06/06/2026
የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የተሰጠ የሐዘን መግለጫ
. **************
የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በኦሮሚያ ክልል በወልመራ ወረዳ ፍርድ ቤት ክብርት ዳኛ ወርቄ ፈከንሳ በችሎት የዳኝነት ሥራ እየሰሩ ሳሉ በባለጉዳይ በተተኮሰባቸው ጥይት ሕይወታቸው በማለፉ የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እንገልፃለን።
የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት እንዲህ አይነቱ በዳኞች ወይም በሌሎች የፍትሕ ሥርዓት ተዋናዮች ላይ የሚፈጸሙ የኃይል ድርጊቶች የሕግ የበላይነትን ለማዳከም የሚደረጉ ተግባራት እንደሆኑ በማመን በጽኑ እናወግዛለን።
የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለሟች ዳኛ ወርቄ ፈከንሳ ቤተሰቦች፣ የሥራ ባልደረቦች እና ለመላው የፍትሕ ማህበረሰብ መጽናናትን ይመኛል።