቡልዲጊሉ ነገ ሰኔ 16 ቀን በሚሄደዉ ምርጫ
1ኛ. የክልሉ መንግሰት ድምጽ እንደማያገኛ በፈራባቸዉ አቁዳ እና ገንገን ምርጫ ጣቦያዎች በሀሰት የጸጥታ ችግር አለ በማለት ለምርጫ ቦርድ ባሳወቀዉ መሰረት ቦርዱ የተፎካካሪ ፓርቲዎች በጉዳዩ ላይ ሐሳብ እንዲሰጡበት እና በሌሎች ሶስተኛ ወገኖች የጸጥታ ችግር ስለመኖሩ አረጋግጦ ውሳኔ መስጠት ሲገባ ህዝቡ እና ፓርቲችንን ጨምሮ የትኛዉም ተፎካካሪ ፓርቲ ባላወቀበት ሁኔታ ገንገን ምርጫ ጣቢያ የጸጥታ ችግር አለ በማለት የምርጫ አስፈጻሚዎች ካለመመደባቸዉም በላይ ነገ በዚህ ጣቢያዉ በግለጽ ምርጫ እንደማይካሄድ ለማወቅ ችለናል፡፡
ያለ በቂ ምክንያት እና ፍጹም ግልጸኝነት በጎደለዉ መንገድ የክልሉ መንግስት በሐሰት ለቦርዱ የሰጠዉን ሀሰተኛ መረጃ መሰረት በማድረግ የተላለፈዉ ወሳኔ ፍጹም ፍትሃዊነት የጎደለዉ ስለሆነ በውሳኔዉ ላይ አስቸኳይ እርምት ተደርጎ ህዝቡ ነገ በምርጫዉ እንዲሳተፍ እንዲደረግ እንጠይቃለን፡፡
2ኛ. በገንገን የጸጥታ ችግር አለ ያለዉ የክልሉ መንግስት በኦዳ ቡልዲግሉ በሚደረገዉ ምርጫ ላይ ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ ሚሊሻ ልብስ የለበሱ ልዩ ሐይሎችን ወደ ቦታዉ ወስዶ በድንኳን በማስፍር በእጩዎቻችን እና በመራጩ ህዘብ ላይ ከፍተኛ ማስፈራራት ሽብር በመፍጠር ላይ ስለሆነ በወረዳዉ የሚካሄደዉ ምርጫ መራጩ ህዝብ ከተጽእኖ ነጻ በሆነ መንገድ ይመርጥ ዘንድ የሚመለከተዉ አካል ወደ ቦታዉ የፌደራል ፖሊስ አሊም የመከላከያ ሰራዊት እንዲልክ እና በክልሉ ምርጫ ለመታዘብ ፈቃድ የተሰጣችሁ የሲቪክ ማህበራትም ታዛቢዎች ወደ ስፍራዉ ትልኩ ዘንድ እንጠይቃለን፡፡
3ኛ. በ አሶሳ መጌለ እና አሶሳ ሆሃ የምርጫ ጣቢያ በተለይም በአሶሳ ከተማ ስታዲየም ሰፈር ያለ ምርጫ ጣቢያ በቀበሌ እና ወረዳ አማራሮች ተሰባስበዉበት የሚገኘን ከመሆኑም በላይ በከተማዉ ጤና ጫፍ በሚባል አካባቢ የተከበረዉ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን ለክልሉ መንግስት በጻፈዉ ደብዳቤ መሰረት በመደበኛ ፖሊስ አልያም በፌደራል ፖሊስ መጠበቅ ሲገባዉ አጋጅ ሐይል በሚባል ሀይል እየተጠበቀ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ከክልል እስከ ቀበሌ ያሉ የመንግስት አመራራችና እና ካደርዎች ከምርጫ ጣቢያዎች እንዲርቁ እና ጣቢያዎቹ በፌደራል ፖሊስ አንዲጠበቁ በቀጥታ ቦርዱ ለፌደራል ፖሊስ እንዲሰጥ እንጠይቃለን፡፡
4ኛ. በዚህ ምሽት በ አሶሳ መገሌ ምርጫ ጣቢያ ታዛቢ የሆኑት
አቶ ሐሊፋ አብዱልጀሊል በአቡራሞ ቀበሌ
አቶ ራህመተላ ሚነላ በአቡራሞ ቀበሌ
አቶ ሚነላህ እስማኤል በአቡራሞ ወረዳ ፖሊስ የታዛቢነት ባጃቸዉን ተነጥቀዉ ታስረዋለ፡፡ መርጫዉን ለመጀመር የቀሩት ሰዓታት 11 ሰዓታት ብቻ እንደመሆናቸዉ መጠን የሚመለከታቸዉ አካላት ለችግሩ እልባት እንዲሰጡ እና የፌደራል ፖሊስ አባላትም ወደ ስፍራዉ እንዲላኩ እንጠይቃለን፡፡

