01/06/2026
ምርጫው የሀገራችንን ዴሞክራሲያዊ ሂደት ወደላቀ ደረጃ መሸጋገሩን የሚያመላክት ነው - ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን
=====
ግንቦት 24/2018 በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን ድምጻቸውን ሰጥተዋል።
በሀላባ ዞን በዌራ ዲጆ ወረዳ ሀንጠዞ ቀበሌ የተዘጋጀው መንደር ነው ዋና አስተዳዳሪው ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን ድምጻቸውን የሰጡት።
የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን ድምፃቸውን ከሰጡ በኋላ በሰጡት አስተያየት፤ ምርጫ የሕዝብን ውክልና ለማረጋገጥና ማኅበራዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ልማቶችን በዘላቂነት ለማስቀጠል ትልቅ መሰረት የሚጥል ሂደት ነው ብለዋል።
ምርጫው የሀገራችንን ዴሞክራሲያዊ ሂደት ወደላቀ ደረጃ መሸጋገሩን የሚያመላክት ነው ሲሉም ተናግረዋል።
በዞኑ የዜግነት መብታቸውን በመጠቀም ያወጡትን ካርድ በየ ምረጫ ጣቢያው በመገኘት ብርድና ዝናብ ሳይበገሩ ለሚደግፉት ፓርቲው ድምጽ እየሰጡ መሆኑን ገልጸዋል።
በዞኑ በሁሉም የአከባቢው ህብረተሰብ የመምረጥ ባህል እያዳበረ የመጣ ታላቅ ህዝብ መሆኑን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ጠቁመዋል።
እያንዳንዱ መራጭ በምሰጠው የሰልፍ ስምረት ከጠዋት 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ተሰልፎ በመጠበቅ የምርጫ ስረዓተ ህጉን ባከበረው ያለ አንዳች እንከን የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።