21/05/2026
በለዉጡ መንግስት የንፁህ መጠጥ ዉሃን ተደራሽነትን ለማስፋትና የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን የዌራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ገለፁ
ግንቦት 12/2018 በሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ በለዉጡ መንግስት የንፁህ መጠጥ የዉሃን ተደራሽነትን ለማስፋትና የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን የዌራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ከድር የሴ ገልፀዋል ።
ዋና አስተዳዳሪ አቶ ከድር የሴ ይህንን የገለፁት በዛሬው ዕለት በመንግሥት ትብብርና በመካና የሱስ ድርጅት ድጋፍ የሀቢቦ ፉራና ቀበሌ የንፁህ መጠጥ ዉሃ ቁፋሮ በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ ነው ።
ዋና አስተዳዳሪ አቶ ከድር የሴ በአከባቢ የንፁህ መጠጥ ውሃ በአቅራቢያው ባለመኖሩ ለዘመናት ማህበረሰቡ ስቸገሩ የነበሩበት በዛሬው ዕለት መፈታት መቻሉን ገልጸዋል።
አያይዘው መንግስት በጊዜ ሂደት የማህበረሰቡን ችግር ከግምት ውስጥ በማስገባት እየፈታ መሆኑን ጠቁመው አሁንም ቢሆን የህዝቡን አዳጊ የልማት ጥያቄ በየደረጃው ለመመለስ በልዩ ትኩረት እየሠራም ነው ብሏል ።
ስለዚህ ህዝቡ በለውጡ መንግስት እየተከናወነ ያለውን ልማት ሥራ በመንከባከብ ቀጣይም በዕቅድ ለመሥራት የተያዙ መሠረተ ልማትን ጨምሮ ሌሎች የልማት ሥራዎችን በትዕግሥት በመጠባበቅ ከመንግስት ጎን መሆን እንደሚገባው አስገንዝበዋል።
የሀላባ ዞን ውሃ ማዕዲን ኢነርጂ መምሪያ ሀላፊ አቶ አ/አዚዝ ከይራዲን በበኩላቸው ይህንን ሃብት የአካባቢው ህብረተሰብ በእንክብካቤ መጠበቅ እንዳለበት ገልፀዋል ።
የአከባቢዉ ማህበረሰብ በመንግስት ትብብርና በመካናየሱስ ድርጅት የንፁህ መጠጥ ውሃ በቅርበት አገልግሎት እንዲያገኝ ላደረገዉ ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል ።
የዌራ ወረዳ ውሃ ማዕድን ኢነርጂ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ መ/ሻፊ አሳሞ በበኩላቸው እንደገለፁት ለህብረተሰቡ አስፈላጊና መሠረታዊ ከሆኑ ልማቶች አንዱ የሆነውን የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር እንደ ወረዳ በዘላቂነት ለመፍታት በቀጣይ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በትኩረትና በቅንጅት ይሰራል ብለዋል።
በተለይ ከመሠረታዊ ፍላጎቶች እጅግ አስፈላጊ የሆነው ፍትሀዊ የንፁሁ የመጠጥ ውሃ ሽፋን በወረዳው ተደራሽነትን በማስፋት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል ።
በመርሃግብሩ ላይ የፕሮጀክቱ አስተባባሪዎች የቀበሌው አመራሮች እና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል ።