በባስኬቶ ዞን የላስካ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት Laska Communication

  • Home
  • Ethiopia
  • Aleta
  • በባስኬቶ ዞን የላስካ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት Laska Communication

በባስኬቶ ዞን የላስካ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት Laska Communication እውነተኛና ተአማኒ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ለማቅረብ እንተጋለን።
(1)

‎1447ኛው ዓመተ ሂጅራ የአረፋ በዓል በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ በደማቅ ሁኔታ ተከበረ።‎‎ግንቦት 19/2018 ዓ/ም‎‎በርካታ የዕምነቱ ተከታዮች በተገኙበት በላስካ ከተማ ዶንኪ ስታዲየም በ...
27/05/2026

‎1447ኛው ዓመተ ሂጅራ የአረፋ በዓል በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ በደማቅ ሁኔታ ተከበረ።

‎ግንቦት 19/2018 ዓ/ም

‎በርካታ የዕምነቱ ተከታዮች በተገኙበት በላስካ ከተማ ዶንኪ ስታዲየም በተለያዩ ሀይማኖታዊ ስነ ስርዓቶች ነው የተከበረው።

‎በዓሉ የትህትና የመታዘዝ በዓል መሆኑን ያወሱት ሼህ አህመድ ዓሊ ከአላህ ዘንድ እዝነትና የመታዘዝን ዋጋ ለማግኘት ከነቢዩ ኢብራሂምና ልጃቸው እስማዔል ፍጹም የፈጣሪ ታዛዥነት ልንማር ይገባል ብለዋል።

‎አቅመ ደካሞችን መጠየቅና በዓሉን አብሮ ማሳለፍ የነቢዩ ኢብራሂም ሱና መሆኑን የገለጹት ሼህ አህመድ አሊ ይህን በመፈጸም ከበዓሉ በረካ መቋደስ ይገባልም ብለዋል።

‎የበዓሉ ታዳሚያን በበኩላቸው የአረፋ በዓል ሃይማኖታዊ ክንውን ብቻ ሳይሆን፣ ማህበራዊ ፍቅርና አንድነት በተግባር የሚታይበት ነው ያሉ ስሆን አቅመ ደካሞችን በመዘየር እንደሚያከብሩም ገልጸዋል።

‎በመርሐ ግብሩ የዒድ ተክብራ ተክብራና ቁርዓን እንዲሁም በህጻናት ሴቶች ነሺዳ የቀረበ ሲሆን በዒድ ሶላትና ሺጥባ በዓሉ ፍጻሜውን አግኝቷል።

‎ ግንቦት 19/2018 ዓ/ም

‎ለ1447ኛው ዓመተ ሂጅራ የአረፋ በዓል በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ እየተከበረ ይገኛል።‎‎ግንቦት 19/2018 ዓ/ም‎‎በዓሉ በርካታ የዕምነቱ ተከታዮች በተገኙበት በላስካ ከተማ ዶንኪ ስታዲየ...
27/05/2026

‎ለ1447ኛው ዓመተ ሂጅራ የአረፋ በዓል በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ እየተከበረ ይገኛል።

‎ግንቦት 19/2018 ዓ/ም

‎በዓሉ በርካታ የዕምነቱ ተከታዮች በተገኙበት በላስካ ከተማ ዶንኪ ስታዲየም ነው እየተከበረ የሚገኘው።

‎እዚሁ ዶንኪ ስታዲየም በሚኖረው ቆይታ የዒድ ተክብራ ተክብራና ቁርዓን እንዲሁም የሴቶች ነሺዳ እንደሚቀርብና በዕለቱ የዒድ ሶላትና ሺጥባ የበዓሉ ፍጻሜ እንደሚሆን ይጠበቃል።

‎የላስካ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዪኒት የበዓሉን ሙሉ ኩነት እየተከታተለ ወደናንተ የሚያደርስ ይሆናል።

‎ ግንቦት 19/2018 ዓ/ም

‎የላስካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢ/ር አንለይ ወንድይፍራው ለ1447ኛው ዓመተ ሂጅራ የአረፋ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ።‎‎የከንቲባው ሙሉ መልእክት እንደሚከተለው ቀርቧ...
26/05/2026

