በቤ/ጉ/ክ/መ በአሶሳ ዞን የአቡራሞ ወረዳ ግብርናና ተፈጥሮ ሀብት ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Asosa
  • በቤ/ጉ/ክ/መ በአሶሳ ዞን የአቡራሞ ወረዳ ግብርናና ተፈጥሮ ሀብት ጽ/ቤት

በቤ/ጉ/ክ/መ በአሶሳ ዞን የአቡራሞ ወረዳ ግብርናና ተፈጥሮ ሀብት ጽ/ቤት This page is owned by Assosa Woreda Agriculture & Natural Resource office page.

The main objective of the page is to disclose information in relation to agricultural and natural resource activities.

በቤ/ጉ/ክ/መ በአሶሳ ዞን አቡራሞ ወረዳ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ፕሮጀክት(LFSDP) ድጋፍ ጋምባሽሪ ቀበሌ በዶሮ ምርት የተደራጁ ማህበራት በዛሬው እለት የአርሶ አደር መስክ ትምህርት(FFS)...
22/02/2026

በቤ/ጉ/ክ/መ በአሶሳ ዞን አቡራሞ ወረዳ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ፕሮጀክት(LFSDP) ድጋፍ ጋምባሽሪ ቀበሌ በዶሮ ምርት የተደራጁ ማህበራት በዛሬው እለት የአርሶ አደር መስክ ትምህርት(FFS) መስክ በዓል አከበሩ።

ከፌደራራል ብሄራዊ የእንስሳትና ዓሳ ሀብት ፕሮጀክት አስተባባሪ ዶ/ር ቶማስ ቸርነት እንዲሁም ከግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ኤክስፐርት አቶ እንደሻው፣የክልሉ ግብርና ቢሮ ም/ሀላፊ አቶ አብደልከሪም እንዲሁም የአቡራሞ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ባበክር ሃሚድ እና ካቢኒያቸው እንዲሁም የክልል ግብርና ቢሮ ባለሙያዎች፣የወረዳ ግብርና ባለሙያዎች፣የልማት ጣቢያ ባለሙያዎች እና የቀበሌው ማህበረሰብ በተገኙበት የመስክ በዓሉ በደማቅ ሁኔታ ተከብራሯል።

FFS( የአርሶ አደር መስክት ትምህርት) አርሶ አደሩ ከባለሙያ ጠባቂነት ተላቆ በራሱ ለውጥ የሚያመጣበት ፕሮግራም መሆኑን በእንግዶች የተገለጸ ሲሆን አባላቱም ትምህርቱን በአግባቡ በመከታተል ለምረቃ እንዲበቁ የወረዳው አስተዳዳረለ አቶ ባበክር አጽንኦት ሰተውበታል።
FFS, "School without wall" በየሳምንቱ ይቀጥላል.......

የካቲት 16/06/2018 ዓ.ም
አቡራሞ፤

 በአቡራሞ ወረዳ የግብርና ቴክኖሎጂን  በማስፋት የግብርና ምርትና ማርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ እየተሰራ ይገኛል፡፡ በክልላችን ብሎም በወረዳችን የግብርና የሜካናይዜሽን ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀ...
10/02/2026



በአቡራሞ ወረዳ የግብርና ቴክኖሎጂን በማስፋት የግብርና ምርትና ማርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ እየተሰራ ይገኛል፡፡

በክልላችን ብሎም በወረዳችን የግብርና የሜካናይዜሽን ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ከጊዜ ወደ ጊዜ የተሻለ ውጤት እየታየበት ይገኛል፡፡

በወረዳችን የግብርና ሜካናይዜሽን ስራ የግብርና ሴክተሩን ከማዘመን ባሻገር ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ እና የስራ እድሎችን በመፍጠር ከፍተኛ አስተዋፅዖ እያበረከተ ይገኛል፡፡

#የዛሬ ውሏችን በተለያዩ የበቆሎ አውድማዎች ላይ ጉብኝታችን እንካችሁ ብለናል!!!

