Arba Minch City Gov't Communication Affairs Office

Arba Minch City  Gov't Communication Affairs  Office Where ever you are; we have deliver actual information concerning to Arba Minch City.

7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ የህዝቡን የዴሞክራሲ ተሳትፎና የሰላም ባህልን ያረጋገጠ ነው "የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ፌደሬሽን ግንቦት 26/2018 ዓ.ም የክልሉ ወጣቶች ፌዴሬሽን 7ኛው...
03/06/2026

7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ የህዝቡን የዴሞክራሲ ተሳትፎና የሰላም ባህልን ያረጋገጠ ነው "የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ፌደሬሽን

ግንቦት 26/2018 ዓ.ም

የክልሉ ወጣቶች ፌዴሬሽን 7ኛውን ጠቅላላ ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ተሰጥቷል ።

የክልሉ ወጣቶች ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ አማኑኤል ሳሙኤል እንደገለጹት፣ ፌዴሬሽኑ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባገኘው የምርጫ ታዛቢነት ፈቃድ መሰረት ተግባራትን ሲያከናውን እንደነበረ ጠቁመዋል ።

በክልሉ 54 የምርጫ አስተባባሪዎችንና ከ2000 በላይ ታዛቢዎችን በተለያዩ አካባቢዎች በማሰማራት የምርጫውን ሂደት ከቅድመ ዝግጅት እስከ ድምጽ ቆጠራ ድረስ በቅርበት መከታተሉን አስታውቀዋል።

በክልሉ የተካሄደው ምርጫ መራጮች ድምጻቸውን ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መስጠታቸውን የገለፁት ፕሬዝደንቱ ፣ የወጣቶች፣ የሴቶች፣ የአረጋውያን እና የሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች ተሳትፎ የዴሞክራሲ ባህልን የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል።

የክልሉ ወጣቶች ፌደሬሽን ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ምህረቱ ዳና በበኩላቸው የክልሉ ወጣቶች በምርጫ አስፈጻሚነት፣ በታዛቢነት፣ በግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች፣ በመራጭነትና በተመራጭነት ባሳዩት ንቁ ተሳትፎ ለዴሞክራሲ ግንባታ የላቀ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን አስረድተዋል።

ለምርጫው ስኬት የድርሻውን አስተዋጽኦ ላበረከቱት ምስጋናቸውን ያቀረቡት አቶ ምህረቱ ምርጫው የህዝቡን የዴሞክራሲ ተሳትፎና የሰላም ባህልን ያረጋገጠ ስለመሆኑ ጠቁመዋል ።

መላው የህብረተሰብ ክፍል በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩ ሀሰተኛ መረጃዎችን ራሱን በመጠበቅ የምርጫ ቦርድ ውጤቱን ይፋ እስከሚያደርግ ድረስ በትዕግሥት እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርበዋል ።

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አካታችና አሳታፊ ነበር - ኡሁሩ ኬንያታ አርባምንጭ ፣ ግንቦት 26፣ 2018 ዓ/ም  7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አካታችና አሳታፊ ነበር አሉ የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢዎች ...
03/06/2026

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አካታችና አሳታፊ ነበር - ኡሁሩ ኬንያታ

አርባምንጭ ፣ ግንቦት 26፣ 2018 ዓ/ም
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አካታችና አሳታፊ ነበር አሉ የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢዎች መሪ እና የቀድሞ የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ፡፡

ኡሁሩ ኬንያታ ኢትዮጵያ ያካሄደችውን 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ምርጫው አካታችና አሳታፊ እንዲሆን መንግስት ያደረገውን ጥረት አድንቀዋል፡፡

የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን የቅደመ ምርጫ ክንውኖችንና የምርጫ ዝግጅቶችን በተመለከተ ቅኝት ማድረጉን አስታውሰዋል፡፡

የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱን በተመለከተ ከምርጫ ቦርድ ኃላፊዎች፣ ከመንግስት ተቋማት፣ ከተፎካካሪ ፓርቲ አባላት፣ ከሲቪክ ማህበራትና ከተለያዩ የዲፕሎማሲ ማህበረሰብ ጋር ውይይት መደረጉን ገልጸዋል፡፡

በደምፅ መስጫው ዕለት የምርጫ አስፈጻሚዎች መራጮችን በአግባቡ ማስተባበራቸውን ጠቅሰው፥ የጸጥታ አካላት ገለልተኝነታቸውን በጠበቀ መልኩ የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱን ማስፈጸማቸውን አብራርተዋል፡፡

ሕዝቡ ረጃጅም ሰልፎችን በመጠበቅ በትዕግስት ሲመርጥ እንደነበር ገልጸው፥ ኹነቱን የዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ሽፋን መስጠታቸውን ገልጸዋል፡፡

ምርጫው በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት አካታችና አሳታፊ ምርጫ ለማድረግ ያደረገውን ጥረት በማድነቅ፤ በሀገሪቱ ብዝሃነትን ለማረጋገጥና እኩል የፖለቲካ ተሳትፎ እንዲሰፍን ለማድረግ ተጨማሪ ጥረቶችን ማድረግ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

ኅብረቱ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲፈጠር የሚያደርገውን ድጋፍ እና ምክረ ሀሳብ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል፡፡

ኤፍ ኤም ሲ)

"ኡሁሩ ኬንያታ እና ባልደረቦቻቸው ለዲሞክራሲ ግንባታ ሂደታችን ላበረከቱት አገልግሎትና አስተዋጽኦ የላቀ ምስጋናችንን እናቀርባለን" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) *********...
03/06/2026

"ኡሁሩ ኬንያታ እና ባልደረቦቻቸው ለዲሞክራሲ ግንባታ ሂደታችን ላበረከቱት አገልግሎትና አስተዋጽኦ የላቀ ምስጋናችንን እናቀርባለን" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
**************

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልእክት የቀድሞ የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እና የስራ ባልደረቦችን በማግኘቴ ታላቅ ደስታ ይሰማኛል። የተከበሩ ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና 73 አባላት የያዘውን የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ፤ ለዲሞክራሲ ግንባታ ሂደታችን ላበረከቱት አገልግሎትና አስተዋጽኦ የላቀ ምስጋናችንን እናቀርባለን ብለዋል።

‎ዲሞክራሲያዊ ሂደቶች ከአኅጉራችን ነባራዊ ሁኔታና ተሞክሮ ጋር የተጣጣሙ እንዲሆኑ ለማድረግ አፍሪካዊ ተቋማት ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ። የምርጫ ሂደታችንን ለመደገፍ በመላው ሀገሪቱ ታዛቢዎችን በማሰማራት የምርጫ ታዛቢ ልዑኩ ላደረገው ያልተቆጠበ ጥረት እውቅና እና አድናቆት እየሰጠን፣ የምልከታውን የተሟላ ውጤት እንጠብቃለን ሲሉም ነው ጠቅላይ መኒስትሩ የገለፁት።

የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን በኢትዮጵያ 7ኛው አጠቃላይ ምርጫ ላይ የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን ይፋ አደረገግንቦት 26/2018ዓ.ምየምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት (ኢጋድ) የኢትዮጵያ...
03/06/2026

የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን በኢትዮጵያ 7ኛው አጠቃላይ ምርጫ ላይ የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን ይፋ አደረገ

ግንቦት 26/2018ዓ.ም

የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት (ኢጋድ) የኢትዮጵያን 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ ያዘጋጀውን የመጀመሪያ ደረጃ የምርጫ ምልከታ ሪፖርት ይፋ አድርጓል።

ከኢትዮጵያ መንግሥት እና ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደረሰው ጥሪ መሠረት 26 አጭር ጊዜ ታዛቢዎችን ያቀፈ ቡድን በማሰማራት ሂደቱን ሲከታተል የቆየው ተቋሙ፣ በምርጫው የታዩ አስተዳደራዊ እና ቴክኖሎጂያዊ ማሻሻያዎችን አወድሷል።

ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በተካሄደው በዚህ ምርጫ ወቅት የተወሰኑ የፖለቲካ እና የፀጥታ ተግዳሮቶች ማጋጠማቸውን ሪፖርቱ ጠቅሷል።

በዚህም ምክንያት ምርጫው ሊካሄድ ከነበረባቸው 557 የምርጫ ክልሎች ውስጥ በ501ዱ ላይ ብቻ የተከናወነ ሲሆን፣ በአጠቃላይ በ52,044 የክልል እና የከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ምርጫ ጣቢያዎች ድምፅ ተሰጥቷል።

የኢጋድ ታዛቢ ቡድን ባወጣው መግለጫ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮውን ምርጫ በማዘጋጀት እና በማስፈጸም ረገድ ያሳየውን ከፍተኛ አስተዳደራዊ እና ተግባራዊ አቅም አድንቋል።

ቦርዱ በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥም ቢሆን በ501ዱ የምርጫ ክልሎች ውስጥ ወደ 52,000 የሚጠጉ የምርጫ ጣቢያዎችን በተሳካ ሁኔታ ሥራ ላይ ማዋል መቻሉን ቡድኑ በሪፖርቱ አመልክቷል።

በተለይም በምርጫው ሂደት ላይ የተስተዋሉ ዘመናዊ አሠራሮች የኢጋድን አድናቆት አትርፈዋል።

ከእነዚህም መካከል፦

* በጂኦግራፊያዊ መረጃ ሥርዓት (GIS) ላይ የተመሠረተ የምርጫ ጣቢያዎች ካርታ ዝግጅት፣
* የተደባለቀ (ሀይብሪድ) የመራጮች ምዝገባ ሥርዓት አጠቃቀም፣
* በሀገር ውስጥ ለተፈናቀሉ ዜጎች (IDPs) እና ለሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት የተዘረጉ ልዩ የድምፅ አሰጣጥ ማዕቀፎች ይገኙበታል።

እነዚህ አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎች የምርጫ ሂደቱን ለማዘመን፣ ይበልጥ ተደራሽ፣ አካታች እና ቀልጣፋ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውን ታዛቢ ቡድኑ ገልጿል።

በተጨማሪም የመራጮች ግንዛቤን ለማሳደግ በተደረገው ጥረት 169 ድርጅቶች የመራጮች ትምህርት እንዲሰጡ ዕውቅና የተሰጣቸው ሲሆን፣ 114 ያህሉ ደግሞ ለሥራው የሚያስፈልጋቸውን የፋይናንስ ድጋፍ ማግኘታቸው በሪፖርቱ ተመላክቷል።

ኢጋድ ይህ የምርጫ ሂደት በቀጠናው ያለውን ግልጽነትና ዲሞክራሲያዊ ትብብር ለማጠናከር ትልቅ እመርታ መሆኑን አስታውቋል።

#

የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መልዕክት *************የሀገር ሉዓላዊነትና ነጻነት በምልዐት የሚረጋገጠው በጥራት፣ በዓይነት እና በብዛት የኢንዱስትሪ ምርቶችን በራስ ዕውቀ...
03/06/2026

የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መልዕክት
*************

የሀገር ሉዓላዊነትና ነጻነት በምልዐት የሚረጋገጠው በጥራት፣ በዓይነት እና በብዛት የኢንዱስትሪ ምርቶችን በራስ ዕውቀት፣ በራስ ክህሎት እና በራስ ቴክኖሎጂ ማምረት ስንችል ነው፡፡

መንግሥትም በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የታለመውን ዘላቂ ዕድገት እና ተወዳዳሪነት ለማረጋገጥ ፖሊሲዎችን አሻሽሏል፡፡ አሠራሮችን ዘርግቷል፡፡ ማበረታቻዎችን አድርጓል።

