በሀላባ ዞን አቶቲ ኡሎ ወረዳ ደን አካባቢ ጥበቃና ልማት ፅ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Alaba K'ulito
  • በሀላባ ዞን አቶቲ ኡሎ ወረዳ ደን አካባቢ ጥበቃና ልማት ፅ/ቤት

በሀላባ ዞን አቶቲ ኡሎ ወረዳ ደን አካባቢ ጥበቃና ልማት ፅ/ቤት ይህ በሀላባ ዞን የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ደንና አካባቢ ልማት ጥበቃ ጽሕፈት ቤት ትክክለኛ የፌስ ቡክ ገፅ ነው

ምርጫው የሀገራችንን ዴሞክራሲያዊ ሂደት ወደላቀ ደረጃ መሸጋገሩን የሚያመላክት ነው - ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን =====ግንቦት 24/2018 ‎በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ...
01/06/2026

ምርጫው የሀገራችንን ዴሞክራሲያዊ ሂደት ወደላቀ ደረጃ መሸጋገሩን የሚያመላክት ነው - ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን
=====

ግንቦት 24/2018 ‎በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን ድምጻቸውን ሰጥተዋል።

‎በሀላባ ዞን በዌራ ዲጆ ወረዳ ሀንጠዞ ቀበሌ የተዘጋጀው መንደር ነው ዋና አስተዳዳሪው ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን ድምጻቸውን የሰጡት።

የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን ድምፃቸውን ከሰጡ በኋላ በሰጡት አስተያየት፤ ምርጫ የሕዝብን ውክልና ለማረጋገጥና ማኅበራዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ልማቶችን በዘላቂነት ለማስቀጠል ትልቅ መሰረት የሚጥል ሂደት ነው ብለዋል።

ምርጫው የሀገራችንን ዴሞክራሲያዊ ሂደት ወደላቀ ደረጃ መሸጋገሩን የሚያመላክት ነው ሲሉም ተናግረዋል።

በዞኑ የዜግነት መብታቸውን በመጠቀም ያወጡትን ካርድ በየ ምረጫ ጣቢያው በመገኘት ብርድና ዝናብ ሳይበገሩ ለሚደግፉት ፓርቲው ድምጽ እየሰጡ መሆኑን ገልጸዋል።

በዞኑ በሁሉም የአከባቢው ህብረተሰብ የመምረጥ ባህል እያዳበረ የመጣ ታላቅ ህዝብ መሆኑን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ጠቁመዋል።

እያንዳንዱ መራጭ በምሰጠው የሰልፍ ስምረት ከጠዋት 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ተሰልፎ በመጠበቅ የምርጫ ስረዓተ ህጉን ባከበረው ያለ አንዳች እንከን የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

የ54 ሚሊዮን ዜጎች ድምጽ፤ የኢትዮጵያ ፖለቲካ አዲሱ አቅጣጫ*******************(የዕለቱ መልዕክት)ለዘመናት የኢትዮጵያ ፖለቲካ በጥርጣሬ ዉስጥ መኖሩ የአደባባይ ምስጢር ነው። ዛሬ ...
31/05/2026

የ54 ሚሊዮን ዜጎች ድምጽ፤ የኢትዮጵያ ፖለቲካ አዲሱ አቅጣጫ
*******************
(የዕለቱ መልዕክት)

ለዘመናት የኢትዮጵያ ፖለቲካ በጥርጣሬ ዉስጥ መኖሩ የአደባባይ ምስጢር ነው። ዛሬ ግን ያ የድሮው መንገድ አክትሞለታል። የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዋዜማ አዲስ ተስፋ ይዞልን መጥቷል፤ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች የተመዘገቡበት፣ በተለይ ደግሞ ከእነዚህም ዉስጥ ከ5.5 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ደግሞ በ“ምርጫዬ” ዲጂታል መድረክ ስማቸውን ያሰፈሩበት ይህ ሂደት፣ ሀገራችን ከጎዳና ጫጫታ ወደ ውይይት መድረክ፣ ከስሜት ወደ ዴሞክራሲያዊ ፉክክር መሸጋገሯን በግልጽ ያሳያል።

በዚህ ምርጫ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ከ10 ሺህ በላይ እጩዎችና 80 የግል ተወዳዳሪዎች በአንድ የህግ ጥላ ስር ቆመው፣ በምርጫ ስነ-ምግባር ሕግ ተሳስረው ለመወዳደር መዘጋጀታቸው የአዲሲቷ ኢትዮጵያ መለያ ነው።

ይህ ምርጫ የአንድ ቀን የድምፅ መስጠት ተግባር ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም የዴሞክራሲ ትርጉም ከፖለቲካ ልሂቃን ጠባብ አዳራሾች ወጥቶ ወደ ህዝብ ልብና ህሊና እየገባ መሆኑን የሚያበስር ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።

ውድድሩ ከብሽሽቅ ወደ ፖሊሲ ክርክር አድጓል። በርካታ የሕዝብ ውይይት መድረኮች በአምስት የሀገር ውስጥ ቋንቋዎች ተዘጋጅተው መቅረባቸው አካታችነትን በተግባር ያሳየ፣ የተፎካካሪና የገዢ ፓርቲዎችን እኩልነት በገሃድ ያረጋገጠ፤ የተቋማዊ ብስለት የታየበት እርምጃ ነው።

ዓለም አቀፍ እና የሀገር ውስጥ ታዛቢዎችን በኩራት ጋብዞ፣ የአፍሪካ ህብረትንና የኢጋድን ታዛቢዎችን በማሳተፍ አፍሪካ የራሷን ጉዳዮች በራስ አቅም የመመልከት አቅሟን ያሳየችበት እንዲሁም በሰላማዊ መንገድ ምርጫን ለማካሄድ መነሳት ራሱ ትልቅ ታሪካዊ ድል ነው። እንደ ኡሁሩ ኬንያታ ያሉ የአህጉሪቱ አንጋፋ መሪዎች የታዛቢ ቡድኖችን ይዘው መግባታቸው የኢትዮጵያን የዲሞክራሲ ጥረት በአፍሪካ መድረክ ከፍ አድርጎታል።

መልዕክቱ ግልጽ ነው፤ ፖለቲካ በሀይል ሳይሆን በህዝብ ድምፅ፣ በስሜት ሳይሆን በውይይት፣ በመገለል ሳይሆን በብሔራዊ ተሳትፎ ሊመራ እንደሚችል በተግባር እያሳየን ነው።

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ትልቁ ድል የትኛው ፓርቲ አሸነፈ የሚለው ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብና ተቋማት በዴሞክራሲያዊ ብስለት ማሸነፋቸው ነው።

ይህ የዲጂታል ዘመን ትውልድ የሀገሩን እጣ ፈንታ በራሱ እጅ እየጻፈ ነው። የነገዋን የበለፀገችና የተረጋጋች ኢትዮጵያን ለመገንባት ሁላችንም በሰላም፣ በህግና በውይይት መስመር ላይ እናጽና፤ ምክንያቱም የነጻነትና የፍትህ መሠረቱ የህዝብ ድምፅ ብቻ ነውና።

ኢትዮጵያ ትመርጣለች!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪ

1447ኛው የዒድ አልአድሃ (ዓረፋ) በዓል በዛሬው ዕለት በሀላባ ዞን በሀላባ ቁሊቶ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል። በዓሉ በዒድ መስገጃ ቦታ  በተክቢራ፣ በዒድ ሶላትና በዒድ መልዕክቶች በድምቀ...
27/05/2026

1447ኛው የዒድ አልአድሃ (ዓረፋ) በዓል በዛሬው ዕለት በሀላባ ዞን በሀላባ ቁሊቶ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል። በዓሉ በዒድ መስገጃ ቦታ በተክቢራ፣ በዒድ ሶላትና በዒድ መልዕክቶች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

