02/06/2026
ኢትዮጵያ በአሸናፊነት ተምሳሌት ሀገር ሆነች፤ ዶ/ር አሸናፊ ኦይዳ
ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደዉ ታሪካዊው የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ አሰጣጥ ሂደት እጅግ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ዴሞክራሲያዊ ሂደቱን ጠብቆ በስኬት በመጠናቀቁ የተሰማኝን ልባዊ ደስታ ለመግለፅ እወዳለሁ፡፡
መላው የወረዳችን ህዝቦች በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫ ቀን እና አሁን ደግሞ በድህረ ምርጫ ወቅት ለሀገራችን መፃይ ብሩህ ተስፋ ቀና በመሆን በሚታሳዩት ትጋት እና ፅናት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ጉዟችንን በማፅናት ዳግም አሸናፊ እንድንሆን አስችሎናል።
ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና እጩዎች ህዝብ በነፃነት የሰጠውን ድምፅ እና የገለጸውን ፍላጎት ሁሉም በፀጋ እና በክብር በመቀበል በጋራ በመተባበር ሀገርን ለማሻገር ትልቅ አደራ ተቀብለናል።
የምርጫ አስፈፃሚዎች ገለልተኛ በመሆን የህዝባችን ድምጽ ወደ ስርዓተ መንግስት ለመቀየር ላደረጋችሁት አስተዋጽኦ የላቀ ምስጋና አለኝ።
ዶ/ር አሸናፊ ኦይዳ
የዲታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