የሀላባ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ

የሀላባ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ Government Organization

ህዝባችን በምርጫው ያሳየዉን ቆራጥነት በዞኑ በተጀመሩ በሌሎች የልማት ዘርፎች ላይ ሊደግም ይገባል - ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን===========ግንቦት 25/2018 የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ...
02/06/2026

ህዝባችን በምርጫው ያሳየዉን ቆራጥነት በዞኑ በተጀመሩ በሌሎች የልማት ዘርፎች ላይ ሊደግም ይገባል - ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን
===========
ግንቦት 25/2018

የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሀላባ ዞን ባሉ የተለያዩ ምርጫ ክልሎች የተደረገው የምርጫ ሂደት ከድምጽ አሰጣጥ ጀምሮ እስከ ድህረ ምርጫ ድረስ በሰላም፣ በቅንጅት እና በትብብር በመጠናቀቁ ለመላው ለዞኑ ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በዚህም የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን እንደገለጹት የዞናችን ህዝብ በምርጫው ያሳዩትን ቆራጥነት በተጀመሩ በሌሎች የልማት ዘርፎች ሊደግሙት እንደሚገባ ገለጹ።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪው ገለጻ የዞኑ ህዝብ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ላሳየው ትዕግስትና ቆራጥነት ምስጋና አቅርበዋል።

በዞኑ በሚገኙ የተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ህዝቡ ከሌሊቱ 11 ሰዓት ጀምሮ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል፣ ዝናብና ፀሐይ ሳይበግራቸው ድምጻቸውን ሰጥተዋል ብለዋል።

የዞናችን ህዝብ ሁልጊዜም ለሀገራዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ያላቸውን ቀዳሚና የነቃ ተሳትፎ በከፍተኛ አክብሮት ማድነቃቸውን ተናግረዋል።

ለሀላባ ዞን ህዝብና ለመላው የሀገራችን ህዝቦች ዛሬ በዞናችንም ሆነ በሀገራችን ታሪክ አዲስ ምዕራፍ የተጻፈበት ታላቅ ቀን መሆኑን ገልጸዋል።

ዜጎች ሉዓላዊ ስልጣናቸውን በምርጫ ካርዳቸው አማካኝነት በነፃነት የሚገልጹበት 7ኛው ሀገራዊ እና ክልላዊ ምርጫ በሀላባ ዞን በሁሉም የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ፍጹም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ነፃ እና ስኬታማ በሆነ መልኩ ተጠናቀዋል ብለዋል።

ይህም የምርጫ ሂደት ማህበረሰባችን የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማስቀጠል ያለውን የበሰለ የፖለቲካ ባህል እና ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበት መሆኑን ተናግረዋል።

በሂደቱም የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች ላሳዩት ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ፉክክር፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ታዛቢዎችና ወኪሎች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካለት ላሳያችሁት የሀገርና የህዝብ ውግንና በዞኑ አስተዳደርና በሀላባ ህዝብ ምስጋና መቅረባቸውን ገልጸዋል።

በዞኑ የተካሄደው የምርጫ ሂደት ያለምንም የጸጥታ ስጋት ሙሉ በሙሉ ሰላማዊና ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ታላቅ ሀላፊነት ለተወጡ የጸጥታ አካላት፣ ለመላው የዞኑ ማህበረሰብ፣ እና ሌሎች ለሚመለከታቸው ባለድርሻ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በተለይም ሚዲያዎች በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት የምርጫ ሂደቱ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ወቅታዊና ፈጣን መረጃዎችን ለህብረተሰቡ በማድረሳቸው ምስጋና መልዕክት አስተላልፈዋል።

ከምርጫው ማግስትም መላው የዞናችን ነዋሪዎች የተለመደውን አንድነት፣ አብሮነት እና ወንድማማችነት ይበልጥ በማጠናከር፣ ፊታችንን ሙሉ በሙሉ ወደ ልማትና መልካም አስተዳደር ስራዎች በማዞር የጋራ ብልጽግናችንን ለማረጋገጥ በጋራ መቆም እንደሚገባ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

