Halaba Zone Health Department - የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ

Halaba Zone Health Department - የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ This is the official Halaba Zonal Health Dept page you can get all the latest information’s.

Detail contact information to follow us:
https://halaba.gov.et/

የሀላባ ዞን ጤና  መምሪያ   የወቅታዊና መደበኛ ስራዎች አፈፃፀምና የቀጣይ ቀሪ ቀናት የትኩረት አቅጣጫ ላይ ዉይይት አካሄደ ፡፡ የዞኑ ጤና መምሪያ  ኃላፊ ዶ/ር ሸምሱ ረሽድ በተገኙበት  የ...
14/06/2026

የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ የወቅታዊና መደበኛ ስራዎች አፈፃፀምና የቀጣይ ቀሪ ቀናት የትኩረት አቅጣጫ ላይ ዉይይት አካሄደ ፡፡

የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ሸምሱ ረሽድ በተገኙበት የወቅታዊ፤ መደበኛና የንቅናቄ ተግባራት አፈጻጸም በተጨማሪ የቀሪ 20 ቀን እቅድ ክለሳ ዝግጅት የደረሰበት ደረጃ ከወራደ ጤና ጽ/ቤት ሀላፊዎች እና ማኔጅሜንት ጋር በዘርቹዋል ተገምግሟል፡፡
በግምገማ መድረኩ የመደበኛ ተግባራት የደረሰበት አፈጻጸም ፣ የፋይዳ፤ኢትዮኮደርስ፤የመዐጤመ ስራዎች፤የወባ ወራርሽኝ መከላከልና ቅድመ ዝግጅት በተመለከተ፤የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ አፈፃፀም ያለበት ደረጃ፤የፅዱ ተቋማት እንሼቲብ፤የጤና ተቋሟት አገልግሎት አሰጣጥ እና የመልካም አስተዳደር ችግሮች በዝርዝር በስፋት ውይይት ተደርጓል ፡፡

በመድረኩ ማጠቃለያ የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ሸምሱ ረሽድ በዞኑ በጤና ልማት እየመጣ ላለው ከፍተኛ ውጤት መንግስት ለዘርፉ ከሰጠው ትኩረት በተጨማሪ ህብረተሰቡ ፣ በየደረጃው ያሉ የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ የአጋራ አካላት ሚና ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል ፡፡

የተመዘገቡ ውጤቶችን በቀጣይም ይበልጥ አጠናክሮ ማስቀጠልና በዉስንነት የተነሱትን መሻሻል ያለበትን የስራ መመሪያ በመመሪያዉ ኃላፊ ዶ/ር ሸምሱ ረሽድ የቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ተጠናቅቋል ።

በቨርቹዋል መድረኩ ለይ የወረዳ ጤና ጸ/ቤት ኃላፊዎች፤የሁለቱም ሆስፒታሎች ስራ አስከጆችና የማኔጅመንት አባላት ተገኝተዋል ፡፡

14/06/2026
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት የ2019 የክትባት ዝርዝር ዕቅድ ዝግጅት(EPI Micro Plan) እና የ2018 ዓ.ም የ11 ወራት የእናቶችና ህጻናት ...
14/06/2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት የ2019 የክትባት ዝርዝር ዕቅድ ዝግጅት(EPI Micro Plan) እና የ2018 ዓ.ም የ11 ወራት የእናቶችና ህጻናት ዳይሬክቶሬት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሄደ።

ሰኔ 7/2018 በሸኖ

በዌራ ዲጆ ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት የ2019 የክትባት ዝርዝር ዕቅድ ዝግጅት(EPI Micro Plan) እና የ2018 ዓ.ም የ11 ወራት የእናቶችና ህጻናት ዳይሬክቶሬት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በዛሬው ዕለት ተካሂዷል።

ለመድረኩ የተዘጋጀ ሪፖርት በዌራ ዲጆ ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት የእናቶችና ህጻናት ዳይሬክቶሬት አቶ አስራት ባንትሮ አማካኝነት የ11 ወራት የእናቶችና ህጻናት ዳይሬክቶሬት አፈጻጸም ሪፖርት በዝርዝር የቀረበ ስሆን፣የ2019 የክትባት ዝርዝር ዕቅድ ዝግጅት(EPI Micro Plan) በአቶ ስለአባት አማካኝነት ቀርቧል።

