የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን

  • Home
  • Ethiopia
  • Arba Mintch
  • የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከሙስና የፀዳች ኢትዮጵያ!!!

‎ዜና ችሎትበሙስና ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በጽኑ እስራትና በገንዘብ ተቀጣ‎‎ግንቦት 28/2018 ዓ.ም ‎የወላይታ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የንብረት ክፍል ሰራተኛ በነበረው ተከሳሽ ሐብቴ ዳ...
05/06/2026

‎ዜና ችሎት

በሙስና ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በጽኑ እስራትና በገንዘብ ተቀጣ

‎ግንቦት 28/2018 ዓ.ም ‎የወላይታ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የንብረት ክፍል ሰራተኛ በነበረው ተከሳሽ ሐብቴ ዳንጋርሶ ላይ የቀረበውን የሙስና ወንጀል ክስ መዝገብ መርምሮ ውሳኔ አስተላልፏል።

‎ተከሳሹ በአረካ ከተማ አስተዳደር ሀንጋዳ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የንብረት ክፍል ሠራተኛና ቁልፍ ያዥ ሆኖ በሚሰራበት ወቅት ከምሽቱ 1፡30 ሰዓት ላይ ከተቋሙ ንብረት ክፍል 16 ካርቶን የዋጋ ግምቱ 585,738 (አምስት መቶ ሰማኒያ አምስት ሺህ ሰባት መቶ ሰላሳ ስምንት) ብር የሆነውን የተማሪዎች እና የመምህራን መጻሕፍትን ለግል ጥቅሙ ለማዋል በባጃጅ ሲጭን እጅ ከፍንጅ ተይዞ በከባድ እምነት ማጉደል የሙስና ወንጀል ተከሷል።

‎የወላይታ ዞን ፍትህ መምሪያ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን የክስ ማስረጃ የተመለከተው የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሹን ጥፋተኛ በማለት በ3 ዓመት ከ3 ወር ጽኑ እስራት እና በ5,000 ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ወስኗል።

ዘገባው:- የወላይታ ዞን ፍትህ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ክፍል

‎በሐሰተኛ የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለመገልገል የሞከሩ ግለሰቦች በፅኑ እስራት ተቀጡ‎‎ግንቦት 26/2018 ዓ.ም ‎​በወላይታ ዞን በሐሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀትና መገልገል የሙስና ወንጀል ...
03/06/2026

‎በሐሰተኛ የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለመገልገል የሞከሩ ግለሰቦች በፅኑ እስራት ተቀጡ

‎ግንቦት 26/2018 ዓ.ም ‎​በወላይታ ዞን በሐሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀትና መገልገል የሙስና ወንጀል ክስ ቀርቦባቸው የነበሩ ሁለት ግለሰቦች በጽኑ እስራትና በገንዘብ መቀጮ ተቀጡ፡፡

‎ተከሳሾቹ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ 1ኛ ተከሳሽ የ2ኛ ተከሳሽ ጠበቃ ሲሆን 2ኛ ተከሳሽ ከአይናቴ ሎሪሶ ከተባለች ግለሰብ ጋር በነበረው የውርስ ክርክር ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ/ቁ 47413 በሆነው በቀን 12/06/16ዓ.ም ለ2ኛ ተከሳሽ ውሰኔ የተወሰነ በማስመሰል ሐሰተኛ የጠቅላይ ፍ/ቤት ማህተምና የጠቅላይ ፍ/ቤቱ ምክትል ፐሬዝዳንት ፊርማ ያልሆነውን በማሳረፍ ሐሰተኛ የውሳኔ ግልባጭ ለ2ኛ ተከሳሽ የሰጠ ሲሆን 2ኛ ተከሳሽም የተዘጋጀውን ሐሰተኛ ውሳኔ እያወቀ በመገልገል የግል ተበዳይ አይናቴ ሎሪሶን የውርስ ክስ በመቃወም ለዳሞት ፑላሳ ወረዳ ፍ/ቤት ያቀረበ በመሆኑ ተከሳሾች በፈጸሙት ሐሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀትና መገልገል ወንጀል ተከሰዋል፡፡

