09/05/2026
👉የአለታ ወንዶ አጠቃላይ ሆስፒታል ቦርድ የ2018 በጀት ዓመት የ3ኛ ሩብ ዓመት ስብሰባውን በዛሬው ዕለት አካሂዷል፡፡
👉 የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፕሬዚዳንት ልዩ አማካሪ ክቡር መድረኩን የመሩት ሲሆን የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሌሎች የቦርድ አባላት ስብሰባውን ተካፍለዋል፡፡
👉የቦርዱ ሰብሳቢ የሆኑት ክቡር የመክፈቻ ንግግር በማድረግና የመወያያ አጀንዳዎችን በማስተዋወቅ ስብሰባውን ያስጀመሩት ሲሆን ዋና ዋና የስብሰባ አጀንዳዎችም
1. የ2019 በጀት ዓመት የ9 ዕቅድ አፈጻጸም
2. የሰው ሀይል ማሟላት በሚመለከት
3. እንዲሁም የሆስፒታሉን ቅጥር ግቢ ማስፋፊያ በሚመለከት ናቸው፡፡
👉በአጀንዳዎቹ ቅደም ተከተል መሰረት የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወር ዕቅድ አፈጻጸም በሆስፒታላችን ስራ-አስኪያጅ ቀርቧል፡፡
👉የሰው ሀብት ስብጥሩን ጨምሮ አጠቃላይ ተቋማዊ ዳሰሳ
👉በበጀት ዓመቱ የተሠጡ የጤና አገልግሎቶች ( )
👉ፋይናንሻል ሪፖርት ( )
👉ሪፎርሞችና ዋና ዋና ኢኒሼቲቭስ ( )
👉ያጋጠሙ ተግዳሮቶች (challenges)
👉ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ (Ways Forward) በሪፖርቱ ላይ ተካተው ተብራርተው ቀርበዋል፡፡
👉የተሰሩ ስራዎችንና የቀረቡ ሪፖርቶችን ማዕከል በማድረግ በተሳታፊያን መካከል ፍሬያማ ውይይት ተካሂዷል፡፡
👉የሆስፒታሉ የ9 ወራቶች ዕቅድ አፈጻጸም ሲዳሰስ ከብዙ በጥቂቱ በሚከተሉት አገልግሎቶች ጥሩ ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል፡፡
1. የቅድመ ወሊድ አገልግሎት ያገኙ እናቶች ቁጥር ( -1, -4, and -8 coverage)
2. ለ1997 (106%) እናቶች የወሊድ አገልግሎት መሰጠት መቻሉ ( and )
3. ለ244 (116%) የጽኑ ጨቅላ ህጻናት የህክምና አገልግሎት መሰጠት መቻሉ ( and_Outcome)
4. ለ126,600 (115%) የተመላላሽ ታካሚዎች አገልግሎት መስጠት ተችሏል ( )
5. ለ52 ጾታዊ ጥቃት ለደረሰባቸው ተጋላጭ የማህበረሰባችን ክፍሎች የአንድ መስኮት አገልግሎት ማቅረብ ተችሏል፡፡ ( )
6. 8135 (101%) ታካሚዎች የድንገተኛ ህክምና ማግኘት ችለዋል ( )
7. ለ3686 (107%) ታካሚዎች የአስተኝቶ ህክምና መስጠት ተችሏል፡፡ ( ) ከዚህ ጋር በተያያዘ 85% የአልጋ መያዝ ምጣኔ ተመዝግቧል፡፡
8. ከፍተኛ የቀዶ ህክምና ያገኙ ታካሚዎች 634 ሲሆኑ ይህም ከዕቅድ አንጻር 101% ሆኗል፡፡ ( )
9. በስፔሻሊቲ ክሊኒኮች ማለትም በአይን ፣ በስነ-አዕምሮ ፣ በቆዳ እና አባላዘር፣ በጥርስ፣ በፊዝዮቴራፒ የህክምና ክፍሎች እና በስነ-ደዌ የምርመራ ክፍል ለበርካቶች አገልግሎት ማቅረብ መቻሉ (Eye_Clinic, , , , , , )
10. እንዲሁም የአዋቂዎች ጽኑ ህክምናም በበጀት ዓመቱ ጥሩ አፈጻጸም ላይ ይገኛል፡፡(Adult ICU)
👉ከነዚህ በተጨማሪ ከወረቀት ነጻ አገልግሎት አሰጣጥ ስራው ከተጀመረበት የበጀት ዓመቱ ጀምሮ ያለመቆራረጥ እና በየጊዜ እየዘመነ መምጣቱ እንዲሁም ሌሎች ዲጂታላይዜሽን ላይ የተሰሩ ስራዎች የምርጥ ተሞክሮ ማዕከል በሚል ቀርቧል፡፡
💧የውስጥ ገቢን ከማሳደግ አንጻር ከዕቅድ አንጻር ጥር አፈጻጸም ላይ መገኘቱ ( )
👉በውይይቱ ወቅትም ከላይ የተዘረዘሩት አፈጻጸሞች በጥሩ ጎን የተነሱና ወደፊትም ሊቀጥሉ ይገባቸዋል የተባሉ ሲሆኑ ይህ በእንዲህ እንዳለ በተደጋጋሚ ለውይይት የቀረበው የህንጻ ግንባታ አለመጀመር በሚመለከት፣ የጤና መድኃን ተጠቃሚዎችን ቁጥር እና እርካታ መጨመር፣ የመድኃኒት አቅርቦት በቀጣይ ትኩረት የሚያሻቸው ናቸው በሚል ሀሳብ ተሰንዝሮባቸዋል፡፡
👉በዚህም መሰረት የህንጻ ግንባታ ከሚመለከተው ባለድርሻ አካል ጋር በመቀናጀት በቶሎ ወደ ግንባታ መግባት
👉የቅጥር ግቢውን ለማስፋት ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ውይይት ማድረግ እንደሚያሻው
👉ከወቅታዊው የነዳጅ አቅርቦት ጋር በተያያዘ ሆስፒታሉን በሚመጥን መልኩ አቅርቦቱን ማሻሻል እንደሚያስፈልግ
👉የመድህኒት በአጠቃላይ የህክምና ግብዓቶችን በሚመለከት የአቅርቦት ሰንሰለቱን በማጠናከር በበቂ ለማቅረብ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ በቀጣይ ሊሰራባቸው ይገባል በሚል ተነስተዋል።
🎯በማጠቃለያውም ክቡር ለተገኙ ስኬቶች የሆስፒታሉን ሠራተኞች ጨምሮ መላውን ባለድርሻ አካላት በማመስገን በአውንታዊ የተነሱ ጉዳዮች ማስቀጠል እንደሚገባ አሳስበው በቀጣይ ሊሰሩ የሚገባቸውን ስራዎች በዝርዝር አንስተው የስራ አቅጣጫዎችንና መመሪያዎች አስቀምጠው ስብሰባው ተጠናቋል፡፡