Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ

Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ Disease prevention and control
Maternal and child health
Nutrition
Health care financing

የማህፀን በር ካንሰር ልየታ በጨንቻ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ተደረገ።‎‎አርባ ምንጭ፡- ሰኔ 5/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምርያ ) ‎‎የጨንቻ አጠቃላይ ሆስፒታል የእናቶችና ህፃናት የቅርብ...
12/06/2026

የማህፀን በር ካንሰር ልየታ በጨንቻ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ተደረገ።

‎አርባ ምንጭ፡- ሰኔ 5/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምርያ )

‎የጨንቻ አጠቃላይ ሆስፒታል የእናቶችና ህፃናት የቅርብ ተጠሪ የሆኑት አቶ ታማኝ ቱይላ ማህፀን በር ካንሰር በመውለጃ እድሜ ክልል ያሉ ሁሉም ሴቶች ምርመራ እንዲያደርጉ ይመከራል ዛሬ እዚህ የተገኘነው ሴት የህግ ታራሚዎችን የማህፀን በር ካንሰር ልየታ ለማድረግ ነው ።

‎በተጨማሪ በጊዜ ምርመራ ቢደረግ መዳን የሚችል በሽታ እንደሆነም ገልፀዋል።
‎ስለ ማህፀን በር ካንሰር የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት በባለሞያዎች ተሰቷል።

‎ከሆስፒታል ከተቋሙ ጤና ጣቢያ በተወጣጡ ሴት የህክምና ባለሞያዎች ጋር በመሆን ወደ ልየታ ተገብቷል።

‎ምንጭ፡-የጨንቻ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም።

የዞኑ የድንገተኛ አደጋዎች ክስተት አስተዳደር ስርዓት የድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ ስራዎች ላይ መደበኛ ስብሰባውን አካሄደ፤‎አርባ ምንጭ፡- ሰኔ 5/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምርያ ) ‎...
12/06/2026

የዞኑ የድንገተኛ አደጋዎች ክስተት አስተዳደር ስርዓት የድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ ስራዎች ላይ መደበኛ ስብሰባውን አካሄደ፤

‎አርባ ምንጭ፡- ሰኔ 5/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምርያ )

‎በናዳ ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚሰጠው ሁሉ አቀፍ የጤና አገልግሎት ተጠናክሮ መቀጠሉ ተነግፘል።

‎በጊዚያዊ መጠለያ ለተጠለሉ ወገኖች በተቋቋመው ጊዚያዊ ክሊኒክ የሚሰጠው አገልግሎት በተጠናከረ መልኩ መቀጠሉ በሪፖርት ተመላክቷል። በዚህም 2 ሺህ 034 ሰዎች የህክምና አገልግሎት እንዲሁም 3 መቶ 70 የላቦራቶሪ አገልግሎት አግኝተዋል።

‎ከእናቶች እና ህፃናት ጤና ጋር በተያያዘ 3 መቶ 34 የቤቴሰብ ዕቅድ አገልግሎት፣ 7 የወሊድ አገልግሎት እንዲሁም 2 መቶ 40 ህፃናት መደበኛ የክትባት አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ ተችሏል።

‎ከወባ በሽታ ጋር በተያያዘ በጋርዳ ማርታ፣ በዳራማሎ ወረዳ እንዲሁም በዋጫ ከተማ አስተዳደር የቤት ለቤት የፀረ-ትንኝ ኬሚካል ርጭት በመካሄድ ላይ ይገኛል። የበሽታውን ስርጭት ለመግታት በሁሉም ወባማ ወረዳዎች ተግባሩን በጥብቅ ዲሲፕሊን ህዝባዊ ንቅናቄ በመፍጠር ሊመራ ይገባል ተብሏል።

‎ይህ በእንዲህ እንዳለ ለተጎጂ ወገኖች የህክምና አገልግሎትን ለማሳለጥ ይረዳ ዘንድ መድሃኒት የማቅረብ ሂደቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

‎በግብረ-ሃይሉ ስብሰባው የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሴይፉ ዋናቃ፣ የመምሪያው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ባንጌ ባንጃ፣ የመምሪያው ከፍተኛ ባለሙያዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ሰበር ዜና!!‎‎የጤና ባለሙያዎች እንኳን ደስ አላችሁ!‎‎የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የጤና ባለሙያዎች የሙያ ምዘገባ ፍቃድ በዞን ደረጃ ለመስጠት ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱ የሚታወቅ ...
11/06/2026

ሰበር ዜና!!

