Gamo Zone women and children affairs department

Gamo Zone women and children affairs department Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gamo Zone women and children affairs department, Government Organization, Arba Mintch.

ከሕብረተሰቡ ጋር በመቀናጀትና ፍትህን በማስፈን በሴቶችና ሕፃናት ላይ የሚፈፀም ጥቃት መቀነስ እንደሚቻል ተገለፀአርባ ምንጭ፦ ጥቅምት  03/2018 ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሚዩኒኬሽን"በሴቶችና ...
14/10/2025

ከሕብረተሰቡ ጋር በመቀናጀትና ፍትህን በማስፈን በሴቶችና ሕፃናት ላይ የሚፈፀም ጥቃት መቀነስ እንደሚቻል ተገለፀ

አርባ ምንጭ፦ ጥቅምት 03/2018 ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሚዩኒኬሽን

"በሴቶችና ሕፃናት ላይ የሚደርስ ጥቃት በጋራ እንከላከል" በሚል መሪ ቃል የጋሞ ዞን ሕዝብ ምክር ቤት ሴቶች፣ ወጣቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ከዞኑ ሴቶችና ሕፃናት ጉዳይ መምሪያ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የሕዝብ አስተያየት መሰብሰቢያ መድረክ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በብርብር ከተማ ተካሂዷል።

የጋሞ ዞን ሕዝብ ምክር ቤት አፌ-ጉባኤ ወ/ሪት አለሚቱ ዮሴፍ በመድረኩ ማጠቃለያ በሴቶችና ሕፃናት ላይ የሚደርስ ጥቃት መከላከል የሁሉም ሕብረተሰብ ተግባር እንዲሆን በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀው በተለይ በቅርብ ሰዎች እያደረሰ ያለውን ጥቃት ዜጎች በሕግ ከማስጠየቅ ባለፈ ማውገዝ እንደሚገባም አሳስበዋል።

ከሕብረተሰቡ ጋር በመቀናጀትና ፍትህን በማስፈን በሴቶችና ሕፃናት ላይ የሚፈፀም ጥቃት መቀነስ እንደሚቻል የጠቆሙት አፈ ጉባኤዋ በእጅ መንሻ የሚንቀሳቀሱ የመንግስት አካላትን ለማረም በርካታ ተቋማት ወደ ሪፎርም መግባታቸውንም አስረድተዋል።

የጋሞ ዞን ሕዝብ ምክር ቤት ሴቶች፣ ወጣቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ዳንኤል ዳርዛ በበኩላቸው በሴቶችና ሕፃናት ላይ ጥቃት የሚፈጽሙ አካላትን መከላከል ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ነው ብለዋል።

አቶ ዳንኤል አክለውም እንዲህ ዓይነት ድርጊቶችን በተሳሳተ መንገድ በሽምግልና ለመጨረስ የሚሞክሩ አካላት ከድርግታቸው መቆጠብ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የብርብር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አብርሃም አይካ በሰጡት አስተያየትም በተለያዩ ስልቶች በሴቶችና ሕፃናት ላይ የሚፈፀመውን ወንጀል ለመቀነስም ሆነ ለመከላከል እያንዳንዱ ግለሰብ በኃላፊነት መስራት እንደሚገባ ገልፀው መንግስት የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያደርገውን ጥረት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

በሴቶችና ሕፃናት ላይ የሚደርስ ወንጀል ለመከላከል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰሩ የገለፁት ተሳታፊዎቹ ጥቃት ደርሶባቸው በፍትህ ሂደት ላይ የሚከሰቱ እንግልቶችንም ማስቀረት ይገባል ብለዋል።

በትምህርት ቤቶችም በስርዓተ ፆታና በስነ-ምግባር ዙሪያ የሚሰሩ ክበባት መጠናከር እንዳለባቸው ተጠይቋል።

በሐይማኖት ተቋማት ግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶች ቢሰጡ ውጤት እንደማያመጣ ተጠቁሟል።

በመድረኩ ከጋሞ ዞን፣ ከደቡብ ዕዝ መከላከያ እና ከብርብር ከተማ አስተዳደር የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

 #‎የጋሞ_ዞን_ሴቶችና_ህፃናት_ጉዳይ_መምሪያ እና   "  " በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀውን የስልጠና ሠነድ ለሁሉም መንግስት ሠራተኛው ስልጠና ሰጠ።‎@@@@@@@@@@@@@@@@@@@‎መስከረም ...
02/10/2025

