14/06/2026
የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ የወቅታዊና መደበኛ ስራዎች አፈፃፀምና የቀጣይ ቀሪ ቀናት የትኩረት አቅጣጫ ላይ ዉይይት አካሄደ ፡፡
የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ሸምሱ ረሽድ በተገኙበት የወቅታዊ፤ መደበኛና የንቅናቄ ተግባራት አፈጻጸም በተጨማሪ የቀሪ 20 ቀን እቅድ ክለሳ ዝግጅት የደረሰበት ደረጃ ከወራደ ጤና ጽ/ቤት ሀላፊዎች እና ማኔጅሜንት ጋር በዘርቹዋል ተገምግሟል፡፡
በግምገማ መድረኩ የመደበኛ ተግባራት የደረሰበት አፈጻጸም ፣ የፋይዳ፤ኢትዮኮደርስ፤የመዐጤመ ስራዎች፤የወባ ወራርሽኝ መከላከልና ቅድመ ዝግጅት በተመለከተ፤የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ አፈፃፀም ያለበት ደረጃ፤የፅዱ ተቋማት እንሼቲብ፤የጤና ተቋሟት አገልግሎት አሰጣጥ እና የመልካም አስተዳደር ችግሮች በዝርዝር በስፋት ውይይት ተደርጓል ፡፡
በመድረኩ ማጠቃለያ የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ሸምሱ ረሽድ በዞኑ በጤና ልማት እየመጣ ላለው ከፍተኛ ውጤት መንግስት ለዘርፉ ከሰጠው ትኩረት በተጨማሪ ህብረተሰቡ ፣ በየደረጃው ያሉ የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ የአጋራ አካላት ሚና ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል ፡፡
የተመዘገቡ ውጤቶችን በቀጣይም ይበልጥ አጠናክሮ ማስቀጠልና በዉስንነት የተነሱትን መሻሻል ያለበትን የስራ መመሪያ በመመሪያዉ ኃላፊ ዶ/ር ሸምሱ ረሽድ የቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ተጠናቅቋል ።
በቨርቹዋል መድረኩ ለይ የወረዳ ጤና ጸ/ቤት ኃላፊዎች፤የሁለቱም ሆስፒታሎች ስራ አስከጆችና የማኔጅመንት አባላት ተገኝተዋል ፡፡