‎የወላይታ ዞን ፍትህ መምሪያ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን የክስ መዝገብ የመረመረው የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሾቹን ጥፋተኛ በማለት 2 አመት ከ9 ወር ጽኑ እስራት እና 1,000 ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል፡፡
‎​"ይህ የቅጣት ውሳኔ ለሌሎች መሰል ድርጊት ለሚፈጽሙ አካላት አስተማሪ እንዲሆን ታስቦ የተላለፈ ነው፡፡ ማህበረሰቡም የሙስና ወንጀልን ለመከላከልና አጥፊዎችን ወደ ሕግ ለማቅረብ የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ ይገባል፡፡"
ዘገባው ‎የወላይታ ዞን ፍትህ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ክፍል

በግል ማህበራዊ ሚዲያ የምርጫ ሂደት ሳይጠናቀቅ ያልተረጋገጠ ሀሰተኛ የምርጫ ውጤት ይፋ ያደረገ ግለሰብ በገንዘብ ተቀጣ‎ግንቦት 24/2018 ዓ/ም፦ ‎በባስኬቶ ዞን ‎ላስካ ከተማ አስተዳደር  ...
01/06/2026

በግል ማህበራዊ ሚዲያ የምርጫ ሂደት ሳይጠናቀቅ ያልተረጋገጠ ሀሰተኛ የምርጫ ውጤት ይፋ ያደረገ ግለሰብ በገንዘብ ተቀጣ

ግንቦት 24/2018 ዓ/ም፦ ‎በባስኬቶ ዞን ‎ላስካ ከተማ አስተዳደር ሰባተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በሂደት ላይ ባለበት ወቅት ''ብልጽግና ፓርቲ በድምፅ እየመራ ነው'' በማለት ሐሰተኛ መረጃ በግል ማህበራዊ ሚዲያ ገፅ ያጋራው ግለሰብ በ3000 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ተቀጣ።

‎መ/ር አለልኝ አሰፉ የላስካ 02 ቀበሌ ነዋሪ ሲሆን የምርጫ ሂደቱ ባልተጠናቀቀበት የድምፅ አሰጣጥ ሂደትን በመጣስ በሰራው ወንጀል የቀረበበትን ክስ ሙሉ በሙሉ አምኖ ተቀብሏል።

‎ግለሰቡ ወንጀሉን እንደፈጸመ በማመኑ ተጨማሪ የምስክር ቃል መስማት አስፈላጊ አለመሆኑን ዐቃቤ ህግ ያቀረበ ሲሆን ፍርድ ቤቱ ክሱን ተቀብሎ ተከሳሽን ያስተምራል ለሌሎችም ትምህርት ይሆናል በማለት በተከሳሽ ላይ የቅጣት ውሳኔ አስተላልፎበታል።

የላስካ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ግለሰቡ ጥፋተኛነቱን አምኖ በመቀበሉ በ3 ሺህ ብር እንዲቀጣ ውሳኔ ማስተላለፉን የላስካ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሚዩኒኬሽን በማህበራዊ ሚዲያ ዘግቧል።።

በምርጫ ዕለት የተከለከለ ተግባር ሲፈጽም የነበረ ተከሳሽ በእስራት መቀጣቱን የደቡብ አሪ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት አስታወቀ         ግንቦት 24/2018 ዓ.ም በምርጫ ዕለት የተከለከለ ተግባር...
01/06/2026

በምርጫ ዕለት የተከለከለ ተግባር ሲፈጽም የነበረ ተከሳሽ በእስራት መቀጣቱን የደቡብ አሪ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት አስታወቀ

ግንቦት 24/2018 ዓ.ም በምርጫ ዕለት የተከለከለ ተግባር ሲፈጽም የነበረ ተከሳሽ በእስራት መቀጣቱን የደቡብ አሪ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በየነ ጉዶ አስታውቀዋል።

አቶ በየነ ጉዶ እንደገለፁት ከምርጫ ጋር በተያያዘ የሚቀርቡ አቤቱታዎችንና ክርክሮችን ለመፍታት በዛሬው ዕለት በወረዳው የተለያዩ ክላስተሮች ጊዜያዊ ችሎቶች ተቋቁመው ሲሰሩ እንደነበር አስታውሰው በወረዳችን አንድ የምርጫ ነክ ወንጀል መዝገብ በፍጥነትና በአጭር ጊዜ ውስጥ ውሳኔ አግኝቷል ብለዋል።