‎የላስካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢ/ር አንለይ ወንድይፍራው ለ1447ኛው ዓመተ ሂጅራ የአረፋ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ።

‎የከንቲባው ሙሉ መልእክት እንደሚከተለው ቀርቧል፦

‎የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ፣ እንኳን ለታላቁ የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

‎የዒድ አል-አድሃ ወይም የታላቁ የአረፋ በዓል ጥልቅ ማህበራዊና መንፈሳዊ አስተምህሮዎችን ሰንቆ፣ ከታላቁ የሐጅ ጉዞና ከፍጹም እምነት ጋር በተያያዘ መንፈሳዊ ሥነ-ስርዓት በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ይከበራል።

‎ይህ በዓል የታላቁን የነብዩ ኢብራሂምን የታዛዥነትና የመስዋዕትነት ትምህርት የምናስብበት፣ ያጣነውን የምንተካበት፣ የተጣላን የምናስታርቅበትና የተቸገሩትን በመርዳት የምናከብረው የበረከት ወቅት ነው።

‎የበዓሉ መነሻ ታሪክ የሚመዘዘው ከነቢዩ ኢብራሂም እና ከልጃቸው ከነቢዩ እስማዔል ፍጹም የፈጣሪ ታዛዥነት ገድል ጋር ነው።

‎የነቢዩ ኢብራሂም (ዐ.ሰ) የሚወዱትን ልጃቸውን መስዋዕት እንዲያደርጉ ከአላህ የተሰጣቸውን ትዕዛዝ ያለ ምንም ማንገራገር ለመፈጸም በተነሱበት ቅጽበት፣ ፈጣሪ ለታማኝነታቸው በግ በመላክ ልጃቸውን ተክቶላቸዋል።

‎ይህ ታሪካዊ ክስተት የዕምነቱ ተከታዮች ለፈጣሪ ያላቸውን ፍጹም ተገዢነት እና ለአላህ ስሉ ውድ ነገራቸውን መስዋዕት ማድረግን በየዓመቱ እንዲያስታውሱ ያደርጋል።

‎ታዛዥነት እሽ ባይነት በጎ ውጤት ፍፁም በረከት ያለው መሆኑን ከዚህ በዓልና የታሪኩ መነሻ ከሆኑት ነቢዩ ኢብራሂም እና ከልጃቸው እስማዔል መማር ይቻላል።

‎በድጋሚ እንኳን ለኢድ አል-አድሃ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ይህ ታላቅ በዓል እርስ በርስ የመረዳዳት፣ የመተሳሰብና የመደጋገፍ እሴቶቻችንን ይበልጥ የምናጠናክርበት እንዲሆን እንመኛለን።

‎ኢድ ሙባረክ!


‎ የላስካ ከተማ አስተዳደር ዋና ከንቲባ
‎ ግንቦት 18/2018 ዓ/ም
‎ ላስካ

‎ታላቅ የብልፅግና ፓርቲ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ ተካሄደ‎‎ላስካ፣ ግንቦት 16/2018 ዓ.ም‎‎በርካታ የብልፅግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች በተገኙበት ዞናዊ ማጠቃለያ...
24/05/2026

‎ታላቅ የብልፅግና ፓርቲ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ ተካሄደ

‎ላስካ፣ ግንቦት 16/2018 ዓ.ም

‎በርካታ የብልፅግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች በተገኙበት ዞናዊ ማጠቃለያ የድጋፍ ሰልፍና የ“ምረጡኝ” ቅስቀሳ መርሃ ግብር በባስኬቶ ዞን መዲና ላስካ ከተማ ተካሂዷል።

‎ብልፅግና ፓርቲ በአገራችን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ለውጥ ጉዞ ውስጥ በአምስት ዓመታት ታላቅ ሚና በመጫወት የሕዝብ ተስፋና የአገር እድገት ምልክት ሆኖ ቆይቷል ያሉት በሚንስትር ማዕረግ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግሥት ትርጉምና ውሳኔ አፈጻጸም ቋሚ ኮሚቴ ፀሐፊ ወይዘሪት ፍሬሕይወት ዱባለ፣ ፓርቲው በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አባላትና ደጋፊዎችን በማቀፍ በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ ትልቅ ቁጥር ያላቸውን አባላት በመያዝ ቀዳሚ ሆኗል ሲሉ አክለዋል።