#‎የጋሞ_ዞን_ሴቶችና_ህፃናት_ጉዳይ_መምሪያ እና " " በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀውን የስልጠና ሠነድ ለሁሉም መንግስት ሠራተኛው ስልጠና ሰጠ።
‎@@@@@@@@@@@@@@@@@@@

‎መስከረም 22/2018 ዓ/ም(አርባ ምንጭ)

‎ ለማድረግ " " በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፋዊና ሀገር አቀፋዊ ጉዳይ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ የተዘጋጀውን የስልጠና ሠነድ መድረክ አካሂዷል።

‎መድረኩን መሩት እና ፥ " " በሚሉ ሁኔታዎችን በመረዳት ሀገራችንን የአለም ተምሳሌት ሃገር ለማድረግ በትኩረት ልንሠራ ይገባል ብለዋል።

#የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ሁሉም ዜጋ እና መንግስት ሠራተኛው የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባና የባንዳና የባዳ አስተሳሰብን በማስወገድ ለቀጣይ ለውጥ እየተጋን ኢትዮጵያን ወደተሻለ ሀገረር ግንባታ ላይ የበኩላችንን ሚና መወጣት እንዳለብን አስገንዝበዋል።

‎ #ሁሉም ዜጋ እና ሁሉም መንግስት ሠራተኛው በወቅታዊ ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታ ላይ በጋራ መተባበርና ለጋራ ዓላማ መሠለፍ እንዳለባቸው የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫ ተደርጎ መወሰድ እንዳለበት አሳስበዋል።

የጋሞ ዞን ሴቶችና ሕፃናት ጉዳይ መምሪያ በጨንቻ ማረሚያ ተቋም ለሚገኙ ሴቶችና ሕፃናት የተለያዩ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገአርባ ምንጭ፦ መስከረም  15/2018 ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሚዩኒኬሽንየጋ...
27/09/2025

የጋሞ ዞን ሴቶችና ሕፃናት ጉዳይ መምሪያ በጨንቻ ማረሚያ ተቋም ለሚገኙ ሴቶችና ሕፃናት የተለያዩ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ

አርባ ምንጭ፦ መስከረም 15/2018 ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሚዩኒኬሽን

የጋሞ ዞን ሴቶችና ሕፃናት ጉዳይ መምሪያ በጨንቻ ማረሚያ ተቋም ለሚገኙ ሴቶችና ሕፃናት የተለያዩ አልባሳትና የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርገዋል።

በስፍራው ተገኝተው መልዕክት በማስተላለፍ ስጦታውን ያበረከቱት የሴቶችና ሕፃናት ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ሕሩት ማሞ ተቋሟቸው በክረምት ወራት የተለያዩ የበጎ ተግባራት ሲያከናውን መሰንበቱን አውስተው በማረሚያ ተቋም የሚገኙ ሴቶችና ሕፃናት ትምሕርት እንዲያገኙና ንጽሕናቸውን እንዲጠብቁ ድጋፍ መደረጉን አብራርተዋል።

ከሁለት መቶ ሃምሳ ሺ ብር በላይ ወጪ የወጣበት የሕፃናት ወተት፣ አልባሳትና የትምህርት ቁሳቁስ ይዘው እንደተገኙ የገለፁት ወ/ሮ ሕሩት በማረሚያው የሴት ታራሚዎች ማረፊያ ተዟዙሮ በመመልከት የተሻለ መሆኑን ጠቁመው የታራሚ አያያዝ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

የጨንቻ ማረሚያ ተቋም አዛዥ ምክትል ኮምሽነር አጥናፉ አሰፋ ድጋፉን በተቀበሉበት ወቅት የጋሞ ዞን ሴቶች ሕፃናት ጉዳይ መምሪያ የታራሚዎችን የቁሳቁስ ችግር ለመፍታት በየጊዜው ለሚያደርገው ድጋፍ አመስግነው፤ ለሴት ታራሚዎች ምቹ ማረፊያ የማዘጋጀት ሂደት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን አብራርተዋል።

በስፍራው የጋሞ ዞን ሴቶች ሕፃናት መምሪያ ምክትልና የየሴቶች ዘርፍ ኃላፊ ምህረት ኩንታ፣ የማረሚያ ፖሊስ አባላትና የአከባቢው ሽማግሌዎች ተገኝተዋል።

 ...ዮ...የጋሞ ማስቃላ!!
23/09/2025

...ዮ...የጋሞ ማስቃላ!!