የማጠቃለያ መድረኩን የዌራ ዲጆ ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሀይሻ አበቴ፣የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የክትባት ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ተስፋዬ አለሙ በጋራ መርተዉታል።

በዚህም ለመድረኩ በቀረበው የ2019 የክትባት ዝርዝር ዕቅድ ዝግጅት(EPI Micro Plan) እና የ2018 ዓ.ም የ11 ወራት የእናቶችና ህጻናት ዳይሬክቶሬት አፈጻጸም ዙሪያ ከመድረኩ ተሳታፊዎች በርካታ ሀሳብ አስተያየትና ጥያቄዎች ተነስተው፣በሰፊው ውይይት በማድረግ በቀጣይ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠል ደካማ ጎኖችን በማስቀረት መስራት እንደሚገባ አቅጣጫ በማስቀመጥ መግባባት በመቻል ተጠናቋል።

በመድረኩ የዞን ጤና መምሪያና የወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት የዘርፉ ባለሙያዎችና የጤና ጠቢያ ኃላፊዎች እንድሁም የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

ጥራቱን የጠበቀ የጤና አገልግሎት ለህብረተሰቡ ለመስጠት አፈጻጸምን መሰረት ያረገ ክፍያ ስርዓትን በማጠናከር በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተጠቆመየዌራ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የ2018 የሶስተኛ ሩብ...
14/06/2026

ጥራቱን የጠበቀ የጤና አገልግሎት ለህብረተሰቡ ለመስጠት አፈጻጸምን መሰረት ያረገ ክፍያ ስርዓትን በማጠናከር በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ

የዌራ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የ2018 የሶስተኛ ሩብ አመት አፈጻጸምን መሰረት ያደረገ የክፍያ ስርዓት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሄደ።

በዚህ ወቅት የዌራ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ገመቹ ኤዳሳ እንደገለጹት ጥራቱን የጠበቀ የጤና አገልግሎት ለህብረተሰቡ ለመስጠት አፈጻጸምን መሰረት ያረገ ክፍያ ስርዓትን በማጠናከር በትኩረት መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

በድክመት የተገመገሙ ተግባራትን ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት ማህበረሰቡን በጤና ተጠቃሚ ለማድረግ አፈጻጸሙን ማሻሻል እንደሚገባ ሁሉም ርብርብ ማድረግ ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን አፈጻጸምን መሰረት ያረገ ክፍያ ስርዓት በተመለከተ ኦዲት ማድረግ እንደሚገባ የተናገሩ ሲሆን በተለይም በጤና ዘርፍ የውስጥ ኦዲት መጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል።

በጤና ዘርፍ ተቋሞች እየተሰሩ ያሉ የእስካሁኑ አፈጻጸም በተሻለ ሁኔታ ተግባራዊ እያደረጉ በመሆኑን ተጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በጤና ዘርፍ የወረዳው ህብረተሰብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ባለድርሻ አካላት ለጉዳዩ ትኩረት መስጠት ይገባል ሲሉም ተናግረዋል።

የሀላባ ዞን ጤና መምሬያ ባለሞያ እና የዌራ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ደጋፊ ባለሞያ የሆኑት አቶ ነስረዲን ኑርዬ በበኩላቸው ተቋማት በሚያገኙት ገንዘብ አፈጻጸም መሰረት ያደረገ ክፍያ የህክምና አገልግሎቱን ለማሳለጥ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል።

በተለይም የህክምና ቁሳቁሶችን ከመግዛት እና ለባለሙያዎች ተገቢውን ክፍያ ከመፈፀም አንፃር በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

በኦዲት ስራ የሚታየው ክፍተት ወስዶ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

በበጀት አመቱ በጤና ዘርፍ አፈጻጸምን መሰረት ያደረገ የክፍያ ስርዓት ላይ በጥንካሬ የተፈጸሙ ተግባራትን ማስቀጠል በጉድለት የታየባቸውን ተግባራት ፈጥኖ በማረም ቀጣይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።

የ2018 በጀት ዓመት የጤና ተቋማት፣ የቦርድ ውይይት፣ የውስጥ ገቢ አሰባሰብና አጠቃቀም፣ የመንግስት መደበኛ በጀት፣ ያለክፍያ የሚሰጡ የጤና አገልግሎቶች አፈጻጸም ሪፖርት ተገምግሞው ቀጠይ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች የተሻሉ ተግባራቶችን በማስቀጠልና ውስንነቶችን በቀጣይ በጀት አመት ወስደው በትኩረት በመስራት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

