የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Alaba K'ulito
  • የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት በመንግሥት መስሪያ ቤቶች ስለሚሠሩ ሥራዎች ለከተማው ህዝብ እንዲሁም የከተማውን ህዝብ ፍላጎቶችና ሁሉ ዓቀፍ መረጃዎችን የሚያበስር ገጽ ነው።
(2)

የሀላባ ዞን ዋና አስተዳደር ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን በዞኑ የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በይፋ አስጀመሩሰኔ 8/2018 የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን በሀላባ ዞን በቁሊቶ...
15/06/2026

የሀላባ ዞን ዋና አስተዳደር ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን በዞኑ የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በይፋ አስጀመሩ

ሰኔ 8/2018 የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን በሀላባ ዞን በቁሊቶ ከተማ የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በይፋ አስጀምረዋል።

በይፋ መሰጠት የተጀመረው የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ለተከታታይ 2 ቀናት እንደምሰጥ ተገልጿል።

ተፈታኝ ተማሪዎችን በተረጋጋ መንፈስ ፈተናውን በመውሰድ እንደሚገባቸው ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን አበረታትተዋል።

በዞኑ የ2018 ትምህርት ዘመን ክልላዊ 6ኛ ክፍል ፈተና የሚወስዱ 3ሺህ 375 ተማሪዎች መሆናቸውን የዞኑ ትምህርት መምሪያ አስታውቀዋል።

በማስጀመሪያ መርሀ-ግብሩ ላይ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ት/ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊና የመማር ማስተማር ምዘና ዘርፍ ሀላፊ አቶ ማትዎስ ማልዳዬ፣ የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ከንቲባ ገመዳ መሀመድ፣ የሀላባ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ኤፍሬም ዘለቀ፣ ሌሎች የዞንና ከተማ አስተዳደር አመራሮች ተገኝተዋል።

በዞኑ በኢንቨስትመንት እና በኢንዱስትሪ ዘርፍ ትኩረት ሰጥተው በመሰራቱ አበረታች ውጤቶች ተመዝግቧል፦ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ!!በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ ...
14/06/2026

በዞኑ በኢንቨስትመንት እና በኢንዱስትሪ ዘርፍ ትኩረት ሰጥተው በመሰራቱ አበረታች ውጤቶች ተመዝግቧል፦ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ!!

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ ዞን የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ሁለአቀፍ ልማቷን በማሳለጥ የነዋሪዎቿን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የተለያዩ የዘመናዊ ሆቴሎች ግንባታ እየተፋጠነ ይገኛል!!

በከተሞች የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በፓርቲያችን ብልጽግና እሳቤ ተቀርጾ እየተተገበረ ያሉ አዳዲስ ኢንሼቲቮች ውጤታማነታቸው ከጊዜ ወደጊዜ እያደገ መጥቷል።

ፓርቲያችን ብልፅግና የከተሞችን ሁሉአቀፍ ዕድገት ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ዘርፈ ብዙ ስራዎችን በመስራት ላይ ነው።

የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን በዞኑ የግሉን ዘርፍ በማነቃቃት ለሁለንተናዊ ልማቶች ማፋጠን በአጽንኦት እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በዚህም በዞኑ በኢንቨስትመንት እና በኢንዱስትሪ ዘርፍ ትኩረት ሰጥተው በመሰራቱ አበረታች ውጤቶች ተመዝግቧል ዋና አስተዳዳሪው ተናግሯል።

የኢንዱስትሪና ቱሪዝም ዘርፉ ከሚያበረክተው አስተዋጽኦ ባሻገር ለከተማዋ ኢኮኖሚ እንዲነቃቀ ወሳኝ በመሆኑ መንግስት በዘርፉ በተለይም ጥራቱን የጠበቁ ሆቴሎች ግንባታ በመስፋፋት ላይ እንደሆነ ገልጸዋል።

