Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Arba Minch'
  • Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት Official page of Gamo Zone People's Council Office

የጋሞ ዞን ም/አስተዳዳሪና የሥራና ክሀሎት መምሪያ ኃላፊ የተከበሩ አቶ ሐኪሜ አየለ ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በገረሴ ከተማ ተገኝተው  ድምፅ ሰጡግንቦት 24/2018 ዓ.ም የጋሞ ዞን ም/አስተዳዳ...
01/06/2026

የጋሞ ዞን ም/አስተዳዳሪና የሥራና ክሀሎት መምሪያ ኃላፊ የተከበሩ አቶ ሐኪሜ አየለ ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በገረሴ ከተማ ተገኝተው ድምፅ ሰጡ

ግንቦት 24/2018 ዓ.ም

የጋሞ ዞን ም/አስተዳዳሪና የሥራና ክሀሎት መምሪያ ኃላፊና የክልል ምክር ቤት ዕጩ ተወዳዳሪ የተከበሩ አቶ ሐኪሜ አየለ ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በገረሴ ከተማ ተገኝተው ድምፅ በሰጡበት ወቅት የቦንኬ - ገረሴ ምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ የተወካዮች ምክር ቤት ተወዳዳሪ ፕሮፌሰር ይስሀቅ ከቸሮ፣ የክልል ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ ወ/ሮ አለምነሽ ደመቀ እና ሌሎች አመራሮች በተመዘገቡበት ምርጫ ጣቢያ ድምጽ ሲሰጡ እንዳሉት ሀገራችንን የአፍሪካ ተምሳሌት ያደርጋል ያሉትን ፓርቲ መምረጣቸውንና የምርጫው ሂደት ዲሞክራሲያዊና ፍትሐዊ በሆነ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

01/06/2026

የደቡብ ኢትዮጲያ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ መልዕክት
Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ አለምፀሀይ ጳውሎስ በ 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 09  ምርጫ ጣቢያ መሐዲስ ኮንዶሚኒዬም ድ...
01/06/2026

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ አለምፀሀይ ጳውሎስ በ 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 09 ምርጫ ጣቢያ መሐዲስ ኮንዶሚኒዬም ድምፃቸውን ሰተዋል።

ኢትዮጵያ ትመርጣለች !!!
Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

የብርብር ምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ የፌደራልና የክልል ዕጩዎች ድምፅ ሰጡ።የብርብር ምርጫ ክልል የፌዴራል ዕጩ የሆኑ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ም/ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ...
01/06/2026

የብርብር ምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ የፌደራልና የክልል ዕጩዎች ድምፅ ሰጡ።

የብርብር ምርጫ ክልል የፌዴራል ዕጩ የሆኑ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ም/ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ፍቅርተ አብርሃም: የብርብር ምርጫ ክልል የክልል ዕጩ የሆኑ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊና አጠቃላይ የትምህርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኢሳይያስ እንድሪያስ: የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰበሳቢ የተከበሩ አቶ ዳንኤል ዳርዛ ፣የቦረዳ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ አሸናፊ ሻሌ ፣የዘፍኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መለሰ ማርካን ጨምሮ የቦረዳ ወረዳ እና የዘፍኔ ከተማ አስተዳደር የመንግሥትና የፓርቲ ሥራ ሀላፊዎች ለ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በዘፍኔ ከተማ ድምፅ ሰጥተዋል።
Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

በጋሞ ዞን ብርብር ምርጫ ክልል እና ጌዲቾ ልዩ ምርጫ ክልል ውስጥ በሚገኘው  የብርብር ከተማ አስተዳደር በ20 የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ዜጎች ከማለዳው ጀምሮ በንቃትና በከፍተኛ ተሳትፎ ድምፃቸው...
01/06/2026

በጋሞ ዞን ብርብር ምርጫ ክልል እና ጌዲቾ ልዩ ምርጫ ክልል ውስጥ በሚገኘው የብርብር ከተማ አስተዳደር በ20 የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ዜጎች ከማለዳው ጀምሮ በንቃትና በከፍተኛ ተሳትፎ ድምፃቸውን እየሰጡ ይገኛሉ።

ግንቦት 24/2018 ዓ.ም

ህዝቡ ከማለዳው ጀምሮ በነበረው ቅዝቃዜ ሳይበገር ረጅም ሰልፎችን በመያዝ የራሱን መንግስት ለመምረጥ ያሳየው ቁርጠኝነትና የነቃ ተሳትፎ እያሳየ ነው።

​ይህ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና በስኬታማ መንገድ ተጠናቆ ኢትዮጵያን ወደ ላቀ ሁለንተናዊ ከፍታ እንዲያሻግራት መራጩ ህዝብ እስከ መጨረሻው ሰዓት ድረስ ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት እንዳለበት ጥሪ ቀርቧል።
Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

‎በቁጫ የምርጫ ክልል ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ ቀጥሏል።‎ግንቦት 24/2018 ዓ.ም‎‎የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤና የቁጫ ምርጫ ክልል የብልፅግና ፓርቲ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት...
01/06/2026

‎በቁጫ የምርጫ ክልል ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ ቀጥሏል።

ግንቦት 24/2018 ዓ.ም

‎የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤና የቁጫ ምርጫ ክልል የብልፅግና ፓርቲ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዕጩ ወ/ሪት አለሚቱ ዮሴፍ፣ የብልፅግና ፓርቲ የክልል ምክር ቤት ዕጩ ረ/ፕሮፌሰር ቱማ አየለ እና አቶ ዳንኤል ደሳለኝ በምርጫ ጣቢያው በመገኘት ድምፅ ሰጥተዋል።

