16/02/2026
በከተማዉ በኢኮኖሚ ዘርፍ በርካታ የልማት ስራዎች መከናወናቸዉን፦ ክቡር ከንቲባ አቶ ገመዳ መሀመድ ገለጹ፤
===============
የካቲቲ-09/2018ዓ.ም
በሀላባ ዞን የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 2ኛ ዙር 6ኛ አመት 19ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል።
የኢኮኖሚ ስራዎችን በተመለከተ የከተማ አስተዳደሩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች የግማሽ አመቱን የፊዝካል ስራዎች አፈፃፀም በመገምገም በሴክተሮች የታዩ ጠንካራ ጎኖችን እንዲቀጥሉና ታቅደዉ ያልተሰሩ ስራዎች በመለየት በቀጣይ ግማሽ አመት ተጠናክረዉ እንዲሰሩ ግብረ መልስ በመስጠት ተቋማትን አፈፃፀም መሠረት መመዘን መቻሉን ክብር ከንቲባዉ ገልጸዋል።
መንግስት የኑሮ ሁኔታን ደረጃ በደረጃ ለማሻሻል ፈጣንና ዘላቂ ልማትን እዉን ለማድረግ የልማት ፖሊስዎችን ፕሮግራሞችን ቀርፆ እየሰራ መሆኑን የጠቀሱት ከንቲባዉ በዝህም በትምህርት ቤቶች የስነህዝብ ክበባትን በማቋቋም የግንዛቤ ስራ መሰራቱንም አብራርተዋል።
በበጀት አመቱ 668,516,152 ብር በመደበኛና በማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ለገቢ አሰባሰቡ ዉጤታማነት ከዕቅድ ቅድመ ዝግጅት ምዕራፍ አንስቶ እስከ ተግባር ምዕራፍ ድረስ የባለድርሻዎች ቅንጅት በማጠናከር ከታቀደዉ 403,207,913 መሰብሰብ መቻሉን ከንቲባዉ በሪፖርታቸዉ አክለዋል።
የታክስ ህጎችን ከማክበር አኳያ በግማሽ አመቱ ጠንካራ የቁጥጥርና የኢንተለጀንስ ስራ በመስራት ከ56 በላይ ግብር ከፋዮች ወደ ጀረጃ "ሀ"ማሸጋገር መቻሉን የገለጹት አቶ ገመዳ በአከፋፈል ሂደቱ ደረሰኝ በአግባቡ ባልሰጡ 24 በግብር ከፋዮች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን ጠቁመዋል።
የግብርና ዘርፍ ለኢኮኖሚ ዕድገት እና ለድህነት ቅነሳ የሚያበረክተዉ አስተዋፆ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰዉ በግማሽ አመቱ በበልግ ወቅት 1,994 ሄክታር መሬት በተለያዩ የሰብል አይነቶች መሸፈን መቻሉን አብራርተዋል።
በመኸር ወቅትም 1,405 ሄክታር መሬት በተለያዩ የሰብል አይነቶች የተሸፈነ ሲሆን በአጠቃላይ በምርት ዘመኑ ከ120,394 በላይ ኩንታል ምርት መሰብሰብ መቻሉን አክለዋል።
በሌማት ትሩፋት ዘርፍ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በማርና በዶሮ ልማት 8 መንደሮችን መመስረት መቻሉን ጠቁመዋል ።
መሠረተ ልማት ስራዎችን በተመለከተ የመንገድ ልማት ተደራሽነትን ለማስፋት በተደረገዉ ጥረት 24 ኪ/ሜ አድስ የጥርጊያ መንገድና የከፈታ ለማድረግ መቻሉን ክብር ከንቲባዉ በሪፖርታቸዉ አሳይተዋል።
በህብረተሰብ ተሳትፎ 57,500,000 በጉልበት ማሳተፍ የተቻለ ስሆን ህብረተሰቡ በመሰረተ ልማት ግንባታዎች በገንዘብ በሃላባ ኢንተርናሽናል ስታድየም ግንባታ ፣ለኮሊደር ልማት እና ለደሃ ደሃ ቤት ግምባታ በብር 151,000 000 ሚሊዮን ብር እንዲሳተፉ መደረጉን ገልጸዋል።