በሀላባ ዞን የአቶቲ ኡሎ ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Alaba K'ulito
  • በሀላባ ዞን የአቶቲ ኡሎ ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

በሀላባ ዞን የአቶቲ ኡሎ ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ይህ የአቶቲ ኡሎ ወረዳ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ህጋዊ የሚዲያ ገፅ ሲሆን አጠቃላይ ወቅታዊና መደበኛ የመንግሥት ሥራዎች ዘወትር ይተላለፋል። ከታች ያለውን Follow በታን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

01/06/2026
በሀላባ ዞን አቶቲ ኡሎ ወረዳ በሁሉም ቀበሌዎችና የምርጫ ጠቢያዎች ማህበረሰቡ በነቂስ በመውጣት የሚወክለውን ፓርቲ መርጧል።
01/06/2026

በሀላባ ዞን አቶቲ ኡሎ ወረዳ በሁሉም ቀበሌዎችና የምርጫ ጠቢያዎች ማህበረሰቡ በነቂስ በመውጣት የሚወክለውን ፓርቲ መርጧል።

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ በክሪ አብደላ ፣በሀላባ ቁ.2 ምርጫ ክልል ለሀገራችን ይበጃል ያሉትን ፓርቲ በምርጫ ጣቢያ በመገኘት በምርጫ ካርዳቸው ድምፃቸውን ሰጥተዋል።
01/06/2026

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ በክሪ አብደላ ፣በሀላባ ቁ.2 ምርጫ ክልል ለሀገራችን ይበጃል ያሉትን ፓርቲ በምርጫ ጣቢያ በመገኘት በምርጫ ካርዳቸው ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ዋና  አስተዳደር ኢንጂነር አብዱልቃድር አማን ፣በሀላባ ቁ.2 ምርጫ ክልል ለሀገራችን ይበጃል ያሉትን ፓርቲ በምርጫ ጣቢያ በመገኘት በምርጫ ካርዳቸው ድምፃቸውን ሰጥተዋል።
01/06/2026

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ዋና አስተዳደር ኢንጂነር አብዱልቃድር አማን ፣በሀላባ ቁ.2 ምርጫ ክልል ለሀገራችን ይበጃል ያሉትን ፓርቲ በምርጫ ጣቢያ በመገኘት በምርጫ ካርዳቸው ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

ምርጫው የሀገራችንን ዴሞክራሲያዊ ሂደት ወደላቀ ደረጃ መሸጋገሩን የሚያመላክት ነው - ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን =====ግንቦት 24/2018 ‎በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ...
01/06/2026

ምርጫው የሀገራችንን ዴሞክራሲያዊ ሂደት ወደላቀ ደረጃ መሸጋገሩን የሚያመላክት ነው - ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን
=====

ግንቦት 24/2018 ‎በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን ድምጻቸውን ሰጥተዋል።

‎በሀላባ ዞን በዌራ ዲጆ ወረዳ ሀንጠዞ ቀበሌ የተዘጋጀው መንደር ነው ዋና አስተዳዳሪው ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን ድምጻቸውን የሰጡት።

የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን ድምፃቸውን ከሰጡ በኋላ በሰጡት አስተያየት፤ ምርጫ የሕዝብን ውክልና ለማረጋገጥና ማኅበራዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ልማቶችን በዘላቂነት ለማስቀጠል ትልቅ መሰረት የሚጥል ሂደት ነው ብለዋል።

ምርጫው የሀገራችንን ዴሞክራሲያዊ ሂደት ወደላቀ ደረጃ መሸጋገሩን የሚያመላክት ነው ሲሉም ተናግረዋል።

በዞኑ የዜግነት መብታቸውን በመጠቀም ያወጡትን ካርድ በየ ምረጫ ጣቢያው በመገኘት ብርድና ዝናብ ሳይበገሩ ለሚደግፉት ፓርቲው ድምጽ እየሰጡ መሆኑን ገልጸዋል።

በዞኑ በሁሉም የአከባቢው ህብረተሰብ የመምረጥ ባህል እያዳበረ የመጣ ታላቅ ህዝብ መሆኑን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ጠቁመዋል።

እያንዳንዱ መራጭ በምሰጠው የሰልፍ ስምረት ከጠዋት 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ተሰልፎ በመጠበቅ የምርጫ ስረዓተ ህጉን ባከበረው ያለ አንዳች እንከን የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

01/06/2026
‎የኢፌዴሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሒክማ ከይረዲን በሀላባ ቁ.1 ምርጫ ክልል ለሀገራችን ይበጃል ያሉትን ፓርቲ በምርጫ ጣቢያ በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።
01/06/2026

‎የኢፌዴሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሒክማ ከይረዲን በሀላባ ቁ.1 ምርጫ ክልል ለሀገራችን ይበጃል ያሉትን ፓርቲ በምርጫ ጣቢያ በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

በሀላባ 02 ምርጫ ክልል ሀላባ ፍሬ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ምርጫ ጣቢያ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የፓርኮች ኮርፖሬሽን ምክትል ስራ አስፈፃሚና የፓርላማ አባል ዶ/ር ነጃት ግርማ ተገኝተው ...
01/06/2026

በሀላባ 02 ምርጫ ክልል ሀላባ ፍሬ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ምርጫ ጣቢያ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የፓርኮች ኮርፖሬሽን ምክትል ስራ አስፈፃሚና የፓርላማ አባል ዶ/ር ነጃት ግርማ ተገኝተው ድምፅ ሰጥተዋል።

እንዲሁም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ- ጉባዔ ወ/ሮ መነቴ ሙኒዲኖ በገደባ 1ኛና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ምርጫ ጣቢያ በመገኘት ድምፃቸውን ሰጡ።
ደሬቴድ

“የትናንቷን ኢትዮጵያ የዛሬ አምስት ዓመት አናያትም” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ****************************ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ7ኛው...
01/06/2026

“የትናንቷን ኢትዮጵያ የዛሬ አምስት ዓመት አናያትም” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
****************************

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትውልድ ስፍራቸው በሻሻ በመገኘት ድምጻቸውን ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፣ ምርጫ የኢትዮጵያን መፃኢ ጊዜ የሚወስን ወሳኝ ሁነት መሆኑን ጠቅሰው፣ “የትናንቷን ኢትዮጵያ የዛሬ አምስት ዓመት አናያትም፤ የተለየች የበለጸገች ሀገር ማየት ደግሞ የሁሉም ኃላፊነት ነው” ብለዋል።

“እኔን ጨምሮ ዛሬ የምንወዳደረው ተመራጮች ትልቅ የሕዝብ አደራ አለብን፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገምባት ያለው ቁርጠኝነት የሚደነቅ ነው፤ ይህን ለማሳካት ደግሞ ምርጫ ወሳኝ ነው” ብለዋል።

ይህ ምርጫ በሰላም እንዳይጠናቀቅ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች የሚዘውሯቸው ኃይሎች በስፋት ሲሠሩ ነበር ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ “ኢትዮጵያ ውስጥ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ማድረግ አይቻልም” እያሉ ብዙ ቢሞክሩም እንዳልተሳካላቸው ገልጸዋል።

በትናንሽ ፕሮፓጋንዳዎች ሸብረክ የማይል እና ታሪክ መሥራት ልማዱ የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ በእነዚህ ኃይሎች ሳይዘናጋ በነቂስ በውጣት በመምረጥ ላይ ይገኛል፤ ይህም መካሪ እና ገሳጭ ሳያስፈልገው በራሱ ታሪክ እየሠራ እንደሚገኝ ማሳያ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያውያን በሚያስፈልግ ሰዓት መሰብሰብን መዝመትን እና አንድነትን በሚገባ ያውቁበታል ሲሉም ገልጸዋል።

“ይህን ሕዝብ ለማገልገል መመረጥን ይጠይቃል፤ ሁሉም ተመራጮች ሕዝብን ማዕከል አድርገው ሊሠሩ እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አሳስበዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ ዞን የሀላባ 2 ምርጫ ክልል በነገው ዕለት ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የቁሳቁስ ስርጭት ተጠናቋል=====ግንቦት 23/2018 የምርጫ ክልሉ ጽ/ቤት የሎጂ...
31/05/2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ ዞን የሀላባ 2 ምርጫ ክልል በነገው ዕለት ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የቁሳቁስ ስርጭት ተጠናቋል
=====

ግንቦት 23/2018 የምርጫ ክልሉ ጽ/ቤት የሎጂስቲክ ዘርፍ አስተባባሪ አቶ አበጋዝ አባኪያ እንዳሉት፤ በምርጫ ክልሉ በአጠቃላይ 1 መቶ 14 የምርጫ ጣቢያዎች መኖራቸውን እና የምርጫ ቁሳቁስ ሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች የማጓጓዝ ሥራ መከናወኑን ጠቅሰዋል፡፡

ከቁሳቁስ ሥርጭቱ ጎን ለጎን በየምርጫ ጣቢያዎቹ ለድምጽ አሰጣጥ ህደቱ የሚያስፈልጉ የቦታ ዝግጅት ስራዎች ተከናውነዋል።

በምርጫ ክልሉ ከ1 መቶ 60 ሺህ በላይ ዜጎች ድምጽ ለመስጠት የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውንም ጠቅሰዋል፡፡

አሁን ላይ በጣቢያዎቹ የምርጫ ቁሳቁስ ገብቶ ለድምጽ አሰጣጥ ሒደቱ ምቹ ሁኔታዎችን የመፍጠር ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝም ሃላፊው አረጋግጠዋል፡፡ #ደሬቴድ

Address

Atoti Ullo Guba
Alaba K'ulito

Telephone

+251916268290

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በሀላባ ዞን የአቶቲ ኡሎ ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share