‎ብልፅግና ፓርቲ በሀገራችን ሥር የሰደዱና ለረጅም ጊዜ የቆዩ ችግሮችን በመቅረፍ ኢትዮጵያን ወደ ብልፅግና ማማ ለማድረስ የሚያስችለውን የመደመር መንገድ በመከተል መዳረሻችን የሆነውን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ እየሰራ በከፍታ ጉዞ ላይ ያለ ግዙፍ ፓርቲ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ወይንቱ መልኩ ገልጸዋል።

‎“ዛሬ እዚህ የተሰበሰብነው ስለ ባስኬቶ ዞን ቀጣይ አምስት ዓመታት እድገት፣ ሰላምና ብልፅግና በጋራ ለመወሰን ነው” ያሉት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ዕጩ ዶ/ር ሳሙኤል ደሳለኝ፣ “ቃላችንን በተግባር ለማሳየት ያለንን ቁርጠኝነት እንገልጻለን” ብለዋል።

‎“ብልፅግናን ማረጋገጥ የሚቻለው ሁሉም ነገር አልጋ በአልጋ ሲሆን ሳይሆን፣ ፈታኝ የሆኑ ችግሮችን ወደ መልካም ዕድል በመቀየር ነው” ሲሉም አስተዳዳሪው አክለዋል።

‎ብልፅግና ፓርቲ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ባህል ውስጥ አቃፊ፣ አሳታፊና አካታች ፓርቲ መሆኑን የገለጹት የባስኬቶ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለምብርሃን ካሳሁን፣ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ታይተው የማይታወቁ አዳዲስ ውሳኔዎች መወሰናቸውን ገልጸዋል።

‎በመርሃ ግብሩ በሚንስትር ማዕረግ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግሥት ትርጉምና ውሳኔ አፈጻጸም ቋሚ ኮሚቴ ፀሐፊ ወይዘሪት ፍሬሕይወት ዱባለን ጨምሮ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም በርካታ የብልፅግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ተገኝተዋል።

‎ግንቦት 16/2018 ዓ.ም
‎ላስካ

‎በባስኬቶ ዞን በህዝባዊ ማዕበል ታጅቦ እየተካሄደ የሚገኘው የብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍና የ"ይምረጡኝ" ቅስቀሳ በምስል፦
24/05/2026

‎በባስኬቶ ዞን በህዝባዊ ማዕበል ታጅቦ እየተካሄደ የሚገኘው የብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍና የ"ይምረጡኝ" ቅስቀሳ በምስል፦

‎"በትምህርት ልማት ዘርፍ የተጀመሩ ለውጦችን አጠናክሮ በማስቀጠል ኢትዮጵያን ተምሳሌት ሀገር ለማድርግ ምርጫችን ብልጽግና ነው!" በሚል መሪ ቃል በባስኬቶ ዞን የብልጽግና ፓርቲ አባልና ደጋፊ...
23/05/2026

‎"በትምህርት ልማት ዘርፍ የተጀመሩ ለውጦችን አጠናክሮ በማስቀጠል ኢትዮጵያን ተምሳሌት ሀገር ለማድርግ ምርጫችን ብልጽግና ነው!" በሚል መሪ ቃል በባስኬቶ ዞን የብልጽግና ፓርቲ አባልና ደጋፊ መምህራንና የትምህርት ሴክተር አመራሮች ጋር የአባላት አቅም ግንባታ እና የምርጫ ቅስቀሳ ውይይት ተደረገ።

‎ግንቦት 15/2018 ዓ/ም

‎በባስኬቶ ዞን የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት "በትምህርት ልማት ዘርፍ የተጀመሩ ለውጦችን አጠናክሮ በማስቀጠል ኢትዮጵያን የተምሳሌት ሀገር ለማድርግ ምርጫችን ብልጽግና ነው!" በሚል መሪ ቃል የብልጽግና ፓርቲ አባልና ደጋፊ መምህራንና የትምህርት ሴክተር አመራሮች ጋር የአባላት አቅም ግንባታ እና የምርጫ ቅስቀሳ ውይይት ተደርጓል።

