Arba Minch Zuria Wereda Government Communication Affairs Office

Arba Minch Zuria Wereda Government Communication Affairs Office ArbaMinch Zuria Wereda Gov.t Communication Affairs Office
(1)

የአከባቢያቸውን ሠላም እና ፀጥታ ለማስከበር ሲሰለጥኑ የነበሩ የሚሊሺያ አባላት ተመረቁ።በአርባ  ምንጭ  ዙሪያ  ወረዳ  ጋንታ አፈዜ ቀበሌ የአከባቢያቸውን  ሠላም እና ፀጥታ ለማስከበር መሠረ...
03/06/2026

የአከባቢያቸውን ሠላም እና ፀጥታ ለማስከበር ሲሰለጥኑ የነበሩ የሚሊሺያ አባላት ተመረቁ።

በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ጋንታ አፈዜ ቀበሌ የአከባቢያቸውን ሠላም እና ፀጥታ ለማስከበር መሠረታዊ የውትድርና ጥበብ የተከታተሉ የሚሊሺያ አባላት ስልጠናቸውን አጠናቀው ከሰሞኑን ለምረቃ በቅተዋል።

በምረቃው ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት አቶ ሎቴ ሎንኬ የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ውሃ ኢነርጂ ጽ/ቤት ኃላፊ፣ አቶ ስንታየሁ ሰማዬ የወረዳው ሚሊሻ ጽ/ቤት ኃላፊ የአከባቢው ማህበረሰብ ታድመዋል።

ስልጠናውን ተከታትለው የተመረቁ የሚሊሻ አባለት የአከባቢውን ሠላም እና ፀጥታ በመጠበቅ ወንጀልን ቀድሞ በመከላከል የተሰጣቸውን ኃላፊነት እንድወጡ እና ከመንግሥት ጎን በመሆንና የህዝብን ሠላም በንቃት በመከታተል መስራት እንደሚገባቸው ተገልጿል።

ሰባተኛው ሀገራዊ የምርጫ ሂደትን ሆን ብሎ በማወክና በማስተጓጎል ክስ የቀረበበት ግለሰብ በ1ዓመት እስር እና የገንዘብ መቀጮ ቅጣት ተወሰነበት።አርባ ምንጭ፦ ግንቦት 25/2018 ዓ.ም (የአር...
02/06/2026

ሰባተኛው ሀገራዊ የምርጫ ሂደትን ሆን ብሎ በማወክና በማስተጓጎል ክስ የቀረበበት ግለሰብ በ1ዓመት እስር እና የገንዘብ መቀጮ ቅጣት ተወሰነበት።

አርባ ምንጭ፦ ግንቦት 25/2018 ዓ.ም (የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ጽ/ቤት)፦

በጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ዘይሴ ልዩ ምርጫ ክልል ሰባተኛው ሀገራዊ የምርጫ ሂደትን ሆን ብሎ በማወክና በማስተጓጎል ክስ የቀረበበት ግለሰብ በ1ዓመት እስር እና 30 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ቅጣት ተወስኖበታል።

ተከሳሽ ኤፌሶን እዮብ ጎሹ አድራሻ ዘይሴ አልጎ ቀበሌ ልዩ ስሙ ዱጎ ሠፈር ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በተቋቋመው የምርጫ ጣቢያ የኢፌዴሪ ወንጀል ህግ አንቀፅ 466 (1) የኢትዮጵያ የምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና አዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀፅ 157(2) ለ የተደነገገውን በመተላለፍ
የምርጫ ሂደትን በማዎክና በማደናቀፍ በሚል ከምርጫ ጋር በተያያዘ የሚቀርቡ አቤቱታዎችንና ክርክሮችን ለመፍታት በወረዳው በተቋቋመው ጊዜያዊ ችሎቶች ክስ ቀርቦበታል።

ክሱ የቀረበለት የወረደው ፍርድ ቤትም የዐቃቤ ህግ ምስክሮችን ቃል በማድመጥ፣ ተከሳሽ እንዲከላከል ዕድል ቢሰጠውም መከላከያ ማስረጃ የለኝም በማለቱ በቀረበበት ክስ ጥፋተኛ ነው ሲል በ1ዓመት እስር እና 30 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ውሳኔ አሳልፏል።

በአርባምንጭ ምርጫ ክልል እየተካሄደ ያለው ምርጫ ሰላማዊ መሆኑን አቶ ሰለሞን ሳዴ በምርጫ ክልሉ የኢትዮጵያ ሶሻል ደሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢሶዴፓ) ለክልል ምክር ቤት ዕጩ ተወዳዳሪ ገለፁ።አርባ ...
01/06/2026

በአርባምንጭ ምርጫ ክልል እየተካሄደ ያለው ምርጫ ሰላማዊ መሆኑን አቶ ሰለሞን ሳዴ በምርጫ ክልሉ የኢትዮጵያ ሶሻል ደሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢሶዴፓ) ለክልል ምክር ቤት ዕጩ ተወዳዳሪ ገለፁ።

አርባ ምንጭ፦ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም (የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ጽ/ቤት)፦

እየተካሄደ በሚገኘው 7ኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ በአርባምንጭ ምርጫ ክልል ላይ ተገኝተው የመራጭነት ድምፅ የሰጡት አቶ ሰለሞን ሳዴ በምርጫ ክልሉ የኢትዮጵያ ሶሻል ደሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢሶዴፓ) የክልል ምክር ቤት ዕጩ ተወዳዳሪ በአርባ ምንጭ ምርጫ ክልል እየተካሄደ ያለው ምርጫ ሰላማዊ መሆኑን ገልፀዋል።

አቶ ሰለሞን በአርባ ምንጭ ምርጫ ክልል በአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ኦቾሎ ላንቴ ቀበሌ ስታዲየም ምርጫ ጣቢያ ተገኝተው የመራጭነት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

ምርጫው ከጅምር ጀምሮ ሰላማዊ መሆኑን ተናግረው ህዝቡም በነፃነት ላመነበት ፓርቲ ድምፅ እየሰጠ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

 በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ የ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በነቃ የህብረተሰብ ተሳትፎ ድምፅ አሰጣጥ እንደቀጠለ ይገኛል።አቶ አያሌው አልታዬ የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ዋና አፈጉባኤ በደጋ ኦ...
01/06/2026



በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ የ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በነቃ የህብረተሰብ ተሳትፎ ድምፅ አሰጣጥ እንደቀጠለ ይገኛል።

አቶ አያሌው አልታዬ የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ዋና አፈጉባኤ በደጋ ኦቾሎ ቀበሌ ላጋሜ ምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፃቸውን በመስጠት የዜግነት መብታቸው ተጠቅመዋል።

የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ተሾመ ድምፃቸውን ሰጡ​ #አርባምንጭ ፣ ግንቦት 24/2018ዓ.ም ​እየተካሄደ በሚገኘው የምርጫ ሂደት የአርባምን...
01/06/2026

የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ተሾመ ድምፃቸውን ሰጡ

​ #አርባምንጭ ፣ ግንቦት 24/2018ዓ.ም ​እየተካሄደ በሚገኘው የምርጫ ሂደት የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ተሾመ በኦቾሎ ላንቴ ቀበሌ ገበያ ምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፅ ሰጥተዋል።

​አቶ ተመስገን ተሾመ በኦቾሎ ላንቴ ቀበሌ ገበያ ምርጫ ጣቢያ በማለዳው በመገኘት ነው የዜግነት መብታቸውን ተጠቅሟል።

​ኃላፊው ድምፃቸውን ከሰጡ በኋላ በሰጡት አስተያየት ምርጫ ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመገንባትና የአገርን የልማት ጉዞ ለማቅናት ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸው፣ ህብረተሰቡ በነቂስ በመውጣት ድምፅ በመስጠት ላይ መሆኑን አድንቀዋል።