የሆቴሎቹ በዞኑ ከተሞች በተለይም በሀላባ ቁሊቶ መገንባት በስራ ዕድል ፈጠራ፣ ለከተማ ገቢ እድገት የሚኖረው ሚናው የጎላ መሆኑን ጠቅሰው ለከተማዋና አካባቢው ገጽታ ብሎም ለሁለንተናዊ ዕድገት ወሳኝ መሆኑንም አቶ ሙህዲን ገልጸዋል።

በልማት ስም መሬት ወስደው ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ያልገቡ ባለሀብቶች ፈጥነው ወደ ስራ እንዲገቡ አቶ ሙህዲን ሁሴን አሳስበዋል።

የሆቴሎች መገንባት የሀላባ ቁላቶ ከተማ ቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ምቹ መሆኑን ለማስተዋወቅ ያግዛል ተብለዋል፡፡

በከተማው ደረጃውን የጠበቀ ሆቴሎችን መገንባት በአካባቢው ልማትን ለማፋጠን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል።

የሀላባ ዞን ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ ሀላፊ ወ/ሮ ረውዳ ረሺድ በዞኑ የከተማው ቱሪዝም ለማሳደግ በሚደረጉ ጥረቶች በሆቴል ቱሪዝም ዘርፍ የሚሰሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን ተናግሯል።

በዞኑ 1 ነጥብ 8 ቢልዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 35 አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ፍቃድ መሰጠቱንና ከ3500 ዜጎች የስራ ዕድል መፍጠራቸውንም ወ/ሮ ረውዳ ገልጸዋል።

የሀላባ ቁሊቶ ከተማን ተገቢውን መሠረተ ልማቶች በማሟላት ወደ ዘመናዊ ከተሜነት ለመቀየርና ሁለንተናዊ ብልጽግናዋን ለማረጋገጥ የግሉን ባለሀብቶች ንቁ ተሳትፎ እየተሠራ እንደሚገኝም ሃላፊዋ ገልጸዋል።
በከተማው በሆቴሉ ዘርፍ ባለሀብቶችን በስፋት በማሳተፍ አዳዲስና ጥራታቸውን የጠበቁ ሆቴሎች በመገንባት ላይ መሆናቸውንም ሃላፊዋ ተናግሯል።

በተለይም ለከተማዋ መንግስት በሠጠው ትኩረት ዘመናዊ ገፅታዋን የሚቀይር የኮርደር ልማት ግንባታ በጥራትና በፍጥነት ለመገንባትና ከተማውን ለነዋሪዎቿ ሚቹና ለቱርዝም መስህብ ልዩ በሆነ መንገድ እየተገነባ ይገኛል።

ሲል የሀላባ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ዘግቧል።

ሰኔ 6/2018 ዓ.ም
ሀላባ ቁሊቶ

‎የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ማጠቃለያ ፈተናዎች በዞኑ ከሰኔ 8 እስከ 12 ለተከታታይ ቀናት እንደሚሰጥ የሀላባ ዞን ትምህርት መምሪያ አስታወቀ ‎‎ሰኔ 7/2018 በሀላባ ዞን የ6ኛ እና ...
14/06/2026

‎የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ማጠቃለያ ፈተናዎች በዞኑ ከሰኔ 8 እስከ 12 ለተከታታይ ቀናት እንደሚሰጥ የሀላባ ዞን ትምህርት መምሪያ አስታወቀ

‎ሰኔ 7/2018 በሀላባ ዞን የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ማጠቃለያ ፈተናዎች ከሰኔ 8 እስከ 12 ለተከታታይ ቀናት እንደሚሰጥ የሀላባ ዞን ትምህርት መምሪያ ሀላፊ ዶክተር ኤፍሬም ዘለቀ አስታውቀዋል።