‎መምህራን የትምህርት ክፍል ውስጥ መሪዎች ብቻ ሳይሆኑ፤ የሀገርና የትውልድ መሐንዲሶች ናቸው ያሉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ወይንቱ መልኩ የብልጽግና ፓርቲ የትምህርት ጥራትና የመምህራንን ክብር ሳያረጋግጥ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ማምጣት እንደማይቻል ያምናል ብለዋል።

‎ብልጽግና ፓርቲ የትምህርት ስብራትን ለመጠገን የወሰዳቸው እርምጃዎች ትልቅ እምርታ የፈጠሩ መሆኑን የገለጹት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዱፄ ታምሩ የመምህራንን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል፣ የቤት ባለቤትነት ዕድሎችን ለማመቻቸትና የደመወዝ ስኬል ማሻሻያዎችን ተግባራዊ ማድረግ መቻሉ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ፈጥሯል ብለዋል።

‎የነገዋን ኢትዮጵያ የመቅረጽ ኃላፊነት በመምህሩ እጅ መሆኑን የገለጹት የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዕጩ ዶ/ር ሳሙኤል ደሳለኝ መምህራን ይህን ትልቅ ኃላፊነት በቀጣይ ኢትዮጵያን ተምሳሌት ሀገር ለማድረግ በሚደረገው ጉዞ ላይ የራሳችሁን አሻራ ማሳረፍ ይገባል ብለዋል።

‎መምህራን በበኩላቸው መንግስት በትምህርት መሠረተ ልማትና በዲጂታላይዜሽን የጀመራቸውን ስራዎች ይበልጥ እንዲያስቀጥል እንፈልጋለን ያሉ ሲሆን ይህ እንዲሳካም የፓርቲያችንን የምርጫ ማኒፌስቶ ለህብረተሰቡ በማስተዋወቅና ደጋፊዎቻችንን በማስተባበር የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉ አቋማቸውን ገልጸዋል።

‎ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ሰነድ በባስኬቶ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለምብርሃን ካሳሁን ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

‎ግንቦት 15/2018 ዓ.ም
‎ላስካ

‎‹‹ትውልድ ለመገንባት እኔም የበኩሌን ድርሻ እወጣለሁ›› ‎‎ድር ቢያብር አንበሳ ያስር ነዉና ብሂሉ በህይወት ምዕራፍ ትርጉም ያለዉ ስብዕና የገነባንበት  ፣ማህበራዊ መተሳሰር የፈጠርንበት ፣...
21/05/2026

‎‹‹ትውልድ ለመገንባት እኔም የበኩሌን ድርሻ እወጣለሁ››

‎ድር ቢያብር አንበሳ ያስር ነዉና ብሂሉ በህይወት ምዕራፍ ትርጉም ያለዉ ስብዕና የገነባንበት ፣ማህበራዊ መተሳሰር የፈጠርንበት ፣ የአንድነትና ፍቅር መሰረት የሆኑን እንዲሁም የስኬቶቻችን መነሻ የሆኑን፣ ያለማወቆቻችን ድል መንሻ የሆኑት ትምህርት ቤቶቻቻን ፤ በብዙ ጉድለት ዉስጥ ናቸዉ ፡፡ የተገነባንበትን የተሰራንበትን የእዉቀት ተቋም እንደ ቀጫጭኖቹ ድሮች አብረን ወፍራም ገመድ ሰርተን በትምህርት ቤቶች ያለዉን የመማርያ ቁሳቁስ ችግር ለመፍታት ማህበራዊ ሀላፊነታችንን እንወጣ ፡፡

‎ይሄ ኢንኒሼቲቭ ይሄ ዉጥን የቁጭት ነዉ፡፡ ቁሳቁስ በተለይም የመማርያ ዴስክቶፖች፣ የኢንተርኔት ዝርጋታ ኣክሰሰሪ፣ ፕሪንተሮች፣ መጽሀፍት እና ቤተ መጽሀፍት ለማደራጀት ሚያስፈልጉ መደርደርያዎች ወዘተ በቁስ እና በገንዘብ የምትደግፉ ተቋማትና ግለሰቦች ከታች ፤ለዚሁ ዓላማ ተብሎ በተከፈተዉ አካዉንት የድረሻችሁን አንድትወጡ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ፡፡ ትንንሽ ትብብሮች ትላልቅ ቀዳዳ ይደፍናሉና ማህበራዊ ሀላፊነታችንን እንወጣ ፡፡