የዚህ ሪፎርም አካል የሆነው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄም ፍሬው በግልጽ እየታየ ነው።

የአውሮፓ ኅብረትና አጋር ሀገራት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሒደት አደነቁ ግንቦት 25፣ 2018የአውሮፓ ኅብረት እና አጋር ሀገራት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ...
03/06/2026

የአውሮፓ ኅብረትና አጋር ሀገራት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሒደት አደነቁ

ግንቦት 25፣ 2018
የአውሮፓ ኅብረት እና አጋር ሀገራት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አድንቋል፡፡

ምርጫውን አስመልክቶ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ካደረጉ የኅብረቱ አባል ሀገራትና በኢትዮጵያ የካናዳ፣ የኖርዌይ እና ስዊዘርላንድ ኤምባሲዎች የጋራ መግለጫ አውጥተዋል፡፡

ሀገራቱ በመግለጫቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ እጩዎችና የሲቪል ተቋማት ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲካሄድ ያደረጉትን አስተዋጽኦ አድንቀዋል፡፡

የአፍሪካ ኅብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) በምርጫው ላይ ለነበራቸው የታዛቢነት ሚና እውቅና እንደሚሰጡም ሀገራቱ አረጋግጠዋል፡፡

ኤፍ ኤም ሲ

“ከምርጫው የሀገርን ሰላም፣ ደህንነትና ልማት የሚያረጋግጥ መንግስት እንጠብቃለን”- የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ++++++++++++++  ግንቦት 24  በተካሄደው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በአር...
03/06/2026

“ከምርጫው የሀገርን ሰላም፣ ደህንነትና ልማት የሚያረጋግጥ መንግስት እንጠብቃለን”
- የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች
++++++++++++++

ግንቦት 24 በተካሄደው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በአርባ ምንጭ ከተማ መራጮች ማልደው በምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ድምፃቸውን ሲሰጡ ውለዋል። ከምርጫው የሀገርን ሰላም፣ ደህንነትና ልማት የሚያረጋግጥ መንግስት እንደሚጠብቁ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ያነጋገራቸው የአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪዋ ወይዘሮ ክበቧ አባተ በሰጡት አስተያየት፤ በማለዳው በምርጫ ጣቢያው በመገኘት ያለምንም እንግልት ድምፃቸውን በአግባቡ መስጠታቸውን ገልጸዋል።

በምርጫው ከተሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚጠበቀው ትልቁ ቁምነገር የምርጫውን ውጤት በጸጋ መቀበል መሆኑን ገልጸው፤ እኛም በሰጠነው ድምጽ የምንጠብቀው ምላሽ ለሀገሪቱ ሰላም፣ ዘላቂ ልማትና እድገት ነው ብለዋል።

ለሀገር ልማት፣ ብልጽግና እና እድገት የተሻለ ስራ ይሰራል ያሉትን አካል መምረጣቸውንም ጠቁመዋል።

ሌላኛው የከተማዋ ነዋሪ አቶ በዛብህ ሻዶ በበኩላቸው፤ እንዳሉት፤ "ሀገርን በጥንቃቄ የሚያስተዳድር፣ የሀገርን ደህንነትና ሰላም የሚያስጠብቅ መልካም መንግስት እንጠብቃለን" ብለዋል።

የተሰጣቸውን ዕድል በመጠቀም ድምፅ መስጠታቸውንና ሂደቱ እጅግ በጥሩ ሁኔታ መጠናቀቁን ገልጸዋል።

በምርጫው ዕለት ከሌሊቱ ዘጠኘ ሰዓት ጀምሮ ተሰልፋ ድምጿን እንደሰጠች የገለጸችው የኔነሽ አሻግሬ፣ የምርጫ ውጤት ለሀገሪቱና ለከተማዋ ዕድገት ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብላ እንደምትጠብቅ ተናግራለች።