አቤቱታው የቀረበለት የደቡብ አሪ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት የት/አ/ወ/ምርመራ ማስተባበሪያ ክፍል ከወረዳው ዐ/ህግ ጋር በጋራ ምርመራ በማጣራት በፍጥነት ለዐ/ህግ መዝገቡ እንደተላከ እና ዐ/ህግም ወዲያኑ ክስ መመስረት መቻሉን አስረድተዋል።

የዐ/ህግ ክስ እንደሚያስረዳውም አቶ ኢህአዴግ ኃይሉ የተባለው ተከሳሽ የኢትዮጵያ ምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 157 (2)ን በመተላለፍ በዛሬው ዕለት በቀን 24/9/2018 ዓ.ም ዕለት ሰኞ በግምት ከረፋዱ 4:00 ሰዓት ገደማ በደቡብ አሪ ወረዳ ገድር ቀበሌ ልዩ ስሙ አመንዴል ተብሎ በሚጠራው ልማት ቡድን ውስጥ የራሱን ድምፅ ሰጥቶ ከወጣ በኋላ እዚያው በምርጫ ጣቢያው አጠገብ መንገድ ላይ ሆኖ ወጣት ወገኔ ሰብስቤ የተባለው ድምፅ ለመስጠት ወደ ምርጫ ጣቢያ እየሄደ ሳለ ኢዜማን ምረጥ ወይም የሚዛን ምልክቱ ውስጥ ጣል በማለት በድምፅ መስጫ ዕለት በድምፅ መስጫ ጣቢያ አከባቢ ድምፅ ከመስጠት ውጪ በምርጫ ዕለት የተከለከለውን የፖለቲካ እንቅስቃሴ ወይም ቅስቀሳ አድርጓል በማለት ዐ/ህግ የሰው ማስጃዎችን አስደግፎ ለደቡብ አሪ ወረዳ ፍርድ ቤት የወንጀል ክስ አቅርቧል።

ክሱ የቀረበለት ፍርድ ቤትም ለተከሳሾች ክስ ቻርጅ እንዲደርስ ካደረገ በኋላ የእምነት ክህደት ቃላቸውን በመቀበል፣ የዐ/ህግ ምስክሮችን ቃል በማድመጥ፣ ተከሳሽ እንዲከላከል ዕድል ቢሰጠውም መከላከያ ማስረጃ የለኝም በማለቱ በቀረበበት ክስ ጥፋተኛ ነው ሲል ውሳኔ አሳልፏል።

የግራ ቀኙን የቅጣት አስተያየት ከተቀበለ በኋላ ተከሳሽ የሦስት ልጆች አሳዳጊ በመሆኑና ሌሎችም ማቅለያዎችን በመቀበል ተከሳሽ ይማራል ለሌሎችም ማስጠንቀቂያ ይሆናል በማለት ተከሳሽ በ6 ወር ቀላል እስራት በ2 ዓመት ገደብ እንዲቀጣ በማለት ውሳኔ አስተላልፏል።

የደቡብ አሪ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በየነ ጉዶ ፍርድ ቤቱ የሰጠው ውሳኔ አስተማሪና ተገቢ መሆኑን በመጥቀስ ፍርድ ቤቱ መዝገቡ በፍጥነት ውሳኔ እንዲያገኝ በማድረጋቸው ምስጋና ያቀረቡ ስሆን ሰዎች ከመሰል የወንጀል ድርጊት እንዲታቀቡም አሳስበዋል።

‎በምርጫ ሰነድ ማጥፋት ወንጀል የተከሰሰው የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚ በእስራት ተቀጣ ‎‎ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ‎በወላይታ ዞን ኪንዶ ኮይሻ ምርጫ ክልል ቴጭና ቀበሌ በሚገኘው ባንቶ ጤና ኬላ...
01/06/2026

‎በምርጫ ሰነድ ማጥፋት ወንጀል የተከሰሰው የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚ በእስራት ተቀጣ

‎ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ‎በወላይታ ዞን ኪንዶ ኮይሻ ምርጫ ክልል ቴጭና ቀበሌ በሚገኘው ባንቶ ጤና ኬላ ምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚ የነበረው ተከሳሽ አብነት በርገነ ባንቴሮ የመራጮችን መዝገብ በማጥፋት ወንጀል ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ የ5 ወር ቀላል እስራት ተፈረደበት።