‎የባስኬቶ ዞን የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ግብዓት ማሟያ አካውንት
‎የአካውንቱ ስም፡- BASKETO ZONE HULETEGNA DEREJA TIMIRT
‎አካውንት ቁጥር፡- 1000767836825

‎"ብልጽግና ፓርቲን በመምረጥ በሀገራችን የተጀመሩ ሁለንተናዊ የልማት ሥራዎች እናስቀጥላለን" አሉ የዋጳ ባልኣሳ ሞጆ ከተማ ቀበሌ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች‎‎ግንቦት 12/2018 ዓ...
20/05/2026

‎"ብልጽግና ፓርቲን በመምረጥ በሀገራችን የተጀመሩ ሁለንተናዊ የልማት ሥራዎች እናስቀጥላለን" አሉ የዋጳ ባልኣሳ ሞጆ ከተማ ቀበሌ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች

‎ግንቦት 12/2018 ዓ.ም

‎በባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ ዋጳ ባልኣሳ ሞጆ ከተማ ቀበሌ ታላቅ የብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍና የ"ይምረጡኝ" ቅስቀሳ ተካሄደ።

‎የድጋፍ ሰልፉ ዋና ዓላማ ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት ጥቅት የለውጥ ዓመታት ያስመዘገባቸውን ትልልቅ ስኬቶችን ለማስቀጠልና ፓርቲው ኢትዮጵያን ተምሳሌት ሀገር ለማድረግ ያስቀመጠውን ግብ ዕውን ለማድረግ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።

‎በድጋፍ ሰልፉ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዕጩ ዶ/ር ሳሙኤል ደሳለኝ ብልጽግና ፓርቲ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር እያሻገረ ያለ ፓርቲ ነው ብለዋል።

‎የባስኬቶ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዓለምብረሃን ካሳሁን በሀገራችን የተጀመረውን የልማትና የዕድገት ጉዞ ለማስቀጠል የብልጽግና ፓርቲን ይምረጡ ብለዋል።

‎ተሳታፊዎች በበኩላቸው “ብልፅግና ለሁሉም ዜጎች እኩል ተሳትፎና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፓርቲ ነው” በማለት ፓርቲው በመደመር እሳቤ ላይ ተመስርቶ የህዝቦችን አንድነት ለማጠናከር፣ የልማት ተጠቃሚነትን ለማስፋትና የወጣቶችና ሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

‎በቅስቀሳው ወቅት የፓርቲውን የምርጫ አርማና መፈክሮች የያዙ ባነሮችና ፅሁፎች ሲታዩ በባህላዊ ዝግጅቶች፣ ጭፈራና የድጋፍ መዝሙሮች የታጀበ የህዝብ ተሳትፎ ተስተውሏል።

‎አመራሮቹ በመጨረሻ ለሀገሪቱ የተረጋጋ ሰላም፣ ፈጣን ልማትና የተሻለ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መገንባት የሁሉንም ዜጎች ተሳትፎ የሚጠይቅ መሆኑን በመግለፅ ህዝቡ በንቃት በምርጫ ሂደቱ እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።

‎ግንቦት 12/2018 ዓ.ም
‎ ላስካ

‎ታላቅ የብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍ በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ አስተዳደር ተካሄደ።‎‎ግንቦት 12/2018 ዓ/ም (ላስካ ኮሙኒኬሽን)‎‎በላስካ ከተማ አስተዳደር በ01 እና በ02 ቀበሌያት ...
20/05/2026

‎ታላቅ የብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍ በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ አስተዳደር ተካሄደ።

‎ግንቦት 12/2018 ዓ/ም (ላስካ ኮሙኒኬሽን)

‎በላስካ ከተማ አስተዳደር በ01 እና በ02 ቀበሌያት የሚገኙ የብልጽግና ፓርቲ ደጋፊና አባላት በነቂስ በአደባባይ በመውጣት ለብልፅግና ፓርቲ ያላቸውን ድጋፍና አጋሪነት አሳይተዋል።