​በኦቾሎ ላንቴ ቀበሌ ገበያ ምርጫ ጣቢያ እየተከናወነ የሚገኘው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በሰላማዊ ሁኔታ የቀጠለ ሲሆን፣ ቁጥራቸው ከፍ ያሉ መራጮች በጣቢያው ተገኝተው ድምፃቸውን እየሰጡ እንደሚገኝ ታውቋል።

የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ታደሰ ካርድ በወሰዱበት የምርጫ ጣቢያ በመገኘት ድምጽ ሰጡ።​ዋና አስተዳዳሪው በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ጋንታ ካንቻማ ኦቾሌ ቀበሌ ወጣቶች...
01/06/2026

የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ታደሰ ካርድ በወሰዱበት የምርጫ ጣቢያ በመገኘት ድምጽ ሰጡ።

​ዋና አስተዳዳሪው በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ጋንታ ካንቻማ ኦቾሌ ቀበሌ ወጣቶች ማዕከል ምርጫ ጣቢያ በመገኘት ነው ድምጻቸውን ሰጥተዋል።

​ድምጻቸውን ከሰጡ በኋላ መልዕክት ያስተላለፉት ዋና አስተዳዳሪው በሀገራችን ዘላቂ ሰላምና ዲሞክራሲን ለማረጋገጥ እንዲሁም የህዝብን ድምጽ ያከበረ መንግስት ለመመስረት ብቸኛው መንገድ ምርጫ ብቻ ነው ብለዋል።

አክለውም ይህ የምርጫ ካርድ የእያንዳንዱ ዜጋ የወደፊት እጣ ፈንታ መወሰኛ ሃይል በመሆኑ ካርድ የያዘ ማንኛውም የወረዳው ነዋሪ ይህንን ወርቃማ እድል ሳይጠቀምበት እንዳያልፍና ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በመውጣት የዜግነት ድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

 !​ዘይሴ ልዩ ምርጫ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዕጩ አምባሳደር ገበየሁ ጋንጋ (ዶ/ር) እና የክልል ምክር ቤት ዕጩ ወ/ሮ አለማዝ ሻንቆ ድምፅ ሰጡ​የጋሞ ዞን አርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ...
01/06/2026

!

​ዘይሴ ልዩ ምርጫ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዕጩ አምባሳደር ገበየሁ ጋንጋ (ዶ/ር) እና የክልል ምክር ቤት ዕጩ ወ/ሮ አለማዝ ሻንቆ ድምፅ ሰጡ

​የጋሞ ዞን አርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ዘይሴ ልዩ ምርጫ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዕጩ የሆኑት አምባሳደር ገበየሁ ጋንጋ (ዶ/ር) እና የክልል ምክር ቤት ዕጩዋ ወ/ሮ አለማዝ ሻንቆ በማለዳው ተገኝተው ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

አምባሳደር ገበየሁ ጋንጋ (ዶ/ር) በምርጫ ክልሉ ተገኝተው ድምፅ የሰጡት ህዝባዊና አገራዊ አደራቸውን በታማኝነት ለመወጣት መሆኑን ገልጸዋል ።

​ድምፅ ከሰጡ በኋላ በሰጡት አስተያየት ይህ ምርጫ የህዝባችንን የልማትና የሰላም ፍላጎት በተግባር የምናረጋግጥበት ታሪካዊ መድረክ መሆኑን ጠቅሰው እያንዳንዱ የዜጋ ድምፅ የነገዋን የበለፀገችና የተረጋጋች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚጣል ጠንካራ መሰረት ነው ብለዋል።

የተከበሩ ታገሰ ጫፎ እና ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ድምጽ ሰጡ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ ታገሰ ጫፎ እና ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ...
01/06/2026

የተከበሩ ታገሰ ጫፎ እና ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ድምጽ ሰጡ

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ ታገሰ ጫፎ እና ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በጋሞ ዞን በአርባ ምንጭ ከተማ የመራጭነት ካርዳቸውን በመጣል ድምጽ ሰጥተዋል፡፡