‎ተከሳሹ አብነት በርገነ ባንቴሮ በተሰጠው ህዝባዊና ሙያዊ ኃላፊነት ተጠቅሞ የዜጎችን ድምጽና የምርጫ ሂደት ውሳኔ የሚወሰንበትን የባንቶ ጤና ኬላ ምርጫ ጣቢያ የመራጮች መዝገብ በማጥፋት ወንጀል ተጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።
የወንጀሉን ክብደትና የምርጫ ሂደቱን ሰላማዊነት ለማረጋገጥ ሲባል ጉዳዩን በአስቸኳይ ለማጣራት በተቋቋመው ልዩ ችሎት የምርመራ መዝገቡ በሰፊው ሲመረመር የቆየ ሲሆን ልዩ ችሎቱ ግራ ቀኙን ካደመጠና የቀረቡትን የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች በጥብቅ ከመረመረ በኋላ ተከሳሹ የወንጀል ድርጊቱን መፈጸሙን በማረጋገጡ ጥፋተኛ በማለት በ5 ወር ቀላል እስራት እንዲቀጣ በዛሬው ዕለት ውሳኔ አስተላልፏል።

‎ይህ ውሳኔ በምርጫ ሂደት ላይ የሚፈጸሙ ማናቸውንም ህገ-ወጥ ድርጊቶች ለመከላከል እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር የተወሰደ ጠንካራ እርምጃ መሆኑ ተገልጿል።

ዘገባው ‎የወላይታ ዞን ፍትህ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ክፍል ነው

 እንኳን  #ለ1447ኛው የኢድ አል-አድሀ ( #አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!ይህ ታላቅ በዓል የነቢዩ ኢብራሂም (ዐ.ሰ) እና የልጃቸው የነቢዩ ኢስማኢል (ዐ.ሰ) ታላቅ የመታዘዝ፣ የፅናት...
26/05/2026



እንኳን #ለ1447ኛው የኢድ አል-አድሀ ( #አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

ይህ ታላቅ በዓል የነቢዩ ኢብራሂም (ዐ.ሰ) እና የልጃቸው የነቢዩ ኢስማኢል (ዐ.ሰ) ታላቅ የመታዘዝ፣ የፅናትና የመስዋዕትነት ታሪክ የሚዘከርበት ቅዱስ ዕለት ነው።

በዓሉ የተጠሙትን በማጠጣት፣ የተራቡትን በማብላትና ለተቸገሩ በማካፈል የእስልምናን ውበትና መተሳሰብ በተግባር የምናሳይበት ይሁን

ኢድ ሙባረክ!

‎የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ምልክት የሆነውን የስንዴ ነዶ ፖስተር የቀደዱ ግለሰቦች የእስራት ውሳኔ እንደተላለፈባቸው ተገለፀ‎ ግንቦት 10/2018 ዓ.ም (አርባምንጭ) ‎ አቡሽ አየለ፣ ትግሉ ...
18/05/2026

‎የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ምልክት የሆነውን የስንዴ ነዶ ፖስተር የቀደዱ ግለሰቦች የእስራት ውሳኔ እንደተላለፈባቸው ተገለፀ

ግንቦት 10/2018 ዓ.ም (አርባምንጭ) ‎ አቡሽ አየለ፣ ትግሉ ክፍሌ፣ ሳሙኤል ጅክሶ እና እምነቱ እሸቱ የተባሉ አራት ተጠርጣሪዎች የብልግና ፓርቲ የምርጫ ምልክት ፖስተር ቀድደው በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ይታወቃል።

‎በተጠረጠሩበት የምርጫ አዋጅ ቁጥር 1162 አንቀጽ 158 ስር የተደነገገውን በመተላለፍ ተከሶ 3ቱ ተከሳሾች በችሎቱ ድርግቱን መፈፀማቸውን ስላመኑ ምስክር መስማት ሳያስፈልግ በወንጀልኛ መቅጫ ሥነ-ስርዓት ህግ ቁጥር 149/1/ መሠረት የጥፋተኝነት ውሳኔ ተሰጥቷል።

‎ፍ/ ቤቱ በቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 3/2017 አንቀፅ 12 "መሠረት ወንጀሉ ደረጃ ያልወጣለት ስለሆነ ደረጃ በማውጣት የወንጀሉን አፈፃፀም ሂደት በከፍተኛ የፈረጀ ሲሆን እያንዳንዳቸው በ7 ወር እስራት እንድቀጡ ወስኗል።

‎4ኛ ተከሳሽ በተመለከተ ድርጊቱን ክዶ በመከራከሩ በዛሬው ዕለት የሰው ማስረጃ የተሰማ ሲሆን ግለሰቡ ወንጀል ያለመፈፀሙን እንድከላከል ለመከላከያ ማስረጃ ተቀጥሯል።

ምንጭ:- የጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት ነው

የመንግስት ሥራን በማያመች አኳኋን መምራት የሙስና ወንጀል መሆኑን ያውቃሉ?*****************ሥራን በማያመች ሁኔታ መምራት ማለት ግልጽ የሆኑ የአሠራር መመሪያዎችን አለመከተል፣ መረጃ...
16/05/2026

የመንግስት ሥራን በማያመች አኳኋን መምራት የሙስና ወንጀል መሆኑን ያውቃሉ?

*****************

ሥራን በማያመች ሁኔታ መምራት ማለት ግልጽ የሆኑ የአሠራር መመሪያዎችን አለመከተል፣ መረጃን መደበቅና ለሕዝብ ክፍት አለማድረግ ማለት ነው። አሠራሩ ግልጽ ካልሆነ ደግሞ ተጠያቂነት ይጠፋል፤ ይህም ሙስና በስውር እንዲከናወን ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።

አንድ የመንግስት የሥራ ኃላፊ ወይም ባለሙያ፣ ቀልጣፋ መሆን የሚገባውን አሠራር ውስብስብና አድካሚ በማድረግ፣ ተገልጋዩ ጉዳዩ እንዲያልቅለት የግዴታ "ጉቦ" እንዲከፍል ወይም "አቋራጭ" እንዲፈልግ ይገፋፋዋል።

የመንግስት ሥራ በተገቢው መንገድና ቅልጥፍና ካልተመራ፣ ጊዜና ገንዘብ ያለአግባብ ይባክናል። ይህ መባከን ደግሞ ለግል ጥቅም የሚውሉ ክፍተቶችን ይፈጥራል። ለአብነት የአቅርቦት ሰንሰለትን ማጓደል ወይም አላስፈላጊ ሂደቶችን መደርደር ለሙስና ተጋላጭ ያደርጋል።

ሥራን ለተገልጋይ በማያመች መምራት አንድ የመንግስት ሠራተኛ የተሰጠውን ሕዝባዊ ኃላፊነት ተጠቅሞ አገልግሎትን ማዘግየት ወይም ማወሳሰብ የሥነ-ምግባር መጓደል ብቻ ሳይሆን፣ ሕጋዊ ተጠያቂነት የሚያስከትል የሙስና ወንጀል ተባባሪነት ነው።

አሠራሩ አመቺ ካልሆነ ተገቢው አገልግሎት ለዜጎች በወቅቱ አይደርስም። ይህም በዜጎችና በመንግስት መካከል ያለውን መተማመን ይሸረሽራል። ሥራን በአግባቡ አለመምራት የሥራ መጓደልን ስለሚፈጥር፣ ይህ ክፍተት የሙስና ሰንሰለት እንዲበራከት ያደርጋል።

ይህን አስመልክቶ የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣው አዋጅ ቁጥር 881/2007 በሚከተለው መልኩ በግልጽ አስቀምጦታል።

ማንኛውም የመንግስት ሠራተኛ ወይም ህዝባዊ ድርጅት ሠራተኛ የማይገባ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለማስገኘት በማሰብ ስልጣኑን ወይም ኃላፊነቱን ተጠቅሞ ከሚያከናውነው ሥራ ጋር በተያያዘ በማናቸውም የሥራ ግንኙነት ማናቸውንም ዓይነት ጥቅም የወሰደ፣ አግባብ ባለው ባለስልጣን ከተወሰነው በላይ በሆነ ዋጋ የዕቃ ማቅረብ ውል፣ የሥራ መቋረጥ ውል ወይም ማናቸውም የሥራ ውል የተዋዋለ እንደሆነ፤ በሥራዉ ሥልጣን መሠረት በአደራ የተሰጠውን የመንግስት መስሪያ ቤት፣ የመንግስት የልማት ድርጅት ወይም የህዝባዊ ድርጅት ጥቅም የሚጎዳ ተግባር በማናቸዉም ዘዴ የፈፀመ እንደሆነ በሙስና ወንጀል ያስጠይቃል ሲል ይደነግጋል፡፡