በሀላባ ዞን አቶቲ ኡሎ ወረዳ“ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ ቃል የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ ቡና ጠጡ ፕሮግራም ተካሄደ ።=========(ግንቦት፣13/2018 ዓ.ም)ጉባ አ...
21/05/2026

በሀላባ ዞን አቶቲ ኡሎ ወረዳ“ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ ቃል የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ ቡና ጠጡ ፕሮግራም ተካሄደ ።
=========
(ግንቦት፣13/2018 ዓ.ም)ጉባ አቶቲ ኡሎ ሚዲያ በሀላባ ዞን አቶቲ ኡሎ ወረዳ“ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ ቃል የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ ቡና ጠጡ ፕሮግራም በጉባ ሸረሮና በሮ/ጤፎ ቀበሌ ተካሄዷል ።

በዛሬዉ እለት በሀላባ ዞን አቶቲ ኡሎ ወረዳ በሁለቱም ቀበሌዎች የክልል፣የዞንና የወረዳው አመራሮች በተገኙበት "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር!” በሚል የምርጫ ቅስቀሳ ቡና ጠጡ ፕሮግራም ተደርጓል ።

በዕለቱ ፓርቲው የጀመራቸውን ዘላቂ የልማትና የብልጽግና ጉዞዎች አጠናክሮ ለማስቀጠል ያላቸውን ቁርጠኝነት በማሳየት የተለያዩ የልማት ስራዎችን ተዟዙሮ ምልከታ ያደረጉ ሲሆን ህዝቡ በተለየዩ መፈክሮች ብልጽግና ፓርቲ የጀመራቸውን የልማት ስራዎች ለማስቀጠልና በመጪው ምርጫ ብልጽግናን ለመምረጥ በሁሉቱም ቀበሌዎች ደማቅ የቅስቀሳ ቡና ጠጡ ፕሮግራም ተካሂዷል ።

በዕለቱ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክርቤት ምክትል አፈጉባኤ ክብሪት መነቴ ሙንድኖ፣የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ምክትልና የፖለቲካ አቅም ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ አብድ መሀመድ፣የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ምክትልና አደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ አቶ በህረዲን ሪቦ እዲሁም የዞንና የወረዳ ደጋፊ አመራሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝቷል ።

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ዘርፍ ዘግቧል !!

21/05/2026
ለእያንዳንዱ የሰው ልጅ ስድስት ችግኞችን ያበረከተው አረንጓዴ አሻራ++++++++++++++++  | የአየር ንብረት ለውጥ በአሁኑ ወቅት የዓለማችን እና የኢትዮጵያ ዋነኛ ስጋት ነው፡፡ በተለያዩ...
16/05/2026

ለእያንዳንዱ የሰው ልጅ ስድስት ችግኞችን ያበረከተው አረንጓዴ አሻራ
++++++++++++++++

| የአየር ንብረት ለውጥ በአሁኑ ወቅት የዓለማችን እና የኢትዮጵያ ዋነኛ ስጋት ነው፡፡ በተለያዩ ምክንያቶች ወደአየር የሚለቀቀው በካይ ጋዝ መጨመር፤ የደን መጨፍጭፍ፤ የአፈር መራቆት፤ አካባቢን አለመንከባከብና መሰል ጉዳዮች የአየር ንብረት ለውጥን የሚያባብሱ ዋና ዋና ምክንቶች ናቸው፡፡

ይህ የአየር ንብረት ለውጥ መለዋወጥ ደግሞ ኢትዮጵያን ጭምሮ በተለያዩ ሀገራት ላይ ድርቅ እንዲከሰት እና የረሃብ አደጋ እንዲፈጠር፤ የጎርፍ አደጋ፤ በሰው እና በእንስሳት ላይ የረሃብና የሞት አደጋ በማስከተል ከፍተኛ የሆነ ተጽዕኖ እያስከተለ መሆኑን የተለያዩ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

በኢትዮጵያም በተለያዩ ዓመታት የተለያዩ የድርቅ አደጋዎች የተከሰቱ ሲሆን፤ እነዚህ የድርቅ አደጋዎች በህዝቡ ላይ ያስከተሉት የሞትና የረሃብ አደጋ በታሪክ አይረሴ ከሚባሉ ክስተቶች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

