27/05/2026
1447ኛው ዓመተ ሂጅራ የአረፋ በዓል በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ በደማቅ ሁኔታ ተከበረ።
ግንቦት 19/2018 ዓ/ም
በርካታ የዕምነቱ ተከታዮች በተገኙበት በላስካ ከተማ ዶንኪ ስታዲየም በተለያዩ ሀይማኖታዊ ስነ ስርዓቶች ነው የተከበረው።
በዓሉ የትህትና የመታዘዝ በዓል መሆኑን ያወሱት ሼህ አህመድ ዓሊ ከአላህ ዘንድ እዝነትና የመታዘዝን ዋጋ ለማግኘት ከነቢዩ ኢብራሂምና ልጃቸው እስማዔል ፍጹም የፈጣሪ ታዛዥነት ልንማር ይገባል ብለዋል።
አቅመ ደካሞችን መጠየቅና በዓሉን አብሮ ማሳለፍ የነቢዩ ኢብራሂም ሱና መሆኑን የገለጹት ሼህ አህመድ አሊ ይህን በመፈጸም ከበዓሉ በረካ መቋደስ ይገባልም ብለዋል።
የበዓሉ ታዳሚያን በበኩላቸው የአረፋ በዓል ሃይማኖታዊ ክንውን ብቻ ሳይሆን፣ ማህበራዊ ፍቅርና አንድነት በተግባር የሚታይበት ነው ያሉ ስሆን አቅመ ደካሞችን በመዘየር እንደሚያከብሩም ገልጸዋል።
በመርሐ ግብሩ የዒድ ተክብራ ተክብራና ቁርዓን እንዲሁም በህጻናት ሴቶች ነሺዳ የቀረበ ሲሆን በዒድ ሶላትና ሺጥባ በዓሉ ፍጻሜውን አግኝቷል።
ግንቦት 19/2018 ዓ/ም