‎መራጮቹም ሌሊት ከ10:30 ጀምሮ ሰልፍ ይዘው መጠበቃቸውን ገልፀው ሂደቱ ሰላማዊና መራጩም በነፃነት ድምፁን እየሠጠ መሆኑን ተናግረዋል።

የአርባምንጭ ከተማ ከንቲባ ዶክተር መስፍን መንዛ  ሠላምበር ከተማ አስተዳደር ጎርማ ቀበሌ ኖክ ማደያ ምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፅ ሰጥተዋል፡፡ዕጩዎቹ ምርጫው በሰላማዊ ሁኔታ መጀመሩንና ያለምን...
01/06/2026

የአርባምንጭ ከተማ ከንቲባ ዶክተር መስፍን መንዛ ሠላምበር ከተማ አስተዳደር ጎርማ ቀበሌ ኖክ ማደያ ምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፅ ሰጥተዋል፡፡

ዕጩዎቹ ምርጫው በሰላማዊ ሁኔታ መጀመሩንና ያለምንም ችግር እየቀጠለ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

የኢጋድ ታዛቢዎችም የተገኙበት በአርባምንጭ ምርጫ ክልል ጫሞ ካምፓስ ምርጫ ጣቢያGamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት
01/06/2026

የኢጋድ ታዛቢዎችም የተገኙበት በአርባምንጭ ምርጫ ክልል ጫሞ ካምፓስ ምርጫ ጣቢያ
Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

በካምባ ምርጫ ክልል መራጮች የምርጫ ድምፅ ከማለዳው 12፡00 ሰዓት ጀምሮ መስጠት ተጀምሯልግንቦት 24/2018ዓ/ምበካምባ ምርጫ ክልል በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች መራጮች ከማለዳው 12፡00 ሰዓ...
01/06/2026

በካምባ ምርጫ ክልል መራጮች የምርጫ ድምፅ ከማለዳው 12፡00 ሰዓት ጀምሮ መስጠት ተጀምሯል

ግንቦት 24/2018ዓ/ም

በካምባ ምርጫ ክልል በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች መራጮች ከማለዳው 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ቀድመው በመገኘት ድምጻቸውን እየሰጡ ይገኛሉ።

በዲሞክራሲ ግንባታ ውስጥ እያንዳንዱ ድምፅ ዋጋ ስላለው መራጮች ወደ ምርጫ ጣቢያዎቻቸው በመሄድ እና ድምፃቸውን በመስጠት የሀገራቸውን የወደፊት እጣፈንታ በመወሰን የበኩላቸውን አስተዋፅዖ ማበርከት እንደሚጠበቅባቸው ተገልጿል።

በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ታዛቢዎችና የምርጫ ባለድርሻ አካላት የምርጫ ሂደቱን በቅርበት እየተከታተሉ ያሉ ሲሆን የምርጫ ሂደቱም ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ በሥነ-ሥርዓት እንዲጠናቀቅ በአግባቡ እየተመራ እንደሆነ ከስፍራው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

የተከበሩ ታገሰ ጫፎ እና ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ድምጽ ሰጡ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ ታገሰ ጫፎ እና ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ...
01/06/2026

የተከበሩ ታገሰ ጫፎ እና ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ድምጽ ሰጡ

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ ታገሰ ጫፎ እና ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በጋሞ ዞን በአርባ ምንጭ ከተማ የመራጭነት ካርዳቸውን በመጣል ድምጽ ሰጥተዋል፡፡

ክቡር አፈ ጉባኤው ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲሁም ክቡር ርዕሰ መስተዳድሩ ለክልሉ ሕዝብ ምክር ቤት በሚወዳደሩበት ምርጫ ክልል፤ በአርባ ምንጭ ከተማ በጫሞ ካምፓስ ምርጫ ጣቢያ በመገኘት ድምጽ የሰጡ ሲሆን፤ በዚህም የዜግነት መብታቸውን ተጠቅመው ታላቅ ሀገራዊ ሃለፊነት መወጣት ችለዋል፡፡

በተጨማሪም የተከበሩ አቶ ብርሃኑ ዜውዴ የክልሉ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ እንዲሁም የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ (ዶ/ር)፤ ለክልሉ ሕዝብ ምክር ቤት በሚወዳደሩበት በዚሁ ምርጫ ክልል፤ በጫሞ ካምፓስ ምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምጽ በመስጠት የዚህ ታሪካዊ ሁነት አካል መሆን ችለዋል፡፡

በታሪካዊው የዛሬው 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ 80 የግል ተወዳዳሪዎችን ጨምሮ የ42 የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች፤ በአጠቃላይ 10 ሺህ 4 መቶ 38 ዕጩ ተወዳዳሪዎች የሚወዳደሩ ሲሆን፤ ሀገሩን ያስቀደመው መራጩ ሕዝብ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች በምገኙ ምርጫ ጣቢያዎች ከንጋት ቀድሞ ድምጽ በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡

በምርጫው ከሃምሳ አራት ሚሊዮን በላይ (54,057,861) ዜጎች የመራጭነት ካርድ ወስደው በድምፃቸው መፃይ የሀገራቸውን ኢጣ ፈንታ ለመወሰን ወደየምርጫ ጣቢያዎቻቸው በመትመም ላይ ሲሆኑ፤ ከማለዳው 12፡00 ሰዓት አስከ ምሽቱ 12፡00 ሰዓት በሚካሄድው ምርጫ በድምጻቸው ታሪክ ይሰራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!

ኢትዮጵያ በድምጻችን ታሸንፋለች!
Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

Address

Secha
Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share