‎በድጋፍ ሰልፉ ላይ የተገኙት የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዕጩ ዶ/ር ሳሙኤል ደሳለኝ ፓርቲያችን ብልጽግና ወደ አመራርነት ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ ሀገራችን ኢትዮጵያ በብዙ ፈተናዎች ውስጥ አልፋለች። ሆኖም ግን፣ በፈተናዎች ተንበርክከን አልቀረንም! ይልቁኑ ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር አዳዲስ የታሪክ ምዕራፎችን ፅፈናል ብለዋል።

‎ታላቁ የሕዳሴ ግድባችን ማጠናቀቅ መቻላችን፣ በአረንጓዴ አሻራ ያረገብነው ምድራችን፣ የገበታ ለሀገር የቱሪዝም መናፈሻዎቻችን፣ እና እንደ ሀገር በየከተሞቻችን የተገነቡት ውብ መሠረተ ልማቶች የሚያሳዩት አንድ ነገር ብቻ ነው እኛ ኢትዮጵያውያን ከተባበርንና ካቀድን የማንሻገረው ተራራ፣ የማናሳካው ከፍታ የለም ብለዋል።

‎በቀጣይ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ላይ ድምጻችሁን ለብልፅግና ፓርቲ በመስጠት ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር ያሻግሩ ሲሉም መልእክት አስተላልፈዋል።

‎የላስካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢ/ር አንለይ ወንድይፍራው ዛሬ እዚህ የተሰበሰብነው በባዶ ተስፋ ለመደለል ሳይሆን፣ በአይናችን ያየናቸውን፣ በእጃችን የዳሰስናቸውንና በጋራ ያመጣናቸውን ስኬቶች ለመመስከር ነው ብለዋል።

‎ብልጽግና ፓርቲ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊያንን የሚመጥን አዳጊና ትውልድ ተሻጋሪ ሃሳብ ያለው ፓርቲ መሆኑን የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ብቻም ‎ሳንሆን የተፎካካሪ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎችም ጭምር የሚያምኑትና የሚቀበሉት ሐቅ ነው ሲሉም አክለዋል፡፡

‎ኢትዮጵያ የጀመረቻቸውን የብልጽግና ጉዞ ከዳር ለማድርስና ተምሳሌታዊት ሀገር ለማድረግ ምርጫችሁ የስንዴ ነዶ ይሁን ብለዋል።

‎በድጋፍ ሰልፉ ላይ እኛ ከመከፋፈል ይልቅ አንድነትን፣ ከጥፋት ይልቅ ልማትን፣ ከትናንት ጥላቻ ይልቅ የነገን ብልፅግና እንመርጣለን!

‎የጀመርነው የብልፅግና ጉዞ በሕዝባችን ኃይል ይቀጥላል!

‎ኢትዮጵያ በልጆቿ ትጋት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር የሚሉና መሰል መፈክሮችንም በሰልፉ የታደሙ መላው የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች አሰምተዋል።



ግንቦት 2018ዓ/ም
‎ ላስካ

‎በባስኬቶ ዞን የዘንድሮውን 12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በበየነ መረብ በመታገዝ በላስካ ከተማ ለመስጠት በቂ ዝግጅት መደረጉ ተገለፀ።‎‎ግንቦት 10/2018 ዓ.ም‎‎የክልልና የዞን ከፍተኛ የ...
18/05/2026

‎በባስኬቶ ዞን የዘንድሮውን 12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በበየነ መረብ በመታገዝ በላስካ ከተማ ለመስጠት በቂ ዝግጅት መደረጉ ተገለፀ።

‎ግንቦት 10/2018 ዓ.ም

‎የክልልና የዞን ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በላስካ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመገኘት የተደረገውን ዝግጅት ምልከታ አድርገዋል።

‎የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በበየነ መረብ በመታገዝ በላስካ ከተማ ለመስጠት በቂ ዝግጅት መደረጉን የዞኑ ምክትል አስተዳደርና የትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ክንፉ ሻቦ ገልጸዋል።

‎አቶ ክንፉ አክለውም በዞኑ በኩል የኮሚፒውተር አቅርቦትና የነትዎርክ ዝርጋት ስራዎች መጠናቀቃቸውና በሀገር አቀፍ ደረጃ የተዘጋጀ ፈተና ለሙከራ መሰጠት መጀመሩን ተናግረዋል።