የካቲት 03/06/2018 ዓ.ም
አቡራሞ፤

የአቡራሞ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት  የአርሶ አደሩን የፋይናሻል አቅርቦት ችግር መፍታት የሚያስችል  የብድር ስምምነት ፊርማ ከኢትዮጲያ ንግድ ባንክ ጋር ተፈራረመ፤********************...
24/01/2026

የአቡራሞ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት የአርሶ አደሩን የፋይናሻል አቅርቦት ችግር መፍታት የሚያስችል የብድር ስምምነት ፊርማ ከኢትዮጲያ ንግድ ባንክ ጋር ተፈራረመ፤
************************************************************************************
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዙምባራ ቅርንጫፍ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ግዛቸው ፈንቴ እንዲሁም የዳቡስ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ጋር የተፈራረምን ሲሆን አቶ ግዛቸው ፈንቴ ንግድ ባንኩ እንደ ሃገር ለ1ሚሊየን አርሶ አደሮች ብድር ለማቅረብ አቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል። የብድር ስምምነቱ የአነስተኛ ገበሬዎችን የብድር አቅርቦት ችግር በመቅረፍ ትልቅ መፍትሄ ነው ብለዋል።

በግልም ሆነ በማህበር ተደራጅተው ለሚመጡ አርሶ አደሮች ባንኩ 30% በማስቆጠብ እስከ 10 ሚሊየን ብር ግምት ያለው የብድር አቅርቦትና በ14.5% አነስተኛ ወለድ አርሶ አደሩን የብድር ተጠቃሚ ለማድረግ ከወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ጋር የብድር ስምምነት ተፈራርመናል ሲሉ ተናግረዋል።

የብድር መመለሻ ጊዜውም ከአንድ ዓመት እስከ አምስት ዓመት መሆኑን የባንኩ ሥራ አስኪያጅ አስረድተዋል።

የአቡራሞ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አታላይ ደረጀ በበኩላቸው ለበርካታ አመታት አርሶ አደሩ ማልማትና መለወጥ እንዳይችል የፋይናንሻል ችግሮ ማነቆ ሁኖበት መቆየቱን አስታውሰው ዛሬ ላይ የተደረገው የብድር ስምምነት የፋይናሻል አቅርቦት ችግሩን በመቅረፍ ፋይዳው ላቅ ያለ ነው ብለዋል።

አቶ አታላይ አያይዘውም ይህ የብድር ስምምነት አርሶ አደሩ ግብርናውን በማዘመን ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ለግብርና ግብዓት አቅርቦት፣ዘመናዊ ሜካናዜሽን ትግበራ፣ የገበያ ትስስር ለመፍጠር ፣ በብድር አቅርቦት እና ቴክኖሎጂ መር የግብርና ስርዓት ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑ ገልፀዋል።

አርሶ አደሩ የብድር ተጠቃሚ እንዲሆን ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት እስከ ታች ቀበሌና ጎጥ ወርዶ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ መሥራት ከሁሉም ሰው የሚጠበቅ ተግባር ነው ሲሉ የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊው መልዕክት አስተላልፈዋል።

በአሶሳ ዞን አቡራሞ ወረዳ  የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ተጀመረ፤********************************************( አሶሳ፣ ታህሳስ 27/2018) ወረዳዊ የ2018 የአፈርና...
06/01/2026

በአሶሳ ዞን አቡራሞ ወረዳ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ተጀመረ፤
********************************************
( አሶሳ፣ ታህሳስ 27/2018) ወረዳዊ የ2018 የአፈርና ውኃ ጥበቃ ስራ በመገሌ 34 ቀበሌ በይፋ ተጀምሯል፣

በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የዞንና የወረዳ አመራሮችና የቀበሌው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

የአቡራሞ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ባበክር ሃሚድ በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት፦ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ስራ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል።

ላለፉ ዓመታት በወረዳ የተከናወኑ የተፈጥሮ ሀብትጥበቃ ሥራዎች በርካታ ጥቅሞች ማስገኘታቸውን ገልጸዋል።

ስራው ቀጣይ በሁሉም ቀበሌዎች ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት አቶ ባበክር፣ ህብረተሰቡን የሚሰጠውን ጠቀሜታ በመገንዘብ በንቂስ ወጥቶ እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።

የአቡራሞ ወረዳ ግብርናና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አታላይ ደረጀ በበኩላቸው፦ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የተፈጥሮ ሐብት ጥበቃ ሥራዎች የተራቆቱ መሬቶችን መልሰው እንዲያገግሙ በማድረግ በተሰራው ስራ ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ማስቻሉን ተናግረዋል።

በተያዘው 2018 ከ5 ሺህ 5 መቶ 14 ሄክታር በላይ መሬት በ53 ንዑስ ተፋሰሶች የአፈርና ውኃ ዕቀባ ሥራ ለማከናወን ታቅዶ ዛሬ መጀመሩን ገልፀዋል።

በዚህም በወረዳው ወጣቱን ጨምሮ በርካታ የሕብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሳተፉ አቶ አታላይ መጠቆማቸውን ከወረዳው ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

  በ2017/18 ዓ.ም የምርት ዘመን  #በ69.5 ሄክታር መሬት ላይ እየለማ   ዘር ብዜት አሁናዊ ቁመና በከፊል፤
29/12/2025

በ2017/18 ዓ.ም የምርት ዘመን #በ69.5 ሄክታር መሬት ላይ እየለማ ዘር ብዜት አሁናዊ ቁመና በከፊል፤

የአቡራሞ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ባበክር ሀሚድ የ2018 ዓ.ም የበጀት አመት መደበኛ የበጋ መስኖ ልማት ሥራዎችን ጎበኙ፤******************************************...
11/11/2025

የአቡራሞ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ባበክር ሀሚድ የ2018 ዓ.ም የበጀት አመት መደበኛ የበጋ መስኖ ልማት ሥራዎችን ጎበኙ፤
******************************************
(አቡራሞ፣ ጥቅምት 02/2018 ዓ.ም) የአቡራሞ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ባበክር ሀሚድ የ2018 ዓ.ም የበጀት አመት በተለያዩ ቀበሌዎች እየለሙ ያሉ መደበኛ የበጋ መስኖ ልማት ሥራዎችን ጎበኙ፣

አቶ ባበክር ሀሚድ በጉብኝቱ ወቅት አንዳሉት አቡራሞ ወረዳ በተያዘው የበጋ ወቅት በመሥኖ እየተከናወኑ የሚገኙ የመደበኛ የበጋ መስኖ ሥራ ገበያ ከማረጋጋት ባለፈ ለኢኮኖሚው ዕድገት የጀርባ አጥንት በመሆኑ በወረዳው በመኸር ወቅት ከተከናወነው የግብርና ሥራ ባሻገር በመደበኛ የመሥኖ ልማት ስራ ላይ ኩታ ገጠምን መሰረት በማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ አየተሠራ ነው ብለዋል።

በወረዳው በግብርናው ዘርፍ በየዓመቱ ተጨባጭ ዕድገት እየተመዘገበ መሆኑን የጠቀሱት ዋና አስተዳዳሪው አርሶ አደሩ ከመኸር በተጨማሪ የውኃ አማራጮችን በመጠቀም በመሥኖ ልማት እያደረጉ ያለው ተሣትፎ አበረታች ነው ብለዋል።

በመሥኖ ልማት እየተገኘ ያለው ምርት የኑሮ ውድነቱን ለመቀነስ ዓይነተኛ ሚና አየተጫወተ ስለመሆኑም ጠቁመው ለአብነትም በወረዳችን አየተመረተ ያለው የሽንኩርት፣የቲማቲም፣የጥቅል ጎመን ምርት ገበያን በማረጋጋት ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል።

ወረዳው ለመኸርም ይሁን ለመስኖ እርሻ ሥራ አመቺ ነው ያሉት አቶ ባበክር፣ በግብርናው ዘርፍ በርካታ ሞዴል አርሶ-አደሮችአየተፈጠሩ መምጣቸውንም ገልጸዋል።

የወረዳው አመራርም ይሁን ባለሙያ እንዲሁም አርሶ አደሮች ግብርናውን ለማዘመን እያደረጉት ያለውን ጥረት አጠናክረው እንደሚቀጥሉም ጠቅሰዋል።

የአቡራሞ ወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አታላይ ደረጀ እንደገለፁት በወረዳው ለእርሻ ምቹ መሬቶች እስካሉን ድረስ በዘንድሮው የመኸር ወቅትም ሆነ አሁን በመደበኛ መስኖ የተሻለ አፈጻጸም መኖሩን ጠቅሰው በወረዳው ሁሉንም የውኃ አማራጮች በመጠቀም መደበኛ የመስኖ ሥራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል ብለዋል።

አቶ አታላይ ደረጄ፣ አክለውም በወረዳው በተያዘው የበጋ ወቅት ከታቀደው 9 ሺህ 165 ሄክታር ውስጥ እስካሁን 3 ሺህ 404 ሄክታር መሬት በመደበኛ መስኖ መልማቱን ተናግረዋል።

በአቡራሞ ወረዳ ከተረጅነት ለመላቀቅ ከወረዳ እስከ ቀበሌ በመኸር እርሻ በሰብል የተሸፈኑ ማሳዎች ጥሩ ቁመና ላይ እንዳሉና የተሻለ ምርት እንደሚሰጡ  የአቡራሞ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ባበክ...
10/11/2025