ክቡር አፈ ጉባኤው ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲሁም ክቡር ርዕሰ መስተዳድሩ ለክልሉ ሕዝብ ምክር ቤት በሚወዳደሩበት ምርጫ ክልል፤ በአርባ ምንጭ ከተማ በጫሞ ካምፓስ ምርጫ ጣቢያ በመገኘት ድምጽ የሰጡ ሲሆን፤ በዚህም የዜግነት መብታቸውን ተጠቅመው ታላቅ ሀገራዊ ሃለፊነት መወጣት ችለዋል፡፡

በተጨማሪም የተከበሩ አቶ ብርሃኑ ዘውዴ የክልሉ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ እንዲሁም የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ (ዶ/ር)፤ ለክልሉ ሕዝብ ምክር ቤት በሚወዳደሩበት በዚሁ ምርጫ ክልል፤ በጫሞ ካምፓስ ምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምጽ በመስጠት የዚህ ታሪካዊ ሁነት አካል መሆን ችለዋል፡፡

በታሪካዊው የዛሬው 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ 80 የግል ተወዳዳሪዎችን ጨምሮ የ42 የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች፤ በአጠቃላይ 10 ሺህ 4 መቶ 38 ዕጩ ተወዳዳሪዎች የሚወዳደሩ ሲሆን፤ ሀገሩን ያስቀደመው መራጩ ሕዝብ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች በምገኙ ምርጫ ጣቢያዎች ከንጋት ቀድሞ ድምጽ በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡

በምርጫው ከሃምሳ አራት ሚሊዮን በላይ (54,057,861) ዜጎች የመራጭነት ካርድ ወስደው በድምፃቸው መፃይ የሀገራቸውን ኢጣ ፈንታ ለመወሰን ወደየምርጫ ጣቢያዎቻቸው በመትመም ላይ ሲሆኑ፤ ከማለዳው 12፡00 ሰዓት አስከ ምሽቱ 12፡00 ሰዓት በሚካሄድው ምርጫ በድምጻቸው ታሪክ ይሰራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

#ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!

#ኢትዮጵያ በድምጻችን ታሸንፋለች!

በሂሳብ መዝገብ አያያዝ ፣ በመረጃ አደረጃጀትና በአመታዊ ሂሳብ ሪፖርት አቀራረብ ላይ በግብር ከፋዩ ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ማረም የሚያስችል ስልጠና ተሰጠ።አርባ ምንጭ፦ ግንቦት 20/201...
28/05/2026

በሂሳብ መዝገብ አያያዝ ፣ በመረጃ አደረጃጀትና በአመታዊ ሂሳብ ሪፖርት አቀራረብ ላይ በግብር ከፋዩ ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ማረም የሚያስችል ስልጠና ተሰጠ።

አርባ ምንጭ፦ ግንቦት 20/2018 ዓ.ም (የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ጽ/ቤት)፦

የአርባ ምንጭ ዙርያ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ከጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ ጋር በጋራ በመሆን በወረዳው ለሚገኙ ደረጃ "ሀ" ግብር ከፋዮች የሂሳብ መዝገብ አያያዝ፣ አስተዳደራዊና የወንጀል ቅጣቶች ላይ ያተኮረ የክህሎት ስልጠና መስጠቱን አቶ ገነቱ ቡናቤ የወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ ገልፀዋል።

አቶ ገነቱ አክለውም በንግድ ዘርፍ የተሰማሩ ግብር ከፋዮች ላይ በተደረገው ዳሰሳ ጥናት ክፍተት ያለባቸውን ቦታዎች በመለየት ስልጠናው መዘጋጀቱን ገልጸዋል።

ስልጠናውን ከሰጡት መካከል የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ የታክስ ትምህርትና ድጋፍ ባለሙያ አቶ የማነ ተክሉና በመምሪያው የታክስ ትምህርትና ድጋፍ ባለሙያ አቶ ብርሀኑ ተስፋዬ ስልጠናው ግብር ከፋዩ በግብር ህጉ መሠረት የራሱን የንግድ ስራ በአግባቡ ለመምራት ለመስራትና ለመቆጣጠር ከማስቻሉም ባሻገር ፍትሀዊ የሆነውን ግብር በአግባቡ ለመክፈል ያስችላል ብለዋል።

ለግብር ከፋዩ በየወቅቱ መሠል ስልጠናዎች ሊሰጡ እንደሚገባ ገልጸው በተለይ በሂሳብ መዝገብ አያያዝ፣ በመረጃ አደረጃጀትና በአመታዊ ሂሳብ ሪፖርት አቀራረብ ላይ ግብር ከፋዩ ላይ ክፍተቶች እንደሚስተዋሉና ስልጠናው ይህን የሚቀርፍ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

በስልጠናው ማጠቃለያ ለሰልጣኝ የደረጃ ሀ ግብር ከፋዮች የሙከራ ፈተና የሚሰጥ ሲሆን ይህም መደረጉ ከስልጠናው ምን ያህል ግንዛቤ እንደጨበጡ ለማወቅና ክፍተቶቻቸውን በመለየት ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል ነው ብለዋል።

የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ የታክስ ስርአት ዳይሮክተሬት የታክስ ስጋት ስራ አመራርና የትምህርትና ድጋፍ ቡድን መሪ አቶ ሄኖክ ናፋቆ እንዳሉት ስልጠናው ግብር ከፋዩ መሰረታዊ የሂሳብ መዝገብ አያያዝ መርህን ይዞ መስራቱ ከራስ ጥቅም ባሻገር ለመንግስት የሚገባው ገቢ በተገቢው እንዲሰበሰብ የሚይስችል መሆኑን ገልፀዋል።

እንደዚሁም የታክስ ህጉን በመጣስ ከሚከሰቱ አላስፈላጊ ቅጣቶች ግብር ከፋዩ እንዲጠበቅ የሚያስችል በመሆኑ ግብር ከፋዮች የታክስ ህጉን በመጣስ የሚከሰቱ ክፍተቶችን አውቀው ቅድሚያ ተጠንቅቀው እንዲሰሩ የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ነው ብለዋል።

በወረዳው 167 የደረጃ ሀ እና 1453 የደረጃ ለ ግብር ከፋዮች ግብር ከፋዮች መኖራቸውን የሚጠቅሱት አቶ ፍሬው ዘለቀ የጽ/ቤቱ ታክስ ኦፕሬሽን ዳረክቶሬት ግብር ከፋዩ ሁሉንም ተግባር ለሂሳብ ሰራተኛ መጣሉና የሚፈጠሩ ቅጣቶች ጋር ተያይዞ ለቅጣት ሲዳረግ ከመረዳት ይልቅ ቀድሞ ግንዛቤ እንዲኖረው በማሰብ መዘጋጀቱን ጠቅሰዋል።

ከወረዳው የደረጃ "ሀ" ግብር ከፋዮች መካከል በሆቴል ዘርፍ የተሰማሩት አቶ ዝናቡ ከበደና በአታክልትና ፍራፍሬ ንግድ የተሰማሩት ወ/ሮ አዳነች ኤልያስ በጋራ እንዳሉት የክህሎት ስልጠናው መዘጋጀት ከዚህ ቀደም ባለቸው እውቀት ላይ ተጨማሪ እውቀት የሚጨምርላቸው ከመሆኑም ባሻገር ካላስፈላጊ ቅጣት የሚታደጋቸው እንደሆነ ገልጸዋል።

ሌለኞቹ በአታክልትና ፍራፍሬ የተሰማሩት የደረጃ "ሀ" ግብር ከፋዮች አቶ ነጻነት ቀቼ እና ጭንባቼ ጽጌ እንዳሉት ለግብር ከፋዩ የሂሳብ መዝገብ አያያዝና ከቅጣቶች ጋር በተያያዘ ስልጠና ማግኘታቸው ለስራቸው እንደሚያግዛቸውና ባለማወቅ ከሚመጣ መቀጮ የሚታደጋቸው እንደሆነ ተናግረዋል።

Address

Arba Minch'

Telephone

+251916854517

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arba Minch Zuria Wereda Government Communication Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share