የሰውን ልጅ በከፍተኛ ሁኔታ እያሳሰቡ ያሉት የአየር ንብረት ለውጥና ሌሎች የተፈጥሮ አደጋዎች አጠቃላይ የምድርን ተፈጥሯዊ ሂደት እየጎዱት ነው፡፡

ኢትዮጵያ በታሪክና በተግባር የምታውቀውን ይህንን ክስተት ለመቋቋም በተለይ የለውጡ መንግስት ከመጣ በኋላ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን በመቅረጽ መተግበር ከጀመረች ዓመታት ተቆዋረል፡፡ ይህም ”ከምድራችን ጋር ያለንን ግንኙነት ከላስተካክልን የወደፊት ዕጣ ፋንታችን ማስተካከል አንችልም “ በሚል የተጀመረ ለችግሩ ዘላቄታዊ መፍትሔ ለመስጠት የተወጠነ ጅምር ነው፡፡

በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አፍላቂነት የተጀመረው ይህ የ'አረንጓዴ አሻራ' መርሃ ግብር ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በተከታታይ ዓመታት እየተተገበረ ነው፡፡

መርሃ ግብሩ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም፣ የአፈር ለምነትን ለመጠበቅ እና የሙቀት መጠንን ለመቀነስ እጅግ ከፍተኛ እና ዘርፈ ብዙ ጥቅሞችን እያስገኘ ያለ ሲሆን፣ በአፍሪካና በዓለም አቀፍ ደረጃ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ ስኬታማ ተነሳሽነት ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡

በአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም በየዓመቱ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን በሁሉም የሃገራችን ክፍሎች የዝናብ ወቅትን ጠብቆ የመትከልና የመንከባከብ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡

ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ባሉት ዓመታት በአጠቃላይ ወደ 48 ቢሊዮን የሚጠጉ ችግኞች መተከላቸውን በተለያየ ጊዜ የወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ይህ ተግባር በዚህ ዓመትም ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን 8 ነጥብ 5 ቢሌን ጭግኞችን ለመትከል መታቀዱን ከግብርና ሚኒስትር የተገኘው መረጃ ያሳያል፡፡

በባለፉት ዓማተት የተተኩሉ ችግኞች ውሃ ሃብትን በመጠበቅ፤ የአፈር መሸርሸርን በመከላከል፣ በየዓመቱ ይወድም የነበረውን ለም መሬት በመታደግ እና ወደ ወንዞች የሚገባውን ደለል በመቀነስ እንዲሁም የሙቀት መጠንን በመቀነስና አካባቢን ለኑሮ ምቹ በማድረግ በኩል ከፍተኛ ውጤት የተገኘባቸው ሁነዋል፡፡

በመንግስት ቁርጠኛ አቋምና በህብረተሰቡ ያልተቋረጠ ጥረት በየዓቱ በክረምት ወራት በንቅናቄ የተተገበረው የእግኝ ተከላ የሀገሪቱ የደን ሽፋን ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ እንዲያድግ ማስቻሉን የግብርና ሚኒስትር መረጃ ያመለክታል፡፡

በወንዞች ላይ የሚፈጠረው ደለል እንዲቀንስ እና በወንዞች ላይ ይከማች የነበረው 1 ነጥብ 9 ቢሊየን ቶን ዓመታዊ የደለል ክምችት ወደ 208 ሚሊየን ቶን እንዲቀንስ በማድረግ ለውሃ ሀብት ጥበቃ ትልቅ አስተዋጽዖ እያበረከተ ይገኛል።

ይህም ተግባር ሀገራችን በዓለም ትልቁ ዘላቂ የተፈጥሮ ሀብት ልማት መርሃ-ግብር የሚተገበርባት ሀገር እንድትሆን አስተዋፅዖው ከፍ ያለ ነው፡፡

በአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ፕሮግራም የደን ዛፍ ችግኝና ዘርፈ-ብዙ ጥቅም የሚሰጡ በአርሶ አደር ማሳ የሚተከሉ የጥምር ደን አካል የሆኑ የፍራፍሬ፣ የመኖና የማገዶ ዛፍ በተጨማሪም የከተማ ውበትን የሚያላብሱ ዛፎችን የመትከል ስራዎች ተከናውነዋል፡፡

ይህም ለደን ጥበቃ እና ለአረንጓዴ አካባቢ መፈጠር ከሚያበረክተው አስተዋጽኦ ባለፈ በለሙ ተፋሰሶች እና ባገገሙ መሬቶች ላይ ወጣቶች በንብ ማነብ፤ በአትክልትና ፍራፍሬና በእንስሳት ማድለብ ተግባራት በመሰማራት ኢኮኖሚያዊ ጠቃሚነታቸውን እንዲያረጋግጡ እድል የፈጠረ ተግባር ሁኗል፡፡

የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም ካለው ትልቅ ሀገራዊ የልማት ፋይዳ ባሻገር አለም አቀፍ ትኩረት፣ አድናቆት እና ምስጋና ያገኘ ሲሆን ሌሎች ሀገራትም የአየር ንብረት ለውጥን ለመዋጋት ለሚያደርጉት ጥረት ፕሮግራሙን በሞዴልነት መከተል ጀምረዋል፡፡

ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አረንጓዴ ኢኮኖሚ እየገነባች ሲሆን፤ ከዓለም አቀፍ ስምምነቶች አንጻርም ኢትዮጵያ የፓሪስ የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነት (Paris Agreement)፣ የ2030 የዘላቂ ልማት ግቦችን (SDGs) እና የአፍሪካ ህብረት 2063 አጀንዳ (Agenda 2063) ግቦችን በተግባር በመተግበር ረገድ በግንባር የምትጠቀስ ሀገር አድርጓታል፡፡

በአጠቃላይ ኢትዮጵያ እያከናወነችው ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ ለአየር ንብረት ለውጥ ዘላቂ መፍትሄ፣ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትና የፖለቲካ ቁርጠኝነት የተገነባበት የትውልድ ቅርስ ነው። ሌሎች ሃገሮች ምድርን ለመጠበቅ የሚያደርጉትን ተግባር የሚያነሳሳ ኢኒሼቲቭ ነው፡፡

በክብረአብ በላቸው

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ የብልፅግና ፓርቲን ወክለዉ በሀላባ ቁ.2 የምርጫ ክልል የቀረቡ እጩ ተወዳዳሪዎችኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር!      ብልፅግናን ...
15/05/2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ የብልፅግና ፓርቲን ወክለዉ በሀላባ ቁ.2 የምርጫ ክልል የቀረቡ እጩ ተወዳዳሪዎች

ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር!
ብልፅግናን ይምረጡ!

በሀላባ ዞን በአቶቲ ኡሎ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ የፐብሊክ ሰርቫንት የአባላት የ3ኛ ሩብ ዓመት ኮንፈረንስ ተካሄደ**************(ግንቦት፣4/2018 ዓ.ም)ጉባ አቶቲ ኡሎ መንግስት ኮሚ...
12/05/2026

በሀላባ ዞን በአቶቲ ኡሎ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ የፐብሊክ ሰርቫንት የአባላት የ3ኛ ሩብ ዓመት ኮንፈረንስ ተካሄደ
**************
(ግንቦት፣4/2018 ዓ.ም)ጉባ አቶቲ ኡሎ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን በሀላባ ዞን በአቶቲ ኡሎ ወረዳ "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር!" በሚል መሪ ቃል የብልፅግና ፓርቲ የ3ኛው ዙር የአባላት ኮንፍረንስ ተካሂዷል።

በመድረኩ ላይ በሁሉም ዘርፍ የሚገኙ የፐብሊክ ሰርቫንት የብልፅግና አባላት የየህብረታቸውን የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት አቅርበው ሰፊ ውይይት አካሂደዋል።