በአቡራሞ ወረዳ ከተረጅነት ለመላቀቅ ከወረዳ እስከ ቀበሌ በመኸር እርሻ በሰብል የተሸፈኑ ማሳዎች ጥሩ ቁመና ላይ እንዳሉና የተሻለ ምርት እንደሚሰጡ የአቡራሞ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ባበክር ሀሚድ ገለፁ፣
************************************************************************************
(ጥቅምት 01/03/2018 ዓ.ም አቡራሞ)በምግብ ራስን በመቻል የሀገር ሉዓላዊነትን ማስከበር በሚደረገው ጥረት በወረዳው ባሉ ቀበሌዎች በዘንድሮው የመኸር እርሻ የተሰሩ ስራዎችን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ባበክር ሀሚድ፣የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊዎችና ቡድን መሪዎች የመስክ ምልከታ አድርገዋል።

የወረዳው ዋና አሰተዳዳሪ አቶ ባበክር ሀሚድ በመስክ ምልከታው ወቅት እንዳሉት እንደ ሀገር ከተረጅነት ለመላቀቅ እንደ ወረዳ የተሰጠንን ተልዕኦ ትኩረት ተሰጥቶ በሁሉም ቀበሌዎች እንዲተገበር በተደረገው ርብርብ የተሻለ ስራ መሰራቱን ገልፀው በወረዳው በ2018 ዓ.ም የበጀት አመትም በወረዳ 25 ሄክታር በቀበሌ ደረጃ 137 ሄክታር በድምሩ 162 ሄክታር በተለያዩ የሰብል አይነቶች በዘር መሸፈኑን ገልፀው ከዚህም 2,500 ኩንታል ምርት ይጠበቃል ብለዋል፡፡

የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አታላይ ደረጀ በበኩላቸው በተያዘው የምርት ዘመን የሁሉም ቀበሌ የማህበረሰብ ክፍሎች ቀድመን ግንዛቤ በመፍጠር በምግብ ራስን የመቻል ሀገራዊ ጉዞ በወረዳው በስኬት የቀጠለ ሲሆን በዚህ ዙሪያ በወረዳው በሁሉም ቀበሌዎች ከተረጅነት ለመላቀቅ እየተሰሩ ያሉ የእርሻ ስራዎች የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ እኳያ እጅግ ወሳኝ ስራዎች እየተሰሩ ናቸው ብለዋል።

በአሶሳ ዞን አቡራሞ ወረዳ አምባ14 ቀበሌ በአ/አደር ማሰልጠኛ ማዕከልትና በስርዓተ-ምግብ ተኮር ግብርና(NSA) Model Village ፕሮግራም ተሳታፊ አርሶ አደሮች የተተገበሩ የአትክልትና ...
28/10/2025

በአሶሳ ዞን አቡራሞ ወረዳ አምባ14 ቀበሌ በአ/አደር ማሰልጠኛ ማዕከልትና በስርዓተ-ምግብ ተኮር ግብርና(NSA) Model Village ፕሮግራም ተሳታፊ አርሶ አደሮች የተተገበሩ የአትክልትና ፍራፍሬ ማሳዎች ላይ የአርሶ/አደሮች የመስክ በዓል ተከበረ
******************************************
(ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም አቡራሞ)በአሶሳ ዞን አቡራሞ ወረዳ አምባ14 ቀበሌ በአ/አደር ማ/ማዕከላትና የክልሉ ቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት(LLRP) ከክልሉ እንዲሁም ከወረዳው ግብርና ጋር በመተባበር በስርዓተ-ምግብ Model Village ፕሮግራም ተሳታፊ አ/ደሮች የተተገበሩ የአትክልትና ፍራፍሬ ማሳዎች ላይ የአርሶ/አደሮች የመስክ በዓል ተከብሯል።

በመስክ ምልከታው የአቡራሞ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት የተለያዩ የስራ ዘርፎች ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም የል/ጣቢያ ሰራተኞችን ጨምሮ የቀበሌው አርሶ/ከፊል አርብቶ አደሮች ተሳትፈዋል።

በእለቱ በተካሄደው የመስክ ምልከታ ቀደም ሲል በቀበሌው ተከስቶ በነበረው የተፈጥሮ አደጋ ምክንያት የወደሙ ሰብሎችን በአንፃራዊ መልኩም ቢሆን ቀድመው በሚደርሱ (Cash Crop,s) እንዲሁም በተለያዩ የአትክልት ዘር ዓይነቶች ለመተካት አርሶ/አደሮች ያደረጉትን ጥረት ለመመልከት ተችሏል።