በዚህ ግምገማ መድረክ የሀላባ ዞን አፈጻጸምን መሰረት ያደረገ ክፍያ ስርዕት አስተባባሪ አቶ አስቲሁን፣ የሀላባ ዞን ጤና መምርያ ከፍተኛ ባለሞያ የሆኑት አቶ ነስረዲን ኑርዬ፤ የጤና ጣቢያ ሀላፋዎች፤ የጤና ጣቢያ PBF ፎካሎች ፤የጽ/ቤት ደጋፊ ባለሞያዎች እና ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የ11 ወራት አፈጻጸም እና የ3ኛ ሩብ ዓመት lss ግብረመልስ መድረክ እየተካሄደ ነው**************(ሰኔ፣7/2018 ዓ.ም)ጉባ አ...
14/06/2026

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የ11 ወራት አፈጻጸም እና የ3ኛ ሩብ ዓመት lss ግብረመልስ መድረክ እየተካሄደ ነው
**************
(ሰኔ፣7/2018 ዓ.ም)ጉባ አቶቲ ኡሎ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የ11 ወራት አፈጻጸም እና የ3ኛ ሩብ ዓመት lss ግብረመልስ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

ለመድረኩ የዘጋጀውን ሰነድ የጤና ጽ/ቤት ልማት ዕቅድ በሆኑት በአቶ ሙሉብረሃን በስካል በኩል በዝርዝር እያቀረበ ይገኛል።

በመድረኩ ላይ የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሙፍቲ አወል፣የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ምክትል ሀላፊ አቶ ሸሪፉ ከድር፣እንዲሁም የዞን የወረዳው የጤና ጽ/ቤት ባለሙያዎች ከ21 ቀበሌ የተወጣጡ ጤና ኢክስትሽኖች ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላቶች ተገኝተዋል።

የጤና ባለሙያዎች ቁርጠኝነትና የሕብረተሰቡ ተሳትፎ በጤና ተቋማት ለውጥ ለማምጣት ቁልፍ ሚና ይጫወታል የዌራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ከዲር  የሴበሀላባ ዞን በዌራ ወረዳ ስር የሚገኙ ጤና ተ...
13/06/2026

የጤና ባለሙያዎች ቁርጠኝነትና የሕብረተሰቡ ተሳትፎ በጤና ተቋማት ለውጥ ለማምጣት ቁልፍ ሚና ይጫወታል የዌራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ከዲር የሴ

በሀላባ ዞን በዌራ ወረዳ ስር የሚገኙ ጤና ተቋማት የ2018 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት የሥራ አመራር ቦርድ ግምገማ እየተካሄደ ሲሆን በዛሬው እለትም በሀማጣ ሌንዳ ጤና ጣቢያ ተካሄዷል።

የዌራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ እና የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ከዲር የሴ የግምገማው መድረኩ በጤናው ዘርፍ አክሞ የማዳንና የመከላከል ሥራዎችን ለማጠናከርና የአገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን ፈር ቀዳጅ መሆኑን ተናግረዋል።

በሽታው አስቀድሞ ከመከላከል ባሻገር የታመሙትን አክሞ የማዳን ሥራ ለማጠናከር የባለሙያዎች አቅም ከማጎልበት ጀምሮ ቁሳቁስ የማሟላት ሥራ ለማጠናከር እንደምሰራ ጠቁመዋል።

መልካም ተሞክሮዎችን በመቀመር ማነቆዎችን በማረም ውጤት ማስመዝገብ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።

ከአመራር አካላት ጀምሮ የጤና ባለሙያዎች ቁርጠኝነትና የሕብረተሰቡ ተሳትፎ ለጤና ተቋማት ለውጥ ቁልፍ ሚና ይጫወታል ብለዋል።

የዌራ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ገመቹ ኤዳሳ ጤና ተቋማትን ለማጠናከር ከቦርድ አባላት ጀምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የተቋማትን አቅም ለማጎልበት በቅርበት መደገፍ እንደሚገባ በመግለጽ የተሻለ ሥራ መስራት ይገባል ብለዋል ።