ስለሆነም፣ የመንግስት ሥራን ምቹና ቀልጣፋ አለማድረግ ለፍትሕ መጓደል፣ ለሙስናና ብልሹ አሰራር መበራከት መደላደል የሚፈጥር በመሆኑ፣ እያንዳንዱ የተቋም የሥራ ኃላፊና ሠራተኛ አሠራሩ ግልጽ፣ ፈጣንና ለሕዝብ አመቺ እንዲሆን የማድረግ ግዴታ አለበት። ተገልጋዩም ራሱን በመልካም ሥነምግባር አርዓያ ከማድረግ ባሻገር ሙሰኞችን የማጋለጥ ኃላፊነት መወጣት አለበት።

ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!

የታማኝነት ተምሳሌት - በስህተትህ ወደ አካውንቱ የገባውን ግማሽ ሚሊዮን ብር የመለሰው  ዘማሪ አብነት ነጋሽ ቶክቻውዘማሪ አብነት ነጋሽ ቶክቻው በስህተት ወደ አካውንቱ የገባለትን ከግማሽ ሚሊ...
15/05/2026

የታማኝነት ተምሳሌት -

በስህተትህ ወደ አካውንቱ የገባውን ግማሽ ሚሊዮን ብር የመለሰው ዘማሪ አብነት ነጋሽ ቶክቻው

ዘማሪ አብነት ነጋሽ ቶክቻው በስህተት ወደ አካውንቱ የገባለትን ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ (500,000+) በአካል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመገኘት ለባለቤቱ እንዲመለስ አድርጓል።

• በፈተና ወቅት ታማኝነትን በተግባር አሳይቷል።

• እንዲህ አይነት ቅንነት ከግለሰብ አልፎ ለሀገር እድገትና ለህዝብ ትስስር መሰረት ነው።

ይህ መልካም ተግባር ለሁላችንም ትልቅ ትምህርትና መነሳሳት ይሁን።

 በምርጫ ምልክት ላይ ጉዳት ያደረሰው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ‎‎ #ግንቦት 06/ 2018 ዓ. ም ‎በወላይታ ዞን ባይራ ኮይሻ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ምልክት የሆነውን የ"ስንዴ ነዶ" ...
14/05/2026



በምርጫ ምልክት ላይ ጉዳት ያደረሰው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ

‎ #ግንቦት 06/ 2018 ዓ. ም ‎በወላይታ ዞን ባይራ ኮይሻ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ምልክት የሆነውን የ"ስንዴ ነዶ" ባነር ቀድዶ የጣለው ተከሳሽ በ5 ወር ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ተወሰነበት።

‎ተከሳሽ አቶ በላቸው ባሳ በቀን 06/09/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 5:00 ገደማ በባይራ ኮይሻ ወረዳ "ጠካቻ ቀጠና 1" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተሰቅሎ የነበረን የፓርቲውን የምርጫ ቅስቀሳ ባነር ቀድዶ በመጣል ለማምለጥ ሲሞክር በአካባቢው በነበሩ ሰዎች እጅ ከፍንጅ ተይዟል።

‎በወረዳው ፖሊስ ምርመራው በአስቸኳይ ተጠናቅቆ የቀረበለት ዐቃቤ ሕግ ክስ የመሰረተ ሲሆን ተከሳሹ በ2011 ዓ.ም የወጣውን የኢትዮጵያ የምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162 አንቀጽ 158ን በመጣስ ወንጀል መፈጸሙን የሚያስረዱ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል።

‎ተከሳሹ የቀረበበትን የጥፋተኝነት ክስ አምኖ በችሎት ቃሉን ሰጥቷል።
‎የባይራ ኮይሻ ወረዳ ፍርድ ቤት መዝገቡን መርምሮ ድርጊቱ መፈፀሙን በማረጋገጡ ተከሳሹን የሚያርምና ሌሎችም ተመሳሳይ ድርጊት እንዳይፈጽሙ የሚያስተምር መሆን አለበት በማለት ተከሳሹ በ5 ወር እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።

"‎የምርጫ ህግን ማክበር የሰለጠነ ዜጋ መገለጫ ነው!"

ምንጭ:- የወላይታ ዞን ፍትህ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት ክፍል

፤ !

Address

Arba Mintch

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share