15/06/2026
የሀላባ ዞን ዋና አስተዳደር ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን በዞኑ የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በይፋ አስጀመሩ
ሰኔ 8/2018 የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን በሀላባ ዞን በቁሊቶ ከተማ የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በይፋ አስጀምረዋል።
በይፋ መሰጠት የተጀመረው የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ለተከታታይ 2 ቀናት እንደምሰጥ ተገልጿል።
ተፈታኝ ተማሪዎችን በተረጋጋ መንፈስ ፈተናውን በመውሰድ እንደሚገባቸው ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን አበረታትተዋል።
በዞኑ የ2018 ትምህርት ዘመን ክልላዊ 6ኛ ክፍል ፈተና የሚወስዱ 3ሺህ 375 ተማሪዎች መሆናቸውን የዞኑ ትምህርት መምሪያ አስታውቀዋል።
በማስጀመሪያ መርሀ-ግብሩ ላይ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ት/ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊና የመማር ማስተማር ምዘና ዘርፍ ሀላፊ አቶ ማትዎስ ማልዳዬ፣ የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ከንቲባ ገመዳ መሀመድ፣ የሀላባ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ኤፍሬም ዘለቀ፣ ሌሎች የዞንና ከተማ አስተዳደር አመራሮች ተገኝተዋል።