16/06/2024
ሰኔ 16 ቀን በኦሶሳ ፣ በኦዳ ቡልዲግሉ እና በመንጌ በሚከሄደዉ ምርጫ መምረጥ የሚችለዉ ማን ነዉ ?ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ም በኦሶሳ ፣ በኦዳ ቡልዲግሉ እና በመንጌ በሚደረገዉ ምርጫ መራጭ...
16/06/2024

ሰኔ 16 ቀን በኦሶሳ ፣ በኦዳ ቡልዲግሉ እና በመንጌ በሚከሄደዉ ምርጫ መምረጥ የሚችለዉ ማን ነዉ ?

ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ም በኦሶሳ ፣ በኦዳ ቡልዲግሉ እና በመንጌ በሚደረገዉ ምርጫ መራጭ ሆኖ መቅረብ እና መምረጥ የሚችለዉ፤ በ 2013 ዓ.ም በነበረዉ ምርጫ በመራጭነት ተመዘግቦ የነበረ መራጭ ብቻ ሲሆን ፡፡ ይህ መራጭ በምርጫዉ ዕለት መታወቂያዉን ይዞ በመቅረብ ስሙ ከቀድሞዉ መዝገብ ጋር ተገናዝቦ መምረጥ ይችላል፡፡ ሰሞኑን በምርጫ አስፈጻሚ አካላት እየተሰጠ ያለዉ የመራጮች መዝገብ ተራ ቁጥር ማሳወቂያ ካርድ የአንድን መራጭ ተራ ቁጥር ለማሳወቅ እንጂ የመምረጫ ካርድ አይደለም፡፡
ስለ ድምጽ መስጫ ወረቀት
በዚህ ምርጫ ለመምረጥ ሲሄዱ 2 የድምጽ መስጫ ወረቀቶች ይሰጦታል
1ኛዉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የድምጽ መስጫ ወረቀት ሲሆን
2ኛዉ ደግሞ የክልል ምክር ቤት ተወካይ የድምጽ መስጫ ወረቀት ነዉ
አንድ መራጭ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የድምጽ መስጫ ወረቀት ላይ ከተመለከቱት የተለያዩ ዕጩ ተወዳዳሪዎች ውስጥ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አንድ እጩ ተወዳዳሪ ብቻ የመምረጥ መብት ያለዉ ሲሆን ለክልል ምክር ቤት ደግሞ በወረዳዉ ምርጫ ክልል ኮታ ልክ የመምረጥ መብት ይኖረዋል
ለምሳሌ ፡
የአሶሳ ምርጫ ክልል ኮታ 6 ነዉ፡፡
ስለዚህ አንድ መራጭ በክልል ምክር ቤት የድምጽ መስጫ ወረቀት ላይ
ከተዘረዘሩት በርካታ እጩ ተወዳዳሪዎች መካከል መምረጥ የሚችለዉ 6ቱን ብቻ ነዉ
የቡልዲግሉ ምርጫ ክልል ኮታ በተመሳሳይ 6 ነዉ
ስለሆነም አንድ መራጭ በክልል ምክር ቤት የድምጽ መስጫ ወረቀት ላይ
ከተዘረዘሩት በርካታ እጩ ተወዳዳሪዎች መካከል መምረጥ የሚችለዉ 6ቱን ብቻ ነዉ
የመንጌ ምርጫ ክልል ኮታ 6 ነዉ፡፡
ስለሆነም አንድ መራጭ በክልል ምክር ቤት የድምጽ መስጫ ወረቀት ላይ
ከተዘረዘሩት በርካታ እጩ ተወዳዳሪዎች መካከል መምረጥ የሚችለዉ 6ቱን ብቻ ነዉ
ድምጽ እንዴት ይሰጣል ?
የድምጽ መስጫ ወረቀቱ ከታች በምስል እንደሚታየዉ ተራ ቁጥር በመቀጠል የተመራጩን ፎቶ፣ቀጥሎ የፓርቲው አርማ ከዚያም የድምጽ መስጫ አራት መዓዘን ሳጥን በመቀጠል የተመራጭ እጩውን ስም የያዘ ነዉ፡፡ ስለሆነም መራጩ ለመምረጥ ማድረግ ያለበት ሊመርጠዉ በፈለገዉ ተመራጭ አጠገብ ባለዉ አራት ማዕዘን ውስጥ የ X ወይም የ ✓ ምልክት ወይም ደግሞ የጣት አሻራ በማድረግ መምረጥ ይቻላል ፡፡
ቤህነንን ምረጡ
ምልክታችን መጨባበጥ ነዉ