የጋሞ ዞን ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ   እንኳን ለጋሞ ህዝቦች ዘመን መለወጫ 'የዮ- ማስቃላ' በዓል በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን  መልዕክት አስተላልፈዋል!~~~~~~~~~~~~~~~~...
23/09/2025

የጋሞ ዞን ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ እንኳን ለጋሞ ህዝቦች ዘመን መለወጫ 'የዮ- ማስቃላ' በዓል በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን መልዕክት አስተላልፈዋል!
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ቀን፦ ‎‎12/2018 ዓ.ም አርባምንጭ

‎ወ/ሮ ህሩት እንዳሉት የጋሞ ዮ...ማስቃላ ዘመን መለወጫ በዓል የፍቅር፣ የሠላም፣ የአንድነትና የመተሳሰብ መገለጫ ለሆነው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

‎ለጋሞ ዞን ህዝቦች ዘመን መለወጫ ዮ...ዮ... ማስቃላ በዓል በጋሞዎች ዘንድ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠውና የህዝቡን ባህል፣ ወግ፣ እሴትና ልማድ ከፍ አድርጎ የሚያሳይ ክዋኔ ነዉ፡፡

‎ዮ...ማስቃላ ከትውልድ ትውልድ ሲተላለፍ የመጣ የብሔሩ ማንነት መገለጫ የሆነው በዓሉ የአሮጌው አመት ማብቂያ እና የአዲሱ አመት መሸጋገሪያ ነው ።

‎የጋሞ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ ለሰው ልጆች ብቻም ሳይሆን ለእንስሳት እና ለአዕዋፋት ጭምር የደስታ በዓል ነው።

‎በዓሉ ህብረ ብሄራዊነት የሚዘከርበት በመሆኑ ባህሉ እንዲጎለብት መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።

‎ዞናችን የሰላም አምባሳደርና በፈጣን እድገት ላይ የሚገኝ የተፈጥሮ ፀጋ ባለቤት፣ የቱሪዝም መዳረሻ፣ የቱሪስቶች ማረፊያ ነው።

‎በአዲሱ ዘመን አንድነትንና አብሮነትን በማጠናከር የዞኑን ሰላም በማስጠበቅና ልማቱን በማሳለጥ ወደ ብልጽግና የተጀመረውን ጉዞ በጋራ በመሆን ማፍጠን ያስፈልጋል።

‎ዮ...ዮ...ማስቃላ በተለያዩ ስፍራዎች ተራርቀው የሚገኙ የቤተሰብ አባላት፣ ዘመድ አዝማድና በተለያዩ ማህበራዊ መስተጋብሮች የተጣመሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከቤተሰብ ጋር በመሆን በጋራ የሚያከብሩት የአብሮነትና የአንድነት ማሣያ በዓል ነው።

‎በመሆኑም በተለያየ ምክንያት የተጣሉ ታርቀው፣ የተራራቁ ዘመድ አዝማድ እና ወዳጆች ተሰባስበው፣ ያዘኑት ሀዘናቸውን ትተው፣ ያለው ለሌላው አካፍሎና አቅመ ደካማ ወገኖቻችን በማሰብ በዓሉን በማክበር አብሮነታችንን በማጎልበት የህዝብ ለህዝብ ግንኙነታችንን ይበልጥ ልናጠናክር ይገባል።

ኃላፊዋ በድጋሚ እንኳን ለጋሞ ህዝቦች ዘመን መለወጫ 'ዮ...ዮ...ማስቃላ' በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ አደረሰን ብለዋል!!

ዮ...ዮ...ዮ ...ማስቃላ!
Yoo..yoo..Habba Masqala!