‎በዚህ ወቅት የሀላባ ዞን ትምህርት መምሪያ ሀላፊ ዶክተር ኤፍሬም ዘለቀ እንደገለጹት ከነገ ጀምረው የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ሰኞና ማክሰኞ እንደሚሰጥ ገልጸዋል።

‎አያይዘውም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከሰኔ 11 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ይሰጣል ሲሉም አስገንዝበዋል።

‎ዶክተር ኤፍሬም ዘለቀ ገለጻ በፈተናው ወቅት እንደተለመደው የተከለከሉ ቁሳቁሶችና ተግባራት ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚደረግ ገልጸዋል።

‎በተለይም ለኩረጃ የሚያመቹ ማናቸውም እንቅስቃሴዎች፣ በትምህርት ቤት አካባቢ ፈጽሞ የተከለከሉ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

‎ከተቀመጡት መመሪያዎች ውጭ የሚገኙ አካላትም በህጉ መሰረት ወዲያውኑ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው አስታውቀዋል።

‎ከነገ ሰኔ 8 የሚጀመረውን የ6ኛ ክፍል ፈተና 3ሺህ 375 ተማሪዎች በ97 ትምህርት ቤቶች እንደሚፈተኑ ተናግረዋል።

‎አክለውም ከሰኔ 11 ጀምሮ በሚሰጠው የ8ኛ ክፍል ፈተና 2ሺህ 354 ተማሪዎች በ68 ትምህርት ቤቶች እንደሚፈተኑ ጠቁመዋል።

‎በድምሩ በአጠቃላይ በዘንድሮው አመት የ6ኛና የ8ኛ ክፍል 5729 ተማሪዎች ክልላዊ ፈተናውን የሚወስዱ ይሆናል ብለዋል።

‎ለፈተናዎቹ ስኬታማ አፈጻጸም አስፈላጊ የሆኑ ቅድመ ዝግጅቶች በተገቢው ሁኔታ መጠናቀቃቸውን ዶክተር ኤፍሬም ተናግረዋል።

‎በመጨረሻም የፈተናዎቹ ሰላማዊና ስኬታማ አፈጻጸም የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ ርብርብ እንደሚጠይቅ ነው ብለዋል።

‎ሁሉም አካላት የድርሻቸውን ሀላፊነት በብቃት እንዲወጡ የዞኑ ትምህርት መምሪያ ሀላፊ ዶክተር ኤፍሬም ዘለቀ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

የህዝብ ተሳትፎ እና  ተጠቃሚነት  ማረጋገጥ በሚያስችሉ ስራዎች ላይ በትኩረት  መስራት ይገባል:-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) *********(ሰኔ ፣7/2018) በማዕከላዊ ኢት...
14/06/2026

የህዝብ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ በሚያስችሉ ስራዎች ላይ በትኩረት መስራት ይገባል:-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )
*********
(ሰኔ ፣7/2018) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ አፈጻጸም ማጠቃለያ ክልል አቀፍ የአመራር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )እንደገለጹት የህዝብ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ በሚያስችሉ ስራዎች ላይ በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል።

ክልሉ ሲመሰረት የነበሩ ችግሮችን ለመፍታት ጥረት በመደረጉ ክልሉ በትክክለኛ አቅጣጫ ላይ እንዲሆን ምክንያት መሆኑን ተናግረዋል።

የጋራ ትርክት ለመገንባት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ እንደነበሩ ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል።

ምርጫው በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ የነበረው የቅድመ ዝግጅት ስራ ውጤታማ እንደነበር ርዕሰ መስተዳድሩ አስታውሰዋል።

የልማት እና የምርጫ ስራ ተመጋጋቢ እንዲሆን መስራት በመቻሉ የህዝቡን ተሳትፎ ማረጋገጥ ስለመቻሉም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

በክልሉ ህዝቡን የሰላም ባለቤት በማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ለቅድመ ዝግጅት ስራ አጋዥ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ በንግግራቸው ጠቅሰዋል።

በክልሉ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት መሰራቱን ርዕሰ መስተዳድሩ አስረድተዋል።