15/06/2024

عيد مبارك تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال كل عم وأنتم بخير اللهم امين
💫እንኳን ለ1445ኛው ዓ.ሂ የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡ 🌙በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብና የደስታ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን!💫

10/06/2024

ግልጽ ፣ ገለልተኛ እና ከተጽእኖ ነጻ የሚሉ መርሆዎች ዋነኛ የምርጫ መርሆዎች የአንድ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ መርሆዎች መሆናቸዉ ይታወቃል፡፡
የፊታችን ሰኔ 16 ቀን በክልላችን በአሶሳ ፣ በመንጌ እና በኦዳ ቡልዲግሉ ወረዳዎች የሚደረገዉ ምርጫ፡ እጩዎች እንደ አዲሲ የማይመዘገቡበት እና በ2013 ዓ.ም የተቋረጠዉን ምርጫ ለማኬድ በ 2013 ዓ.ም ለመምረጥ የተመዘገቡ መራጮች ብቻ በምርጫ መዝገቡ መሰረት የሚመርጡበት ምርጫ እንደሆነ ይታወቃል፡፡
ይሁን እንጂ
1ኛ. በነዚህ ወረዳዎች መራጩ ህዝብ ቀርቦ የመራጮች መዝገብ ተራ ቁጥር ማሳወቂያ ካርድ መውሰድ ያለበት ስለመሆኑ በአሶሳ ከተማም ሆነ በሌሎች ወረዳዎች መራጩ ህዝብ እንዲያወቅ ምንም አይነት ቅስቀሳ ሳይደረግ ግልጽ ባልሆነ መንገድ ካርድ እየተሰጠ መሆኑን
2ኛ. ካርዱ እየተሰጠ ያለዉ ከ 2013 ዓ.ም የመራጮች መዝገብ በቀጥታ እየታየ እና እየተመሳከረ የፓርቲ ተወካዮች ባሉበት ካርዱ መሰጠት ሲገባዉ፡ ከመራጮች መዝገብ በታይፕ ተገልብጦ የመጣ ዝርዝር ነዉ በማለት፡ ከዚህ ከማይታወቅ ወረቀት ስም እየታየ ካርድ እየታደለ ያለ እና በ 2013 ዓ.ም የተመዘገቡ የፓርቲያችን ደጋፊ መራጮች ካርዱን ለመውሰድ ሲሄዱ ስማችሁ የለም እየተባሉ እየተመለሱ መሆኑን
3ኛ. በ 2013 ዓ.ም የመራጮች ምዝገባ በበርካታ ቀበሌዎች እና ጣቢዎች የተደረገ መሆኑ እንደመሆኑ መጠን በሁሉም ጣቢያዎች ለህዝቡ ጥሪ ተደርጎ ካርዱን ማደል ሲገባ፡ እየታደለ ያለዉ በውስን ቀበሌዎች ብቻ መሆኑን እና የምርጫ አስታሚነት ማስረጃ ባልያዙ ሰዎች እየተከናወነ ያለ መሆኑን ለመገንዘብ ችለናል፡፡
የዚህ አይነቱ ግልጸነት የጎደለዉ አሰራር ተገቢነት የሌለዉ ከመሆኑም በላይ ዝርዝር እየታየ ካርድ እየተሰጠ ያለዉ በቀጥታ ከባህር መዝገቡ ሳይሆን ከመዝገቡ በታይፕ የተገለበጠ ነዉ በሚል በወረቀት ከተያዘ ዝርዝር መሆኑ ግልጸኝነትን ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ አሰራር ስለሆነ የሚመለከታቸዉ አካላት ጉዳዩን በመረዳት አስቸኳይ ማስተካከያ እንዲደረግ እና በግለጽ መራጩ ህዝብ ካርድ እየታደለ ስለመሆኑ እና ካረድ መውሰድ ያለበት ስለመሆኑ እንዲያወቅ ቅስቀሳ እንዲደረግ እንጠይቃለን፡፡

https://www.facebook.com/100066827943709/posts/791345549769703/?mibextid=Nif5oz
06/06/2024

https://www.facebook.com/100066827943709/posts/791345549769703/?mibextid=Nif5oz

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛዉ ዙር ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ በሚካሄድባቸዉ የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር፣ ሶማሌ እና ማእከላዊ ኢትዮጵያ በሚገኙ ምርጫ ክልሎች ምርጫ ለማከናወን የወጣ የተሻሻለ የምርጫ አፈፃፀም የጊዜ ሰሌዳ

06/06/2024

Address

Asossa Town Adminstration, Stadium Highway, Next To Hilal Mosque, On Asossa High School And Preparatory Junction
Asosa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Benishangul people Libration Movement posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share