‎ፈተናው በባስኬቶ ዞን ላስካ ማዕከል መሰጠቱ ተማሪዎች በሌሎች አከባቢዎች በመሄድ በሚደርስባቸው የስነልቦና ጫናና የአከባቢ ለውጥ ምክንያት የሚከሰተውን የውጤት ማሽቆልቆል ለማሻሻል ትልቅ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል።

‎የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የማታ ትምህርትን ጨምሮ በርካታ አጋዥ ስራዎች መሰራታቸውን የገለጹት አቶ ክንፉ የዘንድሮውን ሞዴል ፈተና በበየነ መረብ ለመስጠት መታቀዱንም አንስተዋል።

‎በምልከታው የተገኙ ከፍተኛ አመራሮች በበኩላቸው የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላስካ ማዕከል ለመስጠት የተወሰደው እርምጃ አስደናቂ መሆኑንና አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።

‎በዘንድሮው 12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በማህበራዊ ሳይንስና በተፈጥሮ ሳይንስ በመደበኛና በግል 822 ተማሪዎች ፈተና ይወስዳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገልጿል።

‎ግንቦት 10/2018 ዓ.ም
‎ላስካ

‎በባስኬቶ ዞን በተለያዬ አከባቢዎች የብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍና የ"ይምረጡኝ" ቅስቀሳ በደማቅ ሁነታ ተካሄደ።‎‎ግንቦት 9/2018 ዓ.ም‎‎በባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ በተለያዬ አከ...
17/05/2026

‎በባስኬቶ ዞን በተለያዬ አከባቢዎች የብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍና የ"ይምረጡኝ" ቅስቀሳ በደማቅ ሁነታ ተካሄደ።

‎ግንቦት 9/2018 ዓ.ም

‎በባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ በተለያዬ አከባቢዎች የብልጽግና ፓርት የድጋፍ ሰልፍና የ"ይምረጡኝ" ቅስቀሳ በተለያዩ ደማቅ ኩነቶች ታጅቦ በድምቀት ተካሂዷል።

‎የድጋፍ ሰልፉ ዋና ዓላማ ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት ጥቅት የለውጥ ዓመታት ያስመዘገባቸውን ትልልቅ ስኬቶችን ለማስቀጠልና ፓርቲው ኢትዮጵያን ተምሳሌት ሀገር ለማድረግ ያስቀመጠውን ግብ ዕውን ለማድረግ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።

‎በመድረኩ ላይ የተገኙ የፓርቲ አመራሮች፣ አባላት፣ ወጣቶች፣ ሴቶችና የማህበረሰብ ክፍሎች ብልፅግና ፓርቲ ለሀገራዊ አንድነት፣ ለሰላም፣ ለልማትና ለዲሞክራሲ ያደረጋቸውን ጥረቶች በማንሳት ህዝቡ በመጪው ምርጫ ፓርቲውን እንድመረጡ ጥሪ አቅርበዋል።

‎ተሳታፊዎች በበኩላቸው “ብልፅግና ለሁሉም ዜጎች እኩል ተሳትፎና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፓርቲ ነው” በማለት ፓርቲው በመደመር እሳቤ ላይ ተመስርቶ የህዝቦችን አንድነት ለማጠናከር፣ የልማት ተጠቃሚነትን ለማስፋትና የወጣቶችና ሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

‎በቅስቀሳው ወቅት የፓርቲውን የምርጫ አርማና መፈክሮች የያዙ ባነሮችና ፅሁፎች ሲታዩ በባህላዊ ዝግጅቶች፣ ጭፈራና የድጋፍ መዝሙሮች የታጀበ የህዝብ ተሳትፎ ተስተውሏል።

‎አመራሮቹ በመጨረሻ ለሀገሪቱ የተረጋጋ ሰላም፣ ፈጣን ልማትና የተሻለ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መገንባት የሁሉንም ዜጎች ተሳትፎ የሚጠይቅ መሆኑን በመግለፅ ህዝቡ በንቃት በምርጫ ሂደቱ እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።

‎ግንቦት 9/2018 ዓ.ም
‎ላስካ

Address

Basketo, Laska
Aleta

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በባስኬቶ ዞን የላስካ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት Laska Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to በባስኬቶ ዞን የላስካ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት Laska Communication:

Share