‎የጤና ባለሙያዎች እንኳን ደስ አላችሁ!

‎የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የጤና ባለሙያዎች የሙያ ምዘገባ ፍቃድ በዞን ደረጃ ለመስጠት ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱ የሚታወቅ ነው።

‎በመሁኑም የዝግጅት ምዕራፉን አጠናቆ ዛሬ ሰኔ 4/2018 ዓ.ም ወደ ተግባር በመግባት የመጀመሪያውን የሙያ ፍቃድ ምዝገባ አገልግሎት በውጤታማነት ከውኗል። ይህ ተግባር በዞናችን ለሚገኙ የጤና ባለሙያዎች ከፍተኛ ትርጉም ያለው ሆኖ ተገኝቷል።

‎ስለሆነም በዞናችን የምትገኙ የጤና ባለሙያዎች የሙያ ምዝገባ ፍቃድ አገልግሎት ለማግኘት ዘውትር በስራ ሰዓት በመምሪያው በመገኘት መገልገል የምትችሉ መሆናችሁን እናሳውቃለን።

‎በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ!!

በጋሞ ዞን የወባ በሽታ ስርጭትን በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስ የሚያስችል ዞናዊ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው‎‎​አርባ ምንጭ፡ ሰኔ 3/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)‎‎​የጋሞ ዞን...
10/06/2026

በጋሞ ዞን የወባ በሽታ ስርጭትን በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስ የሚያስችል ዞናዊ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው

‎​አርባ ምንጭ፡ ሰኔ 3/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎​የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የወባ በሽታን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠርና ስርጭቱን በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ ከፍተኛ የወባ ጫና ካለባቸው ወረዳዎች እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ ዞናዊ የንቅናቄ መድረክ በአርባምንጭ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

‎​በመድረኩ ላይ የተገኙት የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሴፉ ዋናቃ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በሽታውን በአስተማማኝ ሁኔታ ለመግታት በተለይም ይበልጥ ተጋላጭ በሆኑ ወረዳዎች ላይ የተቀናጀና የተጠናከረ ርብርብ ማድረግ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

‎በአሁኑ ወቅት የወባ ታማሚዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው፣ በሽታው በህብረተሰቡ ላይ ከሚያደርሰው የጤና እክል ባለፈ ከባድ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎችን የሚያስከትል በመሆኑ አስቸኳይና የተቀናጀ እርብርብ ያስፈልጋል ብለዋል።

‎​በዞኑ ውስጥ የሚገኙ 10 ወረዳዎች ይበልጥ ለበሽታው ተጋላጭ መሆናቸውን የገለጹት አቶ ሴፉ፤ የወባ ስርጭት በቀጣይ አላስፈላጊ የሰው ህይወትና የኢኮኖሚ ዋጋ እንዳያስከፍል የሰኔን ወር ታሳቢ ያደረገ የአንድ ወር ልዩ ዕቅድ ተዘጋጅቶ በሽታውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ሰፊ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።

‎​በዚህ የሰኔ ወር ዕቅድም አሁን ያለውን የበሽታውን ስርጭት ጫና ከ50 በመቶ ወደ 22 በመቶ ዝቅ ለማድረግ መታቀዱን የገለጹት ኃላፊው፣ ይህንን ግብ ለማሳካት የሁሉንም ባለድርሻ አካላትና የህብረተሰቡን ንቁ ተሳትፎና ርብርብ ይጠይቃል ብለዋል።

‎በዞኑ የወባ በሽታ ስርጭት ጫና ካለባቸው አካባቢዎች መካከል ጋርዳ ማርታ፣ ካምባና አካባቢዋ፣ ዳራማሎ ወረዳ፣ ዋጫ ከተማ እና አርባምንጭ ዙሪያ ወረዳዎች በዋናነት ተጠቃሽ መሆናቸውንም አብራርተዋል።