በክልሉ በፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ፣በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና፣በገቢ፣በስራ እድል ፈጠራ፣ በኑሮ ማረጋጋት፣ በከተማ እና በገጠር ኮሪደር ልማት ስራ ላይ የተጀመሩ ተግባራትን ማጠናከር ተገቢ ስለመሆኑም አሳስበዋል።

በወቅታዊ የግብርና ልማት ስራ ላይ የጋራ ጥረት ማድረግ ይገባል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የግሪን ኢኔሼቲቭ እና የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ትኩረት የሚሹ ስለመሆኑም አመላክተዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር )እንደገለጹት ህዝቡ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ የነበረው አበርክቶ ከፍተኛ እንደነበር ተናግረዋል።

የምርጫው ሂደት በተሳካ መልኩ እንዲካሄድ መራጩ ህዝብ፣አመራሩ፣አባላት፣ደጋፊዎች፣ወጣቶች፣ ሴቶች፣የጸጥታ ተቋማትና አካላት፣ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣መገናኛ ብዙሀን
ለነበራቸው የላቀ አስተዋጽኦ ዶ/ር ዲላሞ ምስጋና አቅርበዋል።

በምርጫው ሂደት ላይ የነበረው የሕዝብና ተሳትፎ ከፍተኛ እንደነበርም ኃላፊው አስረድተዋል።

አብዛኛው ህብረተሰብ የግል፣ የቤተሰብ፣ የጤናና የማኅበራዊ ሕይወት ፈተናዎች ሳይበገሩ ከፍተኛ ቁርጠኝነት የታየበት ምርጫ ስለመካሔዱም ዶ/ር ዲላሞ ጠቁመዋል።

በየጊዜው በሚሰጡ አገልግሎቶች ምክንያት በሕዝቡ ዘንድ ያለው እምነት እንዳይሸረሸር አጠናክሮ ማስቀጠልና የተጀመሩ የልማትና የሰላም ሥራዎችን አቅጣጫ ይዞ መጓዝ እንደሚገባ አሳስበዋል ኃላፊው ጠቁመዋል።

ምርጫው በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ የላቀ ሚና ለነበራቸው በሙሉ ዶ/ር ዲላሞ ምስጋና አቅርበዋል።

ስል የዘገበው የክልሉ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ነው።

በሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ትምህርት የ 6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ለሚወስዱ ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ኦርንቴሽን ተሰጠ ።የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ትምህርት የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ...
14/06/2026

በሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ትምህርት የ 6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ለሚወስዱ ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ኦርንቴሽን ተሰጠ ።

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ትምህርት የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ለሚወስዱ ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ኦርንቴሽን ሰጥቷል ።

‎የ6ተኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከነጌ ጀምሮ ተከታታይ ለሁለት ቀን የሚሰጥ መሆኑን ተገልጾ ነጻና በሰላም እንዲጠናቀቅ ለማድርግ ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን የሀላባ ዞን ትምህርት መምሪያ ዶ/ር ኤፍሬም ዘለቀ ገልጸዋል ።

አክለውም በነገው ዕለት የሚወስዱ ተማሪዎች ከመረጃ ጉዳይ ሙሉ በሙሉ ዝግጁ እና በስነ ልቦና የተገነቡ እንዲሆኑ እና ፈተና በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊ ጉዳዮችን ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን እንዳለባቸውም አሳውቀዋል ።

‎ተማሪዎች ፈተናው ከመጀመሩ በፊት በተነገራቸው ሰዓት በመገኘትና ፈተናውን ተረጋግተው መፈተን እንደሚጠበቅባቸው እና ተማሪዎች በሰአቱ እንዲገኙ መልዕክት አስተላልፏል ።