በመጨረሻም፣ በአሁኑ ወቅት በየምርጫ ጣቢያው የተለጠፉ ጊዜያዊ የምርጫ ውጤቶችን በትዕግስት በመመልከት፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋዊ ውጤት እስኪሰጥ ድረስ መላው የዞኑ ህዝብ በተለመደው ትብብር እንዲጠባበቅ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

የዞኑ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የውጤት አሰጣጥ የጊዜ ሰሌዳ
02/06/2026

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የውጤት አሰጣጥ የጊዜ ሰሌዳ

በድህረ ምርጫ ወቅት የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ምንድናቸው?======7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትናንትናው ዕለት በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ፣ ሀገራችን በአሁኑ ወቅት አዲስ የፖለቲካ፣ ማኅበራዊ ...
02/06/2026

በድህረ ምርጫ ወቅት የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ምንድናቸው?
======

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትናንትናው ዕለት በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ፣ ሀገራችን በአሁኑ ወቅት አዲስ የፖለቲካ፣ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አቅጣጫ የሚቀረጽበት ወሳኝ የድህረ ምርጫ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች፡፡

ይህ ወቅት የምርጫ ሂደት የመጨረሻው ምዕራፍና የሕዝብ ድምፅ ወደ ተግባራዊ መንግሥታዊ ሥራ የሚቀየርበት ወሳኝ ድልድይ ነው፡፡

በዚህ ወሳኝ የድህረ ምርጫ ምዕራፍ የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦

በየምርጫ ጣቢያው የተሰጡ ድምፆች በግልጽነት ተቆጥረውና ተረጋግጠው በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኩል ጊዜያዊ እና የመጨረሻ ውጤቶች ለሕዝብ ይፋ ይደረጋሉ፡፡

በተያያዥም የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች በሂደቱ ላይ ያስተዋሏቸውን ጠንካራና ደካማ ጎኖች የያዘ ይፋዊ መግለጫ እና ምክረ-ሀሳብ ያቀርባሉ፡፡

በሂደቱ ወይም በውጤቱ ላይ ቅሬታ ያላቸው ተፎካካሪ ፓርቲዎች ወይም የግል እጩዎች ያቀረቧቸውን አቤቱታዎች የምርጫ ቦርድ እና ፍርድ ቤቶች መርምረው ሕጋዊ ውሳኔ የሚሰጡበት ወቅት በመሆኑ፣ ማንኛውም ውዝግብ በሰላማዊና በሕጋዊ መንገድ ብቻ እንዲፈታ ይደረጋል፡፡

በተጨማሪም የምርጫ አስፈጻሚው አካል የሰው ኃይል፣ የቴክኖሎጂ እና የበጀት አጠቃቀሙን የሚገመግምበት ሲሆን፣ ሂደቱ በሰላማዊ መንገድ የፖለቲካ ሥልጣን ሽግግር የሚከናወንበት የሕግ የበላይነት መገለጫ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ሕዝብ ጽናት እና ታላቅነት፤ የታሪክ ማኅተም ያረፈበት የሉዓላዊነት አዲስ ምዕራፍ=====ግንቦት 25/2018 የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩ አስቸጋሪና ፈታኝ ወቅቶችን በጽናት የመሻገር፣ ...
02/06/2026

የኢትዮጵያ ሕዝብ ጽናት እና ታላቅነት፤ የታሪክ ማኅተም ያረፈበት የሉዓላዊነት አዲስ ምዕራፍ
=====

ግንቦት 25/2018 የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩ አስቸጋሪና ፈታኝ ወቅቶችን በጽናት የመሻገር፣ የሀገሩን ሉዓላዊነት እና አንድነት የማስጠበቅ ታላቅ ጥበብ እንዲሁም የማንነት አሻራ ባለቤት ነው፡፡

ትናንት በታሪክ አደባባዮች በጀግንነት የታየው ይህ የሀገር ፍቅር ተጋድሎ፣ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም ሕዝቡ ለሀገሩ ያለውን የማይናወጥ ታማኝነት እና ጽናት ዳግም ለመላው ዓለም ያሳየበት ደማቅ የታሪክ ምዕራፍ ሆኖ በወርቅ ቀለም ተመዝግቧል፡፡