‎​በመድረኩ ላይ የመምሪያው የበሽታ መከላከል አስተባባሪ አቶ ቻለው ንጋቱ አማካኝነት የአሁናዊ ሁኔታ ትንተና እና የቀጣይ የአንድ ወር የትኩረት አቅጣጫዎች እየቀረበ ሲሆን ሰፊ ውይይት ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል።

‎​በዚህ የንቅናቄ መድረክ ላይ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምሴ አድማሱ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የህክምና አገልግሎት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ናፍቆት ብርሃኑ፣ የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሴፉ ዋናቃን ጨምሮ የወባ በሽታ ጫና ያለባቸው አካባቢዎች ዋና አስተዳዳሪዎች፣ ከንቲባዎች እና ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።

 # የዝውውር ማስታወቂያ
10/06/2026

# የዝውውር ማስታወቂያ

የደስታ መግለጫ!‎‎የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሴይፉ ዋናቃ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንዳሻው ሽብሩ አትላንታ የአሜሪካ ሲዲሲ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች አ...
09/06/2026

የደስታ መግለጫ!

‎የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሴይፉ ዋናቃ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንዳሻው ሽብሩ አትላንታ የአሜሪካ ሲዲሲ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች አስተዳደር ዛሬ ባወጣው መግለጫ ታላቅ ክብርና ሙገሳ በመቸራቸው የተሰማቸውን ጥልቅ ልባዊ ደስታ ገልፀዋል።

‎እንዳሻው ሽብሩ ከመደበኛ የጤና ሙያቸው በተጨማሪ በክልላችን ብሎም በሀገራችን ከ20 ዓመታት በላይ የሕብረተሰብ ጤና ሥራ አመራር በመስጠት ብሔራዊና ክልላዊ የድንገተኛ አደጋዎች ክስተት አስተዳደር ሥርዓትን መርተዋል፣ አስተዳድረዋል ውጤት አስመዝግበዋል፣ ህዝባቸውን ጤና አስጠብቀዋል ክብር ይገባቸዋል ብሏል።

‎ኮቪድ 19፣ ኮሌራ፣ ኢቦላ እንዲሁም የቅርብ ጊዜው ማርበርግ ቫይረስ በሽታን ለመቆጣጠር በህብረተሰብ ጤና የድንገተኛ አደጋዎች ክስተት አስተዳደር ስርዓት አስተባባሪ በመሆን ውጤታማ ሥራ ሰርተዋል፤ ለክልሉ ድል! ለሀገር ስኬትን፣ ለአፍርካ ኩራት ሆነዋል።

‎ምክትል ቢሮ ኃላፊዎች፣ ህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት ቢሮ ማናጅመንቱ እና ሠራተኞች ለነበራቸው መተባበር ለስኬት አብቅቷቸዋል።

‎የክልሉን የጤና ፖሊሲን በማሻሻል፣ ድንገተኛ የወረርሽኝ ቁጥጥር፣ የጤና ሥርዓቱን በማጠናከር እና በሽታ የመከላከል ስራዎች ላይ ለነበራቸው ጠንካራ አቋም አለም አቀፍ ጆርናል ዛሬ ዕውቅናን ችሯቸዋል።

‎ጤና ተቋምን በጥበብና በዕውቀት የመምራት ፀጋ የተቸራቸው እንዳሻው ሽብሩ፤ የአመራሩ ቅንጅት፣ የጤና ባለሙያው ትብብር፣ የሠራተኛው አብሮነት ዛሬ በአለም አደባባይ ስሙ ጮክ ብሎ እንዲደመጥ አግዟቸዋል።

‎የወረርሽኝ ወቅት ጠንካራ ተቋማዊ ምላሾችን በመገንባት መርቷል፤ የቴክኒክ ክፍሉን ተከታትለዋል፣ አጋር ድርጅቶችን በቅንጅት የማስተዳደር ጥበብም ነበራቸው ይላል ሲዲሲ።