ከሰላም ባሻገር የምርጫው ውጤት አዲስ የሥራ ዕድሎችንና የልማት አማራጮችን ይዞ እንደሚመጣ ተናግራለች።

በጫሞ ቀበሌ ቁጠባ ምርጫ ጣቢያ የመጀመሪያ መራጭ እንደነበሩ የገለጹልን አቶ ማርቆስ ካንቾ፣ "በሌሊት ተነስቼ በመሰለፍ የመረጥኩበት ለሀገራችንና ለከተማችን ልማትን፣ እድገትንና መልካም አስተዳደርን እንዲመጣ ብዬ ነው።

ከምርጫው ውጤት በኋላም የሚጠብቁት ይህንኑ እንደሆነ ገልጸው፣ “ውጤቱ ምንም ይሁን ምን ሁላችንም እጅ ለእጅ ተያይዘን በጋራ መስራት አለብን” ሲሉም አሳስበዋል።

ሰላም! እንደምን አደራችሁ?ለቀጣይ አምስት ዓመታት የሚመራቸውን መንግሥት ለመምረጥ ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 ቀን ከማለዳ ጀምሮ እስከ ሌሊት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።ዜጎች በየአካባቢው በሚገኙ የ...
03/06/2026

ሰላም! እንደምን አደራችሁ?

ለቀጣይ አምስት ዓመታት የሚመራቸውን መንግሥት ለመምረጥ ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 ቀን ከማለዳ ጀምሮ እስከ ሌሊት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

ዜጎች በየአካባቢው በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት÷ ኢትዮጵያውያን ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና ለሀገረ መንግሥት ምስረታ ያላቸውን ፅኑ ቁርጠኝነት በተግባር ያሳዩበት ሆኖ አልፏል።

በሚሊየን የሚቆጠሩ መራጮች በነቂስ ወጥተው ዝናብና ጸሐይን እንዲሁም ከተለያዩ አካላት የሚነዙ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻዎችንና ዛቻዎችን ሳያዳምጡ በረጃጅም ሰልፎች ተሰልፈው ውሳኔያቸውን አስተላልፈዋል።

በሕመም አልጋ ላይ የነበሩ ከሕመማቸው ጋር እየታገሉ፣ ሐዘን የገጠማቸውም ከሐዘናቸው ተነስተው በመውጣት ለነጋቸው የሚበጀውን ድምፅ የሰጡበት ዕለት ነው ግንቦት 24።

በዚህ ታሪካዊ ሂደት ላይ ለመሳተፍ በሚያስችል ዕድሜ ላይ የሚገኙ ከ54 ሚሊየን በላይ ዜጎች ተመዝግበው ከ10 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎችና 80 የግል ዕጩዎች በተወዳደሩበት ምርጫ ድምጻቸውን በመስጠት ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል።

የምርጫውን ግልጽነት፣ አሳታፊነትና ተዓማኒነት ከፍ ለማድረግ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን÷ ከእነዚህም መካከል ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ ሚና ያላቸውና ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፈቃድ ያገኙ 68 የመገናኛ ብዙኃን ተሰማርተዋል፤ ከእነዚህ ውስጥ 12ቱ የውጭ መገናኛ ብዙኃን ናቸው።

በተጨማሪም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የድምፅ አሰጣጥና የውጤት ቆጠራ ሂደቱን በቅርበት ለመከታተል ከ250 ሺህ በላይ ተወካዮቻቸውን በየምርጫ ጣቢያዎቹ መድበዋል።

በሌላ በኩል የኬንያ ቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመራውና 59 አባላትን የያዘው የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እንዲሁም 26 አባላትን ያሰማራው የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በመሰማራት ሂደቱን በንቃት ታዝበዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ÷ የምርጫው ድምፅ የመስጠት ሂደት በስኬት መጠናቀቁንና በየምርጫ ጣቢያዎቹ የምርጫ ውጤቶችን ለሕዝብ የመለጠፍ ሥራዎች በይፋ መከናወናቸውን አረጋግጠዋል።

ይህም ኢትዮጵያ የራሷን ዕድል ለመወሰን መካሪና ገሳጭ እንደማያስፈልጋት በድጋሚ ያሳየበት ነው።

በድምፅ መስጫው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመራጩ ሕዝብ በላይ የተመራጮች ጉዳይና ኃላፊነት ይበልጥ እንደሚያሳስባቸው መግለጻቸው ይታወሳል።

በመሆኑም ሕዝብ ያሳየውን ፅኑ እምነትና የዴሞክራሲ ፍላጎት ሳይሸረሽር፣ በታማኝነትና በንጹሕ ልብ ማገልገል የነገው መንግሥት ቀዳሚ የቤት ሥራ እንደሚሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አጽንዖት ሰጥተዋል።

የሕዝቡን ሕይወት የሚነካና የሀገሪቱን የነገ ዕጣ ፈንታ የሚወስን እውነተኛ ለውጥ ማምጣት የሚቻለውም ተመራጮች የተጣለባቸውን ታሪካዊ ኃላፊነት በትክክል ተረድተው ሲሰናዱ ብቻ በመሆኑ የኢትዮጵያ ቀጣይ አምስት ዓመታት ጉዞ በዚሁ የተመራጮች የዝግጁነት ሚዛን ላይ የሚያርፍ ይሆናል።

ኢትዮጵያ መርጣለች፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!!

03/06/2026

ኢትዮጲያ መርጣለች

ኢትዮጵያ መርጣለች! አሸናፊ ሆናለች!በትናንትናው ዕለት በመላው ሀገራችን የተካሄደውና ከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ የታየበት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ ሆኖ በመጠናቀቁ ከፍተኛ ደስታ ተሰምቶኛል::...
02/06/2026

ኢትዮጵያ መርጣለች! አሸናፊ ሆናለች!

በትናንትናው ዕለት በመላው ሀገራችን የተካሄደውና ከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ የታየበት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ ሆኖ በመጠናቀቁ ከፍተኛ ደስታ ተሰምቶኛል::

ይህ ኢትዮጵያ ወደ ላቀ የዴሞክራሲ ምዕራፍ ለመሻገር የጀመረችውን ጉዞ የሚያፀና ትልቅ ታሪካዊ ስኬት ነው።

በከተማችን አርባምንጭም አጠቃላይ የምርጫ ሂደቱ ፍፁም ሰላማዊ፣ ነፃ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ ተከናውኗል።

የከተማችን ነዋሪዎች ከማለዳ አንስቶ እስከ ምሽት የሰጡት ድምፅ ለሀገር ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት፤ ለዴሞክራሲ ስርዓት መጎልበት ያለውን የላቀ ግንዛቤ በተግባር ያሳየ ሆኗል።

ለዚህ ታላቅ ስኬት መመዝገብ አንዲት ድምፅ ዋጋ እንዳላት በማመን ከሌሊቱ 10:00 አንስቶ ዝናብና ፀሀይ ሳይበግራችሁ ኃላፊነታችሁን ለተወጣችሁ አባቶች፣ እናቶች፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ አካል ጉዳተኞች በአጠቃላይ ለመላው የከተማችን ሕዝብ ያለኝን ልዩ ክብርና አድናቆት ለመግለጽ እወዳለሁ።

ከዚህ በተጨማሪ የፀጥታ አካላት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የመንግሥት ተቋማት፣ የመገናኛ ብዙኃን፣ የሲቪክ ማኅበራት፣ የሃይማኖት ተቋማት እና ሌሎችም ምርጫው ሰላማዊ እና ስኬታማ እንዲሆን ላበረከታችሁት አስተዋጽኦ ከልብ አመሰግናለሁ።

አይሶጼ ሂሎታ
አርባምንጭ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ
ግንቦት 25/2018 ዓ.ም

Address

Minch District, Middle City
Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arba Minch City Gov't Communication Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Arba Minch City Gov't Communication Affairs Office:

Share