በተለይም በዚህ ታሪካዊ ሂደት ላይ ማኅበረሰቡ የዜግነት ድርሻውን ለመወጣትና ድምጹን ለመስጠት ያሳየው ወደር የለሽ ቁርጠኝነት እጅግ የሚያስደንቅና በኩራት የሚነሳ ነው፡፡

ማንኛውም ዓይነት አስገዳጅ ሁኔታዎች፣ ጊዜያዊ ፈተናዎች እና ማነቆዎች ሳይገድቡት በማለዳው ብርድ እና በቀትሩ ፀሐይ ሳይበገር፣ ረጅም ሰዓታትን በትዕግሥት እና በሰላማዊ መንገድ በመጠበቅ ታላቅ ኃላፊነቱን በስኬት ተወጥቷል፡፡

ሕዝቡ ያሳየው ይህ ተአምራዊ ጽናት በድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ብቻ የተወሰነ ሳይሆን፣ የውጭ ጫናዎችን በቁርጠኝነት ለመቋቋምና የውስጥ ተግዳሮቶችን በአብሮነት ጥንካሬ ለማለፍ ያለውን ጥልቅ ፍላጎት በግልጽ ያነጸባረቀበት ነው፡፡

ከምንም በላይ ደግሞ ልዩነቶቹን በውይይት እና በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት መወሰኑ፣ የሠለጠነ ማኅበረሰብ እና የላቀች ጠንካራ ሀገር ለመገንባት ያለውን ጽኑ ራዕይ በተግባር ያሳየበት ደማቅ ክስተት ሆኗል፡፡

ይህ በዲሞክራሲያዊ መንገድ የወደፊት ዕጣ ፈንታውን በራሱ ለመወሰን ያደረገው ታላቅ ተጋድሎ፣ የሕዝቡን የላቀ የፖለቲካ ብስለት እና ለሀገር ህልውና ያለውን ቀናኢነት በተግባር ያረጋገጠ ነው፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይህንን ታላቅ ስኬት አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት የኢትዮጵያን ሕዝብ ታላቅነት በታላቅ አድናቆት ገልጸዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት "የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተአምረኛም ሕዝብ ነው። ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባህል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል" በማለት የሕዝቡን የጸና ጥንካሬ አውስተዋል፡፡

ይህ መልዕክት እንደሚያመላክተው ምንም ዓይነት ጊዜያዊ ማዕበል እና ፈተና የኢትዮጵያን የነገ ብሩህ ተስፋ ሊያጨልም አይችልም፡፡

የሕዝቡ አንጸባራቂ የሀገር ፍቅር ምንጊዜም የጸና መሆኑን ይህ ታሪካዊ ክስተት ትልቅ ማረጋገጫ ሆኗል፡፡ ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ክብር፣ ሰላም እና ዕድገት ሲሉ በጽናት ቆመው ለመጻኢ ጊዜ የሚሆን ብሩህ ውሳኔያቸውን በሉዓላዊ እጃቸው አሳልፈዋል፡፡

አሁን ግን ቀሪው ታላቅ ኃላፊነት የተመራጮች ትከሻ ላይ ያረፈ ነው፡፡ ሕዝቡ በዚህ ሁሉ ውጣ ውረድ ውስጥ አልፎ የሀገር አደራ የሰጣቸው ተመራጮች፣ ለሀገራችን ሁለንተናዊ ሰላም፣ ክብር እና ልማት ቀን ከሌት በታማኝነት መትጋት ይጠበቅባቸዋል፡፡

01/06/2026

ኢትዮጵያ መርጣለች

01/06/2026

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መግለጫ

ኢትዮጵያ መርጣለች፣ ጸንታለች፣ አሸንፋለች
01/06/2026

ኢትዮጵያ መርጣለች፣ ጸንታለች፣ አሸንፋለች

01/06/2026

ይሄንን ሕዝብ ማገልገል መታደል ነውና ተመራጮች ያከበራችሁን አክብራችሁ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ዋጋ የከፈለውን ይሄንን ሕዝብ በንጽሕና ለማገልገል ያብቃችሁ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

01/06/2026

Address

Alaba K'ulito

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሀላባ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የሀላባ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ:

Share