በጉብኝቱ ወቅት ሞዴል አርሶ/አደር ወ/ሮ አስረበብ ሰጠ እንደገለፁት ከዚህ በፊት በተከሰተው የተፈጥሮ አደጋ ምክንያት የእርሳቸውን ጨምሮ አጠቃላይ በቀበሌው የሚገኙ አርሶ/አደሮች ሰብሎቻቸው መጎዳታቸው በተለይም በሰብል ዝርያዎች ላይ የምርት መቀነስ ሊያጋጥም እንደሚችል ጠቅሰው ነገር ግን የግብርና ባለሙያዎችን ምክረ ሀሳብ ተግባራዊ በማድረግ የተለያዩ የአትክልትና ፍራፍሬ ሰብሎችን በጓሮአችን እንዲሁም የበጋ መስኖን በመጠቀም በዘርፉ አዋጭ የሆኑ የስራ መስኮች ላይ በመሰማራት የደረሰውን የተፈጥሮ አደጋ የሚያካክስ ስራ ላይ መሰማራት ይኖርብናል ሲሉ ሀሳባቸውን ገልፀዋል።

ወ/ሮ አስረበብ አባስ ከመደበኛ የሰብል ምርት ማምረት ጎን ለጎን ግብርና ስራዎች በተጨማሪ በተለይም በስርዓተ-ምግብ ተኮር ግብርና Model Village ፕሮግራም የተደረገላቸውን የተለያዩ የአትክልትና ፍራፍሬ ዘሮች ድጋፍ ወደመሬት በማውረድ ጓሮአቸው ላይ በሰሩት የተቀናጀ የግብርና ስር ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን የተመጣጠነ ምግብ ከመመገብ አልፈው ምርቶችን ወደ ገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያቸውን በማሻሻል ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል።

በመጨረሻምአርሶ አደሮቹ አና አጠቃላይ የጉብኝቱ ተሳታፊዎች የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ባለድርሻ አካላት በመካከላቸው ተገኝተው በመሳተፋቸውና ለሰጧቸው ሙያዊ አስተያየቶችና ምክሮች ሁሉ ምስጋና አቅርበው በቀጣይ በሚያከናውኗቸው ማናቸውም የግብርና የልማት ስራዎች እንደተለመደው ሁሉ ወረዳው ከጎናቸው እንደሚሰለፍ ያላቸውን ፅኑ እምነት ገልፀው የዕለቱ የመስክ ምልከታ ተጠናቅቋል።

28/10/2025
በአሶሳ ዞን በአቡራሞ ወረዳ የአቡራሞ ቀበሌ ፂዎ ጎጥ ማህበረሰብ ክፍሎች የአርሶ አደሮች የመስክ በዓል ተከበረ፤**************************************************...
23/10/2025

በአሶሳ ዞን በአቡራሞ ወረዳ የአቡራሞ ቀበሌ ፂዎ ጎጥ ማህበረሰብ ክፍሎች የአርሶ አደሮች የመስክ በዓል ተከበረ፤
************************************************************************************
(ጥቅምት13/02/2018 ዓ.ም አቡራሞ) በአቡራሞ ወረዳ የአቡራሞ ቀበሌ ፂዎ ጎጥ ማህበረሰብ ክፍሎች በሞዴል አርሶ አደሮች እየተሰሩ ያሉ የቬርሚ ኮምፖስት ስራዎችን እንዲሁም በLLRP ፕሮጄክት ድጋፍ በአርሶ/ከፊል አርብቶ አደር የመስክ ትምህርት ቤት A.P.F.S (Agro Pastoral Field School) ፕሮግራም የተተገበሩ የተለያዩ ማሳዎችንና ሰርቶ ማሳያዎችን ማዕከል ያደረገ የመስክ ጉብኝት ተካሄዷል።

በመስክ ምልከታው የአቡራሞ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት የተለያዩ የስራ ዘርፎች ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም የል/ጣቢያ ሰራተኞችን ጨምሮ የቀበሌው አርሶ/ከፊል አርብቶ አደሮች ተሳትፈዋል።

በእለቱ በተካሄደው የመስክ ምልከታ ጳጉሜ 1/2017 ዓ.ም በቀበሌው ተከስቶ በነበረው የተፈጥሮ አደጋ ምክንያት የወደሙ ሰብሎችን በአንፃራዊ መልኩም ቢሆን ቀድመው በሚደርሱ (Cash Crop,s) እንዲሁም በተለያዩ የአትክልት ዘር ዓይነቶች ለመተካት አርሶ/ከፊል አርብቶ አደሮች ያደረጉትን ጥረት ለመመልከት ተችሏል።