በመድረኩ የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር አብዱልቃድር አማን፣የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ በክሪ አብደላና የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ምክትል ሀላፊዎች ንግግር አድርገዋል።

አባላቱ የቀረቡ አጀንዳዎችን በጥልቀት ከመከሩባቸው በኋላ በማፅደቅ፣ በቀጣይ በሚከናወኑ የአባላት ማፍራት ተግባራት እና በምርጫ ዝግጅት ሥራዎች ዙሪያ በዝርዝር ተወያይተው አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

በተለይ የምርጫ ተግባራትን በቅንጅት ለመምራት የሚያስችል ውይይት የተካሄደ ሲሆን የብልፅግና ፓርቲ ዋነኛ ዓላማ ኢትዮጵያን ተምሳሌት የሆነች ሀገር ማድረግ መሆኑን በመግለጽ በዚህም ምርጫው ፍፁም ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ማድረግ የፓርቲው ቁልፍ ተግባር መሆኑም ተገልፀዋል።

ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት አመታት በርካታ የልማት ስራዎችን በመስራት ጠንካራ ፓርቲና አደረጃጀት በመገንባት አመርቂ ለውጥ ማስመዝገቡንና የ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ዴሞክራሲያዊና ስኬታማ እንዲሆን የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች በቆራጥነት መስራት እንዳለባቸው በመድረኮቹ ተቀምጠዋል።

የስንዴ ነዶ የእድገት ፣የትብብር፣የብልፅግና ተምሳሌት በመሆኑ የብልጽግና ፓርቲ አባሎችና ደጋፊዎች ይህንን ምልክት በመምረጥ ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር በምታደርገው ጉዞ ላይ የድርሻቸውን እንዲወጡም ተገልፀዋል።

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዘግቧል !!

በሀላባ ዞን አቶቲ ኡሎ ወረዳ በሁሉም ፐብሊክ ሰርቪስ ማህበራዊ መሰረት ብልፅግና ህብረቶች የ3ኛ ሩብ ዓመት የአባላት ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው*******************(ግንቦት፣4/201...
12/05/2026

በሀላባ ዞን አቶቲ ኡሎ ወረዳ በሁሉም ፐብሊክ ሰርቪስ ማህበራዊ መሰረት ብልፅግና ህብረቶች የ3ኛ ሩብ ዓመት የአባላት ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው
*******************
(ግንቦት፣4/2018 ዓ.ም)ጉባ አቶቲ ኡሎ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን በሀላባ ዞን አቶቲ ኡሎ ወረዳ በሁሉም ፐብሊክ ሰርቪስ ማህበራዊ መሰረት ብልፅግና ህብረቶች የ3ኛ ሩብ ዓመት የአባላት ኮንፈረንስ እየተካሄደ ይገኛል ።

ኮንፈረሱ ማለትም በአስተዳደር ዘርፍ በማህበራዊና በኢኮኖሚ ቁ.1 እና ቁ.2 የአባላት ኮንፈረንስ መድረክ እየተካሄደ ሲሆን የህብረቱ አመራሮች መድረኩን በመምራት ላይ ናቸው።

በመድረኩ ላይ የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ዋና አስተዳደር ኢንጂነር አብዱልቃድር አማን፣የአቶቲ ኡሎ ወረዳ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ በክሪ አብደላ እንዲሁም የወረዳው አስተባባሪዎችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላቶች ተገኝተዋል ።

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዘግቧል !!

በሀላባ ዞን በአቶቲ ኡሎ ወረዳ በለ መቃላ በመደበኛ በልግ የተዘራው የበቆሎ ሰብል ምልከታ ተደርገዋል ።
12/05/2026

በሀላባ ዞን በአቶቲ ኡሎ ወረዳ በለ መቃላ በመደበኛ በልግ የተዘራው የበቆሎ ሰብል ምልከታ ተደርገዋል ።

Address

Alaba
Alaba K'ulito

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በሀላባ ዞን አቶቲ ኡሎ ወረዳ ደን አካባቢ ጥበቃና ልማት ፅ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share