በመድረኩ ላይ የዌራ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ሀላፊ እና የቦርድ አባል አቶ ሙሀመድ ገለቶ የዌራ ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ቢሮ ሀላፊ እና የቦርድ አባል አቶ ዲሌቦ በቲሻ የዌራ ወረዳ ሴቶችና ህጻናት ጽ/ቤት ሀላፊ እና የቦርድ አባል ወ/ሮ አምርያ ሁሴን እንዲሁም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትና የተቋሙ ባለሞያዎች ተገኝተዋል።

ከአምስት ዓመት በታች ለሆኑ ህጻናት አጣዳፊ የአመጋገብ ችግርን በማስተዳደር ላይ ያተኮረ ለጤና ባለሙያዎች እና ለአመጋገብ የማሻሻያ ስልጠና በአቶቲ ኡሎ ወረዳ የጤና ጽ/ቤት የተዘጋጀው የሰው ...
13/06/2026

ከአምስት ዓመት በታች ለሆኑ ህጻናት አጣዳፊ የአመጋገብ ችግርን በማስተዳደር ላይ ያተኮረ ለጤና ባለሙያዎች እና ለአመጋገብ የማሻሻያ ስልጠና በአቶቲ ኡሎ ወረዳ የጤና ጽ/ቤት የተዘጋጀው የሰው ኃይል ኦፕሬሽን በHCO ፕሮጀክትን በመተባበር ማነቃቂያ ስልጠና እየተሰጠ ነው
*************
(ሰኔ፣6/2018 ዓ.ም)ጉባ አቶቲ ኡሎ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ከአምስት ዓመት በታች ለሆኑ ህጻናት አጣዳፊ የአመጋገብ ችግርን በማስተዳደር ላይ ያተኮረ ለጤና ባለሙያዎች እና ለአመጋገብ የማሻሻያ ስልጠና በአቶቲ ኡሎ ወረዳ የጤና ቢሮ የተዘጋጀው የሰው ኃይል ኦፕሬሽን በHCO ፕሮጀክትን በመተባበር ማነቃቂያ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሙፍቲ አወል እንደገለጹት ወቅቱ የዓመቱ መጠቅለያ የሚደረግበት ወቅት መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት በአጭር ጊዜ በልተሰሩ ሥራዎች ላይ ትኩረት ልደረግባት ይገባል ብለዋል።

አያይዘውም ስልጠናው በጥሞና እንዲከታታሉና ከዚህ መድረክ መነሻ ውጤታማ ሥራዎች የጤና ባለሙያ እንዲሰሩ አሳስበዋል።

አቶ ሙፍቲ በ20ቀናት ከሚከናወነው ተግባራት አንዱ በሆነ በህጻናት ላይ በሚስተወሉ ጉዳቶች ላይ ትኩረት ተደርገው መሠረት ይገባል ብለዋል።

ስልጠናው ለተከታታይ ለ2ቀናት የሚቆይ መሆኑን ተገልጸዋል።

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዘግቧል !!

የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ የቁጥጥር ዘርፍ የማህበረሰቡን ጤና እና ደህንነት ለመጠበቅ በምግብ፣ በመድኃኒትና በጤና ነክ አገልግሎቶች ላይ ተከታታይ የኢንስፔክሽን ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱ ይታ...
12/06/2026

የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ የቁጥጥር ዘርፍ የማህበረሰቡን ጤና እና ደህንነት ለመጠበቅ በምግብ፣ በመድኃኒትና በጤና ነክ አገልግሎቶች ላይ ተከታታይ የኢንስፔክሽን ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱ ይታወቃል።

በዚህም ለህዝብ ጤና ጠንቅ የሆኑ ግኝቶች ሲኖሩ በየጊዜው ይፋ ማድረጉን ቀጥሏል። ​ይህንኑ ተፈጻሚ ለማድረግ፣ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የጤናና ጤና ነክ አገልግሎቶችና ግብዓቶች ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በወጣው መርሃ-ግብር (ስኬጁል) መሰረት ሰፊ የስምሪት ስራ ተከናውኗል።

የዞኑ ጤና መምሪያ የቁጥጥር ዘርፍ እና የአቶቲ ኡሎ ወረዳ የቁጥጥር ዘርፍ በጋራ በመሆን ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ለተከታታይ ሶስት ቀናት የዘለቀ ጥብቅ የድህረ-ገበያ ቅኝት (Post-marketing Campaign) አካሂደዋል።