በጉብኝቱ ወቅት ሞዴል አርሶ አደር አቶ አባስ ሰሌማን እንደገለፁት ከዚህ በፊት ጳጉሜ 1/2017 ዓ.ም በተከሰተው የተፈጥሮ አደጋ ምክንያት የእርሳቸውን ጨምሮ አጠቃላይ በቀበሌው የሚገኙ አርሶ/ከፊል አርብቶ አደሮች ሰብሎቻቸው መውደሙ እንዳሳዘናቸው ጠቅሰው ነገር ግን ቀጣይ የግብርና ባለሙያዎችን ምክረ ሀሳብ ተግባራዊ በማድረግ በዘርፉ አዋጭ የሆኑ የስራ መስኮች ላይ በመሰማራት የደረሰውን የተፈጥሮ አደጋ የሚያካክስ ስራ ላይ መሰማራት ይኖርብናል ሲሉ ሀሳባቸውን ገልፀዋል።

አቶ አባስ ከመደበኛ የግብርና ስራዎች በተጨማሪ በተለይም በቬርሚ ኮምፖስት ዝግጅት ስራ ተሰማርተው አሁን ላይ ከ 30ኩ/ል ቬርሚ ኮምፖስት ብር 90,000 ሺህ: ከ Vermi worm ሽያጭ ብር 18,000 እንደሸጡ እና ከ30 ኩ/ል በላይ ቬርሚ ኮምፖስት ደግሞ የተለያዩ ሰብሎችንና ከደቡብ ክልል ያመጧቸው የአትክልትና ፍራፍሬ ዘሮችን ለመዝራት እንደተጠቀሙበት ገልፀው በቀጣይም ስራቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ያላቸውን ቁርጠኝነት ጠቁመዋል።

በመጨረሻም የአርሶ አደሮች የመስክ ትምህርት ቤት አባላትና አጠቃላይ የጉብኝቱ ተሳታፊዎች የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ባለድርሻ አካላት በመካከላቸው ተገኝተው በመሳተፋቸውና ለሰጧቸው ሙያዊ አስተያየቶችና ምክሮች ሁሉ አክብሮት እንዳላቸው ገልፀው በቀጣይ በሚያከናውኗቸው ማናቸውም የግብርና የልማት ስራዎች እንደተለመደው ሁሉ ወረዳው ከጎናቸው እንደሚሰለፍ ያላቸውን ፅኑ እምነት ገልፀው የዕለቱ የመስክ ምልከታ ተጠናቅቋል።

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአሶሳ ዞን በአቡራሞ ወረዳ በኮመሽጋ 26 ቀበሌ በአርሶ አደር ማሰልጠኛ ማዕከል እና በሞዴል አርሶ አደሮች ማሳ ላይ የአርሶ አደር የመስክ በዓል ተከበረ፤*******...
21/10/2025

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአሶሳ ዞን በአቡራሞ ወረዳ በኮመሽጋ 26 ቀበሌ በአርሶ አደር ማሰልጠኛ ማዕከል እና በሞዴል አርሶ አደሮች ማሳ ላይ የአርሶ አደር የመስክ በዓል ተከበረ፤
************************************************************************************
(ጥቅምት 11/02/2018 ዓ.ም) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአሶሳ ዞን በአቡራሞ ወረዳ በኮመሽጋ 26 ቀበሌ በሞደል አርሶ አደሮች ማሳ እና በአርሶ አደሮች ማሰልጠኛ ማዕከል የአቡራሞ ወረዳ አመራሮች ፣ የግብርና ጽ/ቤት አመራሮችና ቡድን መሪዎች ፣ የኮመሽጋ 26 ቀበሌ አርሶ አደሮች ፣የሀገር ሽማግሌዎች ፣ የቀበሌ አመራሮችና የቀበሌ ግብርና ባለሙያዎች የተሳፉበት የአርሶ አደሮች መስከ በዓል ተከብሯል።

አርሶ አደሮች የተሻሻሉ የሰብል ዝሪያዎችን በመጠቀም አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ተግባራዊ በማድረግ በግብር ዘርፍ የጎላ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸዉን ማረጋገጥ እንዳለባቸዉ የአቡራሞ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አታላይ ደረጄ ገልፀዋል ።

በመስክ በዓሉ የሞደል አርሶ አደር የአቶ አሊጋዝ አድማሴ ዉጤታማ የለውዝ፣ የበቆሎ፣የአኩሪ አተር እና ሌሎች ሰብል ዝርያዎች ጉብኝት የተደረገ ሲሆን የኮ/26 ቀበሌ አርሶ አደር ማሰልጠኛ ማዕከል በሰብል፣በእርባታ፣ የተሰሩ ስራዎች የቀበሌው አርሶ አደሮች በተገኙበት ጉብኝት ተደርጉዋል።