በኦርንቴሽን ለይ የተገኙት የሀላባ ዞን ትምህርት መምሪያ ሀላፊ ዶ/ር ኤፍሬም ዘለቀ የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ኑረዲን የፈተናው አስተባባሪ ፈተኛ መምህራን ተገኝቷል ።

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

“ከስምንት ቢሊዮን በላይ ችግኞች ለተከላ ዝግጁ በሆኑበት በዚህ ወቅት፣ አረንጓዴ ለሆነች ነገ፣ ሁላችንም ተስፋን እንትከል! “- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) #አረንጓዴአሻራ #የአየ...
13/06/2026

“ከስምንት ቢሊዮን በላይ ችግኞች ለተከላ ዝግጁ በሆኑበት በዚህ ወቅት፣ አረንጓዴ ለሆነች ነገ፣ ሁላችንም ተስፋን እንትከል! “- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

#አረንጓዴአሻራ
#የአየርንብረትለዉጥ
#ችግኝመትከል
#አካባቢጥበቃ

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያረጋገጡበት ነው -አቶ አደም ፋራህAMN ሰኔ 6 /2018 ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባ...
13/06/2026

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያረጋገጡበት ነው -አቶ አደም ፋራህ

AMN ሰኔ 6 /2018

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጡበት መሆኑን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ ገለጹ።

የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለተሳተፉና አዎንታዊ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የሲቪል ማኅበራት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሌሎች የዘርፉ ተዋንያን ባዘጋጀው ሀገር አቀፍ የዕውቅናና የምስጋና መርሐ ግብር አካሂዷል፡፡

በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ በዚሁ ወቅት፤ ምክር ቤቱ ምርጫው በስኬት መጠናቀቁን በማስመልከት ላዘጋጀው የዕውቅና መርሐ ግብር ምስጋና ይገባዋል ብለዋል።

የተቋም ግንባታ የሥልጣኔ መገለጫ መሆኑን የጠቀሱት አቶ አደም ፋራህ፤ ዴሞክራሲ ለኢትዮጵያ አማራጭ የሌለው የሕልውና እና የብልፅግና መሠረት መሆኑን አስገንዝበዋል።

ዴሞክራሲ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የምንገነባበት ምሰሶ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል ያሉት አቶ አደም፤ ሀገራዊ ተቋማትን በጋራ ጥረትና መሥዋዕትነት መገንባት እንደሚገባም አሳስበዋል።

በምርጫው ወቅት የሕዝቡ ንቁ ተሳትፎ ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ፅኑ ቁርጠኝነት በግልጽ ያሳየበት መሆኑንም አክለው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት በምርጫው ወቅት የነበረውን ንቁ ተሳትፎ አድንቀው፤ በተለይም ዜጎች ሕገ መንግሥታዊ መብቶቻቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ በማስተማርና ግንዛቤ በመፍጠር ረገድ ድርጅቶቹ ገንቢ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

የሲቪክ ማኅበራት ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ያላቸውን ሚና እንዲያሳድጉ ሰፊ ሥራ መሠራቱን የጠቀሱት አቶ አደም፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ የታየው ከፍተኛ ተሳትፎም ያለፈው ጥረታችን ውጤት ነው ብለዋል።

በቀጣይም የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን ይበልጥ ለማጠናከርና አጋርነታቸውን ለማስቀጠል መንግሥት ሙሉ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።

በፖለቲካው ምኅዳር በፉክክርና በትብብር መካከል ያለውን ሚዛን ጠብቆ የመሄድ ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ማስታወቃቸዉን።
ኢዜአ ዘግቧል።

በሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ በሁሉም ቀጠናዎች ተጠናክሮ ቀጥሏል።‎‎በሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ በሁሉም ቀጠናዎች የነዋሪዎች የ"ፋይዳ" ብሔ...
13/06/2026

በሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ በሁሉም ቀጠናዎች ተጠናክሮ ቀጥሏል።

‎በሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ በሁሉም ቀጠናዎች የነዋሪዎች የ"ፋይዳ" ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ በስፋት እየተካሄደ ይገኛል።

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከሰኔ 8/12/2018 ለመስጣት ለባለድርሻ አካለት የተዘጋጀ የኦረንተሺ...
13/06/2026

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከሰኔ 8/12/2018 ለመስጣት ለባለድርሻ አካለት የተዘጋጀ የኦረንተሺንና የምክክር መድረክ ተካሄደ!!!

የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በርካታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየቱን የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ኑረዲን ከድር ገልጸው ተማሪዎች የተዘጋጁበትን በሚገባ ተረጋግተዉ እንዲሰሩ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

በመድረኩ የፈተና አስተዳደርና አደረጃጀት መማሪያ የፈተናውን ዝግጅት፣ ስርጭት፣ ቁጥጥርና አጠቃላይ የደህንነት ስርዓት ላይ የሚያተኩር ሰነድ ቀርቦ ግንዛቤ ተፈጥሯል።

ተማሪዎች ተረጋግተው እንዲሰሩ በማድረግ የተሻለ ዉጤት እንዲያመጡ እና የፈተና አሰጣጥ ሂደቱን ስኬታማ ለማድረግ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ ነው ተብሏል።

በሁሉም ትምህርት ቤቶች ለሚገኙ ተማሪዎች የስነ-ልቦና ግንባታ በመስጠት በአቀላለም እና በሌሎችም በፈተና አወሳሰድ ሂደት ላይ የሚስተዋሉ ጉድለቶችን በማረም የተሻለ ውጤት እንዲገኝ መስራት እንደሚገባም ተመላክቷል።

በመድረኩ የትምህርት አመራሮች፣ የፀጥታ አካላት፣ የትምህርት ባለሙያዎች፣ የፈተና ጣቢያ ሱፐርቫይዘሮች፣ የትምህርት ቤት ርዕሰ መምህራንና ሌሎችም ተገኝተዋል።

የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከሰኔ 08 እስከ ሰኔ 12/2018 ዓ.ም ድረስ የሚሰጥ ይሆናል።

መልካም ዜና ለመላው ለሀላባ እና አካባቢው ህብረተሰብ የመብራት ቆጣሪ ፈላጊዎች በሙሉ!!!የሀላባና አከባቢው ነዋሪዎች የመኖሪያ ቤት መብራት ቆጣሪ 10% ብቻ ቅድመ ክፍያ በመክፈል የቆጣሪ ተጠ...
13/06/2026

መልካም ዜና ለመላው ለሀላባ እና አካባቢው ህብረተሰብ የመብራት ቆጣሪ ፈላጊዎች በሙሉ!!!

የሀላባና አከባቢው ነዋሪዎች የመኖሪያ ቤት መብራት ቆጣሪ 10% ብቻ ቅድመ ክፍያ በመክፈል የቆጣሪ ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ ተገልጿል።

ቀሪውን 90% (ዘጠና በመቶ) ክፍያ ለአገልግሎቱ ሳያሰጋዎት በቀጣዩች 24 ወራት (ሁለት ዓመታት) ውስጥ በተራዘመ ጊዜ ከፍለው የሚጨርሱበት ምቹ ሁኔታ ተመቻችቷል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ወላይታ ሪጅን የሀላባ አገልግሎት ማዕከል ስራ አስኪያጅ ኢ/ር ዘካሪያስ ወትቾ ይህ ልዩ እድል የሚቆየው ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ በመሆኑ የተሰጠውን አጭር ጊዜ በፍጥነት እንዲጠቀሙበት መልዕክት አስተላልፈዋል።

አገልግሎቱን ለማግኘት በተጠቀሱት ቀናት ውስጥ ወደ ሀላባ አገልግሎት ማዕከል በመምጣት በአንድ ቀን ውስጥ መስተናገድ ይችላሉ።

Address

Halaba
Alaba K'ulito

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት:

Share