ለቅርብና ሩቅ ጠላቶች ኢትዮጵያውያን የማይሞት ስም እንጂ የማይሞት አካል የለንም -  ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብልጽግና የ...
09/09/2025

ለቅርብና ሩቅ ጠላቶች ኢትዮጵያውያን የማይሞት ስም እንጂ የማይሞት አካል የለንም - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብልጽግና የማይሳካ ለሚመስላቸው የቅርብና ሩቅ ጠላቶች እኛ ኢትዮጵያውያን የማይሞት ስም እንጂ የማይሞት አካል የለንም አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፡፡

ዳግማዊ ዓድዋና ኢትዮጵያውያን ሕብረ ብሔራዊነት መገለጫ የሆነው ታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ የምረቃ ሥነ ሥርዓት በጉባ እየተካሄደ ነው፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት የኢትዮጵያን ስኬት ለሚያደናቅፉ የቅርብና ሩቅ ጠላቶች ባስተላለፉት መልዕክት ÷ እኛ ኢትዮጵያውያን የማይሞት ስም እንጂ የማይሞት አካል የለንም ብለዋል፡፡

እኛ ኢትዮጵያውያን አካላችን ሞቶ የማይሞት ስም ለማስቀረት የማይሞት አሻራ ለማኖር የምንተጋ ሕዝቦች ነን ሲሉም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

ስለሆነም ከእኛ ጋር መጋጨት ሳይሆን መስማማት ብቻ ነው የሚያዋጣው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ÷ ምክንያቱም ለሺህ ዘመናት የሞከሩን አንዴም አልተሳካላቸውም ብለዋል፡፡

ከእንግዲህ በኋላ የኢትዮጵያ ብልጽግና እውን በመሆኑ ኢትዮጵያ ዳግም ዓድዋን ለጥቁር ሕዝቦች ደጋግማ ማሳየቷ አይቀሬ ነው ፤መላው የጥቁር ሕዝብም ለመበልጸግ በትብብር እንዲሰራ ጠይቀዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ኢትዮጵያን አከብረው ለተገኙ እንግዶችም ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በመላኩ ገድፍ

 :-
03/09/2025

:-

"ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር በተሻገረ ህልም በላቀ ትጋት አስተማማኝ ነገን መስራት" በሚል መሪ ቃል ገረሴ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ መድረክ...
01/09/2025

"ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር በተሻገረ ህልም በላቀ ትጋት አስተማማኝ ነገን መስራት" በሚል መሪ ቃል ገረሴ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ መድረክ ማካሄድ ጀሚረዋል።

አርባምንጭ፡ ነሐሴ 26/2017 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ )

"ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር በተሻገረ ህልም በላቀ ትጋት አስተማማኝ ነገን መስራት" በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የግምገማ ነክ መድረክ ለሁለት ተከታታይ ቀናት በፓርቲ ዲስፕሊን እየተመራ እንደሚካሄድ ተገልፁዋል።

በዚህም መድረክ የጋሞ ዞን ሴቶችና ህፃናት መምሪያ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ህሩት ማም፣ የገረሴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ኤርምያስ እሸቱ፣የገረሴ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ዋና ተጠሪና የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አማሆ አባይነህ፣የብልጽግና ፓርት ቅ/ ጽ/ቤት የመንግስት ሪዳት ተጠሪና የፖለቲካና የህዝብ ግንኘነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ታዬን ጨምሮ ለሎች የከተማ አስተዳደር ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የመድረኩን ዓላማ እትዮጵያ ከትላንትና እንደት ነበረች ዛረስ ምን ደረጃ ላይ ናት ነገንስ ሚን እጣ ፈንታ ይጠብቃታል በሚል ዋና ዋና ጉዳዮችን አስመልክተው ከላይ እሰከ ታችኛው መዋቅር ድረስ በተዘጋጁ ሰነዶች ዙሪያ ውይይት የሚካሄድ መሆኑን የገረሴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ኤርምያስ እሸቱ ገልፀዋል።

በዚህም የተገኙ የዕለቱ ክቡር እንግዳ ክብረት ወ/ሮ ህሩት ማሞ ፖለቲካ ሀገራዊ ዓላማን እና ብሔራዊ ጥቅምን ከማስጠበቅ ጋር የተቆራኘ መሆኑን ገልፀው ይህም ከተናጠል ይልቅ በጋራ ጥቅምና ለውጥ ላይ የተመሠረተ ሆነው የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህ መሠረት የተዘጋጁ ሰነዶች ቀርበው ውይይት እንደሚደረግም ይጠበቃል።



በሀገሪቱ በሁሉም ዘርፎች እየተመዘገበ ላለው ውጤት የሴቶች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸበጋሞ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2018 ዕቅድ ...
26/08/2025