​ይህ የቁጥጥር ስራ በአቶቲ ኡሎ ወረዳ በጉባ ከተማ ውስጥ በሚገኙ፦​በሸቀጣ ሸቀጥ ሱቆች፣​በቢራና መጠጥ ቤቶች፣​በስንዴ ዱቄት መሸጫዎችና በገበያ ቦታዎች፣ ​በእንጀራ መሸጫዎች፣ በወፍጮ ቤቶችና በባህላዊ የባልትና ማዘጋጃዎች ላይ ያተኮረ ነበር።

​በአጠቃላይ በ26 የጤና ነክ እና የምግብ ተቋማት ላይ በተደረገው በዚህ የድህረ-ገበያ ቅኝት ስራ ከፍተኛ የህግ ማስከበር እርምጃ የተወሰደ ሲሆን፣ የሚከተሉት ህገ-ወጥ ምርቶች ተለይተው እንዲሰበሰቡ ተደርጓል፦

​የተያዙ ህገ-ወጥ ምርቶች ዝርዝር፦
​የአገልግሎት ዘመናቸው ያለፈባቸው መጠጦች፦ በ12 የሸቀጣ ሸቀጥ ሱቆች ላይ የተደረገውን ፍተሻ ተከትሎ፣ ጊዜያቸው ያለፈባቸውና ለጤና አደገኛ የሆኑ 77 የሀይላንድ ኮካ ምርቶች ተለይተዋል። እነዚህ ምርቶች በገንዘብ ሲተመኑ ግምታቸው 5,390 ብር አካባቢ እንደሆነ ታውቋል።

​ህገ-ወጥ የትንባሆ ምርቶች፦ በህገ-ወጥ መልኩ ወደ ገበያ የገቡና ይዘታቸው ያልተረጋገጠ የተለያዩ የሲጋራ ምርቶች የተያዙ ሲሆን፣ የገንዘብ ግምታቸውም 8,590 ብር አካባቢ ይደርሳል።
​በመጨረሻም፣ የሀላባ ዞን ጤና መምሪያና የወረዳው የቁጥጥር ዘርፍ ማህበረሰቡ መሰል የአገልግሎት ጊዜያቸው ያለፈባቸውን ምርቶች ከመጠቀም እንዲቆጠብ አሳስበዋል።

በተጨማሪም ከባዕድ ነገሮች ጋር ከተቀላቀሉ፣ ሀገራዊ ደረጃቸውን ካላሟሉና በህገ-ወጥ መንገድ ከሚቀርቡ የምግብና መጠጥ ምርቶች ራሱን እንዲጠብቅ፣ ሲጠረጥርም ለተቆጣጣሪ አካላት ጥቆማ በመስጠት የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል።

ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር፣ ጤናማ መረጃ ወሳኝ ነው!!  ከሰኔ 8-12/18 ዓ/ም የመረጃ እና ዲጂታል ጤና ሳምንት በክልሉ በተለያዩ ኩነቶች ይከበራል።የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና...
12/06/2026

ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር፣ ጤናማ መረጃ ወሳኝ ነው!!

ከሰኔ 8-12/18 ዓ/ም የመረጃ እና ዲጂታል ጤና ሳምንት በክልሉ በተለያዩ ኩነቶች ይከበራል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ

በአቶቲ ኡሎ ወረዳ በጉባ ጤና ጣቢያ ግቢ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ ፋርማሲ ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።​የክልሉ መንግስት ግንባታውን በሁለት ወራት ጊዜ ...
08/06/2026

በአቶቲ ኡሎ ወረዳ በጉባ ጤና ጣቢያ ግቢ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ ፋርማሲ ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።

​የክልሉ መንግስት ግንባታውን በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ ለህብረተሰቡ አገልግሎት ለማስጀመር በትኩረት እየሰራ ይገኛል።

የሁሉም ባለድርሻ አካላትም ለስራው ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር እያደረጉ የሚገኙ ሲሆን ​ይህ ፋርማሲ ሲጠናቀቅ የማህበረሰቡን የመድኃኒት አቅርቦት ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።

ዘገባው የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ነው

Address

Halaba
Alaba K'ulito

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Halaba Zone Health Department - የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share