‎እንዳሻው፦ በመሪነት ሚናቸው በቀጥታ ስትራቴጂክ በሆነ መልኩ የሁለትዮሽ የጤና ግቦችን ያራምዳል፤ ስለዚህ ይህ ክብር ይገባቸዋል ብሏል።

‎በሀገራችን ብሎም በክልላችን ልከሰቱ ለሚችሉ ወረርሽኞች ምላሽ ለመስጠት ግብረኃይሉን ያስተባብራል፣ ያስተዳድራል ለህዝብ ጤና፣ ለአከባቢ ደህንነትና ለሀገር ሠላም የበኩሉን ይወጣል ብሏል።

‎በድጋሚ እንኳን ደስአልዎት!

‎ሴይፉ ዋናቃ
‎የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ
‎ሰኔ 2/2018 ዓ.ም
‎አርባምንጭ

የቲቢ በሽታ ጫናን መቀነስ እና መቆጣጠር የሚያስችል ስራዎች በዞኑ ተጠናክረው ቀጥለዋል፡፡‎‎አርባ ምንጭ፡-ሰኔ 2/2018 ዓ.ም( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)‎‎በዞኑ የቲቢ በሽታን ለመቆጣጠር ብ...
09/06/2026

የቲቢ በሽታ ጫናን መቀነስ እና መቆጣጠር የሚያስችል ስራዎች በዞኑ ተጠናክረው ቀጥለዋል፡፡

‎አርባ ምንጭ፡-ሰኔ 2/2018 ዓ.ም( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎በዞኑ የቲቢ በሽታን ለመቆጣጠር ብሎም ለመከለከል እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክረው ቀጥለዋል።

‎ኢትዮጵያ ሃገራችን 30 ግንባር ቀደም የቲቢ በሽታ ጫና ካላቸው ሃገራት መካከል አንዷ እንደመሆኗ መጠን በሃገር ደረጃ የበሽታውን ጫና ለመቀልበስ ዘርፈ ብዙ ርብርብ እየተደረገ ይገኘል።

‎የቲቢ በሽታ በተፋፈገ ስፍራ በሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር የቅርብ ግንኙነት ባለቸው ሰውች፣ በልዩ ልዩ ምክንያት የበሽታ መከላከል አቅማቸው በተዳከመባቸው ሰዎች ላይ ይበልጥ ተስፋቶ እንደሚገኝ ይታመናል።

‎በዚህም መነሻ የዞኑ ጤና መምሪያ ከጨንቻ ማረሚያ ተቋም ጋር በመተባበር በማረሚያ ተቋሙ የቲቢ በሽታ ልየታ እና የሕክምና ስራ በዘመቻ መልክ እያካሄደ ይገኛል።

 #የኢቦላ ቫይረስ በሽታ ቅድመ ማስጠንቀቂያ
08/06/2026

#የኢቦላ ቫይረስ በሽታ ቅድመ ማስጠንቀቂያ

ወረዳን መሠረት ያደረገ የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ዝግጅት፤አርባምንጭ:-ሰኔ 1/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ወረዳን መሠረት ያደረገ የ2019 በጀ...
08/06/2026

ወረዳን መሠረት ያደረገ የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ዝግጅት፤

አርባምንጭ:-ሰኔ 1/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ወረዳን መሠረት ያደረገ የ2019 በጀት ዓመት ጤና ተግባራት ዕቅድ ዙሪያ ከዞኖችና ሪጂኦ ፖሊስ ከተሞች ከተውጣቱ ባለድርሻ አካላት ጋር በአርባምንጭ ከተማ እየመከሩ ነው፡፡

የጤና ልማት ዕቅድና አመራሩ ለዘርፉ ትኩረት በመስጠት ወረዳን መሠረት ያደረገ ዕቅድ ማዘጋጀት ያስፈልጋል ሲሉ በክልሉ ጤና ቢሮ የጤና ልማት ዕቅድና ኢኮኖሚ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክቴር አቶ ተገኝ ጮቴ ተናግረዋል፡፡

በዕቅድ ዝግጅቱ የ3 ዓመት ግብ በማስቀመጥ የጤና ሥርዓቱን ለማሻሻል መሥራት ያስፈልጋል ሲሉም ዳይሬክተሩ አቶ ተገኝ ጠቁመዋል፡፡

ለ2019 በጀት ዓመት በጤናው ዘርፍ ተፈጻሚ እቅድ በማዘጋጀት በሁሉም የጤና ተግባራት ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ መስራት እንደሚገባም በመግለፅ።

ወረዳን መሠረት ያደረገ የዕቅድ ዝግጅት መነሻ ሀሳብ የክልሉን የጤና ልማት ዕቅድና ኢኮኖሚ አስተዳደርን ጨምሮ ሁሉም የሥራ ዘርፎችና ዳይሬክቶሬቶች መነሻ ሰነድ አቅርበዋል።

ከዕቅዱ በተጨማሪ ዲጂታል የአሰራር ስርዓትን ለማሻሻል በተግባር የሚዳሰስ የሶፍትዌር ስልጠና ይዘት እንዳለውም ተጠቁሟል።

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ክስተት አስተዳደር ሥርዓት መደበኛ ስብሰባ ዘሬ አካሄደ‎‎አርባ ምንጭ፡ ሰኔ 1/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)‎‎የዞኑ ...
08/06/2026

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ክስተት አስተዳደር ሥርዓት መደበኛ ስብሰባ ዘሬ አካሄደ

‎አርባ ምንጭ፡ ሰኔ 1/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎የዞኑ ጤና መምሪያ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ክስተት አስተዳደር ሥርዓት መደበኛ ስብሰባ አካሂዷል፡፡

‎በዚህም በናዳ ምክንያት ተፈናቅለው ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሰጠው ሁሉ አቀፍ የጤና አገልግሎት ተጠናክሮ መቀጠሉ ታውቃል፡፡ ከ 2 ሺህ በላይ ለሚሆኑ በጋጮ ባባ ማዞ ዶይሳ ጊዚያዊ መጠለያ ለሚገኙ እና በዙሪያው ለሚገኙ የማህበረሰብ ክፈሎች የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡ በገረሴ ከተማ አስተዳደር በሚገኘው የጊዚያዊ መጠለያ ተጠልለው ለሚገኙ 1 መቶ 89 ለሚሆኑ ግለሰቦች እንዲሁ የህክምና አገልግሎት ተሠጥቷቸዋል፡፡

‎ከወባ በሽታ ጋር በተያያዘ በሣለፍነው ሣምንት ውስጥ 11 ሺህ 249 የማህበረሰብ ክፍሎች ለወባ በሽታ ምርመራ ተደረጎላቸው በ 5 ሺህ 758 ሰዎች ላይ በሽታው ተገኝቶ ህክምና ተደርጎላቸዋል፡፡ የወባ በሽታ ስርጭት በጋርዳ ማርታ፣ በቁጫ፣ በካምባ ዙሪያ፣ በዳራማሎ፣ በቦረዳ እና ምዕራብ አባያ ወረዳዎች ጭማሪ ከማሣየቱ በላይ የሽታው ስርጭት በከፍተኛ ደረጃ ከተስተዋለባቸው ግንባር ቀደም አምስት መዋቅሮች መሆናቸው ተመላክቷል፡፡

‎የወባ በሽተ ስርጭት ከፈተኛ በሆነባቸው በጋርዳ ማርታ እና በዋጫ ከተማ አስተዳደር የቤት ለቤት የፀረ-ወባ ኬሚካል ርጭት እየተካሂደባቸው መሆኑ ታውቋል፡፡ የበሽታውን ስርጭትን ለመከላከል በሁሉም መዋቅሮች መላውን የማህበረሰብ ክፍሎች በነቂስ በማሳተፍ የወባ በሽታ የመከላከልና የመቆጣጠር ተግባር ከወትሮው በላቀ መልኩ ተጠነክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተጠቁሟል፡፡

‎በግብረ-ሃይሉ ስብሰባው የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ባንጌ ባንጃ፣ የመምሪያው ከፍተኛ ባለሙያዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

Address

Shecha Sub City, Beside Zone Administration
Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share