በመስክ በዓሉ የሞደል አርሶ አደር የአቶ አሊጋዝ አድማሴ ዉጤታማ የለውዝ፣ የበቆሎ፣የአኩሪ አተር እና ሌሎች የሰብል ዝርያዎች ላይ ጉብኝት የተደረገ ሲሆን በኮመሽጋ 26 ቀበሌ የአርሶ አደር ማሰልጠኛ ማዕከል ላይ በሰብል፣በእርባታ፣በተለይም ደግሞ አድሱ የሩዝ ሰብል ኢኒሸቲቭ ውጤታማነትን የሚያረጋግጥ እና የወረዳውን Agro Ecology መሠረት ያደረገ ተስፋ ሰጭ የሩዝ ሰብል ሰርቶ ማሳያ ጎልቶ የወጣበት ጉብኝት ተካሂዷል።

በመስከ በዓሉ የኮ/26 ቀበሌ ሞደል አርሶ አደር የሆኑት አርሶ አደር ኑርዬ መሀመድ እንደገለፁት የግብርና ባለሙያን ምክርና ድጋፍ በመቀበል፣ አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በመተግበር አኩሪ አተር በመዝራት የተሻለ ምርት ለማግኘትና በምርት ዘመኑ ስኬታማ ስራዎችን በመስራት የተሻለ ምርት እንደሚያገኙ ገለጿል ።

ሞደል አርሶ አደርና አመራር አቶ ያሲን ኑርዬ ሌሎች አርሶ አደሮች እርስ በእርስ ተሞክሮ በመቀመር በጋራ ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ዉጤታማ መሆን እንዳለባቸዉ በመጠቆም በመኽር እርሻ በተጨማሪ በእንስሳት እርባታ ስራ ዉጤታማ ለመሆን ትኩረት አድርገን እየሰራን ነው ያሉ ሲሆን በመጨረሻም ወረዳው የአርሶ አደር ማሰልጠኛ ማዕከል ግንባታ እና የእንስሳት ክሊኒክ ግንባታ ዘመናዊ በመሆነ መንገድ እንዲሰራላቸው ጠይቀዋል።

የቀበሌዉ አርሶ አደሮች ምርትና ምርታማነት ለማሳደግና በግብርና ዘርፍ አርሶ አደሮች የኢኮኖሚ ተጠቃሚ ለማድረግ የቀበሌዉ አመራርና የቀበሌዉ ግብርና ልማት ጽ/ቤት በቅንጅት እየሰራ መሆኑን የኮመሽጋ 26 ቀበሌ ዋና አስተዳደሪ አቶ ያሲን ኑርዬ እና የቀበሌዉ ግብርና ልማት ጣቢያ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ደሳለኝ ሲሳይ ገልፀዋል።

የአቡራሞ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አታላይ ደረጄ አርሶ አደሮች በሞደል አርሶ አደር ማሳ እና በአርሶ አደር ማሰልጠኛ ማዕከል የተሰሩት ስራዎችን በመቀመር፣ በሳይንሳዊ ዘዴ እንዲሁም የባለሙያ ምክርና ድጋፍ ተግባራዊ በማድረግ የተሻሻሉ አዳዲስ ቴክኖሎጅዎችን ተጠቅሞ በማልማት ምርትና ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ አልፈዉ በግብርናው ዘርፍ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን እንዳለባቸዉ አቶ አታላይ ደረጄ አሳስበዋል ።
የአቡራሞ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም አሻፊ በበኩላቸው በሞደል አርሶ አደሮች ማሳ የተጎበኘዉ ዉጤታማ የበርበሬ ፣ የአኩሪአተርና የበቆሎ ሰብል ለሌሎች አርሶ አደሮች ተሞክሮ መሆን የሚችልና የማህበረሰብን በግብርና ዘርፍ እድገትና ተጠቃሚነተን የሚያሳይ በመሆን ሁሉም አርሶ አደሮች ተሞክረዉን በመቀመርና በማስፋት በማሳቸዉ ተግባራዊ በማድረግ የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን በግብርና ዘርፍ ዉጤታማ በመሆን ኑሮዋቸዉን በማሻሻል የኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን እንዳለባቸዉ አቶ ኢብራሂም አሻፊ አሳስበዋል ።

የክልሉ ግብርና ቢሮ የአርሶ አደር ማሰልጠኛ ማዕከል ክትትልና ድጋፍ ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ጌታሁን ስጦታው አና የክልሉ ግብርና ቢሮ የግል ባለሀብቶች ክትትልና ድጋፍ ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ውንዲፍራው አመዴ እንዲሁም ሌሎች የክልሉ ባለሙያዎች ተገኝተው አርሶ አደሮቻችን የተሻለ ስራ እየሰሩ መሆናቸውን ገልፀው ለቀጣይ አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በተለይም ደግሞ ኩታ ገጠምን በሰፊው በመተግበር ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናቸውን በማረጋገጥ ትርፍ ምርት አምርተው የኑሮ ደረጃቸውን ከፍ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