በሀገሪቱ በሁሉም ዘርፎች እየተመዘገበ ላለው ውጤት የሴቶች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ

በጋሞ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2018 ዕቅድ በተመለከተ የምክክር መድረክ በዛሬው ዕለት አካሂዷል።

አርባምንጭ፦ ነሐሴ 20/2017 ዓ.ም

በመደረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የጋሞ ዞን ረዳት የመንግስት ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተመስገን ኢዩኤል ሀገሪቱ በሁሉም ዘርፎች በምታስመዘግበው ውጤት የሴቶች ሚና የላቀ መሆኑን ተናግረዋል።

በየዘርፉ ሴቶችን ይበልጥ ተጠቃሚ ከማድረግ አንፃርም ብልጽግና ፓርቲ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አቶ ተመስገን ጠቁመዋል።

በሴቶች ክንፍ በርካታ ተግባራት ከተለመደው አሠራር ወጣ ባለ መልኩ በመከናወናቸው በግለ ሰብም ሆነ በሀገር ደረጃ ትርጉም ያለው ለውጥ እየተመዘገበ እንደሚገኝ የገለጹት አቶ ተመስገን በቀጣይም የመንግስትና የፓርቲ ተልዕኮዎችን በስኬት ለማጠናቀቅ ለአደረጃጀቶች ጥንካሬና ለመረጃ ጥራት ጥራት ልዩ ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤና የክንፉ አስተባባሪ ወ/ሪት ዓለሚቱ ዮሴፍ በበኩላቸው ብልጽግና ለጠንካራ ፖሊቲካ ፓርቲ ጠንካራ አደረጃጀቶች ያስፈልጋሉ በሚል እሳቤ ሴቶችን የትግል ማዕከል አድርጎ የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ውጤቶችን እያስመዘገበ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ሴቶች በኢኮኖሚያዊ፣ በማህበራዊና በፖሊቲካዊ ዘርፎች ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ እንደሚገኙ የተናገሩት ወ/ሪት ዓለሚቱ እንደ እኛ ዞንም ሆነ በሀገር ደረጃ በውሳኔ ሰጪ ቦታዎች ላይ ሴቶች ያላቸው ተሳትፎ እያደገ መምጣቱንም ጠቁመዋል።

በቀጣይም በሁሉም ዘርፎች ሴቶች የሚያደርጉት ተሳትፎና ተጠቃሚነት አሁን ከደረሰበት ይበልጥ እንዲያድግ አደረጃጀቶችን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ ወ/ሪት ዓለሚቱ አሳስበዋል።

በመድረኩ በዞኑ ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት የ2017 ዓ.ም ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ በጽ/ቤቱ ኃላፊ ተወካይ በወ/ሮ ምስራቅ ታንጋ ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል።

በቀረበው ሪፖርትም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት እንደ ክንፍ በጥንካሬና በጉድለት የተገመገሙ በርካታ ጉዳዮች በዝርዝር የተነሱ ሲሆን በቀጣይም ሊሰሩ የታቀዱ ጉዳዮች ቀርበዋል።

በጥንካሬ ከተነሱ ጉዳዮች መካከልም በሴቶች ተሳትፎ በዞኑ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ፣ በፖለቲካዊ እንዲሁም በበጎ ተግባራት መስኮች የተመዘገቡ ውጤቶች ተገልጸዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎችም ሴቶችን በተመለከተ ከቀደሙት ጊዜያት በአሁኑ ወቅት በሁሉም ዘርፎች የተሻለ ለውጥ መኖሩን ተናግረዋል።

በተጨማሪም ከበጀት አመዳደብ፣ ምቹ ሁኔታ ለሴቶች ከመፍጠር፣ ብድር ከማመቻቸት እና ከመሳሰሉት አንጻር አሁንም በየመዋቅሩ ለሴቶች ትኩረት እንደሚያስፈልግ ተሳታፊዎች ጠቁመዋል።

በመድረኩ ከሁሉም መዋቅሮች የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊዎችና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት የተገኙ ሲሆን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ መዋቅሮችም የዕውቅና ስነ ሥርዓት ተከናውኗል።

በዚህ መሠረትም ቁጫ አልፋ፣ ምዕራብ ዓባያና ቁጫ ወረዳዎች ከ1ኛ እስከ 3ኛ በመውጣት ዋንጫ የተሸለሙ ሲሆን በመጨረሻም መዋቅሮች ከዞኑ ጋር የግብ ስምምነት በመፈራረም መድረኩ ተጠናቋል።

"በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ " በሚል መሪ ሀሳብ በአርባምንጭ  ዙርያ ወረዳ በጫኖ  ጫልባ ቀበሌ የደም ልገሳ እየተካሄደ ነው።አርባምንጭ፦ ነሐሴ 15/2017 ዓ.ም ‎የጋሞ ዞን ሴቶች...
21/08/2025

"በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ " በሚል መሪ ሀሳብ በአርባምንጭ ዙርያ ወረዳ በጫኖ ጫልባ ቀበሌ የደም ልገሳ እየተካሄደ ነው።

አርባምንጭ፦ ነሐሴ 15/2017 ዓ.ም

‎የጋሞ ዞን ሴቶችና ህጻናት መምሪያ ኃላፊ #ወ/ሮ_ሂሩት_ማሞ በተገኙበት በአርባምንጭ ዙርያ ወረዳ የጫኖ ጫልባ ቀበሌ የደም ልገሳ መረሃ ግብር እየተካሄደ ይገኛል።

‎በዚህም በደም ዕጥረት ለህመምና ለሞት የሚዳረጉ እናቶችን፣ ህጻናትንና ለጉዳቱ ተጋላጭ የሆኑ ወገኖችን ለመርዳት የደም ልገሳ መረሐ ግብር እተከናወነ ይገኛል።

‎የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ዘርፍ አካል የሆነው የደም ልገሳ መረሃ ግብር በዞኑ በሁሉም ወረዳች 2017 ዓ.ም እየተከናወነ ሲሆን ዋና ዓላማው በደም ዕጥረት የሚቸገሩ እናቶችንና ወገኖችን ለመርዳት ያለመ መሆኑም ተመላክቷል።

‎በደም ልገሳ መረሐ ግብሩ ላይ የጋሞ ዞን ሴቶችና ህጻናት መምሪያ ኃላፊ #ወ/ሮ_ሂሩት_ማሞን ጨምሮ ምክትል ኋላፊ ፣ ደጋፊ አመራሮች ፣ የጫኖ ጫልባ ቀበሌ፣ ወጣቶች፣ ሴቶች የቀበሌ አመራር እና ጤና ባለሞያዎች ለግሰዋል ።

የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የህብረተሰቡን ማህበራዊ ችግር ከማቃለል ባለፈ የእርስበእርስ ትስስርን እንደሚያጠናክር  ተገለፀአርባምንጭ ፣ ነሐሴ  13 /2017 ዓ.ምየጋሞ ዞን ብልጽግና  ፖርቲ ሴቶ...
19/08/2025

የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የህብረተሰቡን ማህበራዊ ችግር ከማቃለል ባለፈ የእርስበእርስ ትስስርን እንደሚያጠናክር ተገለፀ

አርባምንጭ ፣ ነሐሴ 13 /2017 ዓ.ም

የጋሞ ዞን ብልጽግና ፖርቲ ሴቶች ክንፍ" የወሰን ተሻጋሪ በጎ ተግባር ለህዝቦች ጠንካራ ትስስር" በሚል መሪ ሀሳብ ወንድም ወደ ሆነው ወላይታ ዞን ለክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ተግባር ወደ ወላይታ ሶዶ በመጓዝ ላይ ይገኛሉ።

በዞኑ ዋና አፈ ጉባኤ እና በክንፉ ሰብሳቢ ክብርት አለሚቱ ዩሴፍ የተመሩ የጋሞ ዞን ብልጽግና ፖርቲ ሴቶች ክንፍ የወሰን ተሻጋሪ በጎ ተግባር ለህዝቦች ጠንካራ ትስስር" በሚል መሪ ሀሳብ ወንድም ወደ ሆነው ወላይታ ዞን ለክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ተግባ በመጓዝ ላይ ይገኛሉ።

በጉዞው የዞን ብልጽግና ፖርቲ ሴቶች ክንፍ ጽ/ቤትና የሁሉም ወረዳ ብልጽግና ፖርቲ ሴቶች ክንፍ ጽ/ቤትና ኃላፊዎች ታድመዋል።

Address

Arba Mintch

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Zone women and children affairs department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Gamo Zone women and children affairs department:

Share