በመጨረሻዉ በምርት ዘመኑ የተሻለ ዉጤት ለአስመዝገቡት የቀበሌ የግብርና ባለሙያዎች፣ለሞደል አርሶ አደሮች የዕዉቅና እና የማበረታቻ ሰርቲፊኬት ተሰጧል።

ወጣቶች ለግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ዕድገት አይተኬ ሚናቸውን እንዲወጡ በትኩረት እየተሰራ ነው*************ወጣቶች ለግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ዕድገት አይተኬ ሚናቸውን እንዲወጡ በትኩረት እ...
19/10/2025

ወጣቶች ለግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ዕድገት አይተኬ ሚናቸውን እንዲወጡ በትኩረት እየተሰራ ነው
*************

ወጣቶች ለግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ዕድገት አይተኬ ሚናቸውን እንዲወጡ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ።

በአቡራሞ ወረዳ አበንዴ ምንጊዳ ቀበሌ ወጣቶች እየሰሩት ባለው የበቆሎ ኩታ ገጠም እርሻ የልምድ ልውውጥ ከወረዳው ከተውጣጡ ወጣቶች ጋር ተካሂዷል።

በአቡራሞ ወረዳ አበንዴ ምንጊዳ ቀበሌ በማህበር ተደራጅተው ወደ ስራ የገቡ ወጣቶች እንዳሉት 40 ሄክታር መሬት ላይ በኩታ ገጠም እያለሙት ካለው በቆሎ የተሻለ ምርት እንደሚጠበቁ ተናግረዋል።

በቀጣይም አሁን እያለሙት ያለውን ማሳ በማስፋት በዘርፉ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ እንደሚሰሩም ገልፀዋል ።

ላከናወኑት ስኬታማ ሥራ ወረዳውና የስደተኞች ተፅዕኖ ምላሽ ፕሮጀክት ባደረጉላቸው ድጋፍና ክትትል ወጣቶቹ ምስጋና አቅርበዋል።

የአቡራሞ ወረዳ የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አታላይ ደረጀ እንዳሉት ደግሞ በተያዘው የመኸር ዘመን በወረዳው የሚገኙ 9ሺህ 2 መቶ ወጣቶች በግብርናው ዘርፍ መሰማራታቸውን ጠቁመዋል።

በአበንዴ ምንጊዳ ቀበሌ በማህበር ተደራጅተው ወደ ስራ የገቡ 35 ወጣቶች በ40 ሄክታር መሬት በኩታ ገጠም የእርሻ ዘዴ እያለሙት ያለው ሥራ ለሌሎች ወጣቶች በአርያነት የሚጠቀስ መሆኑንም ተናግረዋል።

የወጣቶችን ጨምሮ በቀበሌው 220 ሄክታር መሬት በኩታ ገጠም እየለማ እንደሚገኝም ገልፀዋል።

የወረዳው ወጣቶች በሀገር ደረጃ ለተያዘው የግብርናው ዘርፍ ክፍለ ኢኮኖሚ ዕድገት አይተኬ ሚናቸውን እንዲወጡም ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ መሆኑንም አሳውቀዋል።

በኢንቨስትመንት ስም ሳይለማ የቆየውን መሬት ለወጣቶች እንዲተላለፍ ተወስኖ በተሰጣቸው መሬት ላይ ወጣቶቹ የሰሩት ስራ ውጤታማ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ባበክር ሃሚድ ናቸው።

ወጣቶች በዘርፉ ተጠባቂ ለውጥ እንዲያስመዘግቡ የሚደረገው ክትትልና ድጋፍ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል ።

መሰል ስራዎች ውስጥ ሁሉም የወረዳው ወጣቶች እንዲሰማሩም ይሰራል ብለዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ባበክር ኻሊፋ እንዳሉት በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች በግብርናው ዘርፍ የተሰማሩ ወጣቶች ውጤታማ ሥራ በማከናወን ላይ መሆናቸውን አሳውቀዋል ።

በቀጣይም ወጣቶች ክልሉ ካለው አቅም አንፃር ከዘርፉ የላቀውን ጥቅም እንዲያገኙ ሜካናይዜሽንን ለማስፋፋት እየተሰራ እንደሚገኝ መግለጻቸውን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሚዲያ ዘግቧል።

Address

Assosa
Asosa
5220

Telephone

+251577750772

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በቤ/ጉ/ክ/መ በአሶሳ ዞን የአቡራሞ ወረዳ ግብርናና ተፈጥሮ ሀብት ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share