08/04/2022
🔑የሀላባ ቁሊቶ ከተማ መልሶ ማልማት ስራ ያለበትን ደረጃ እናስቃኛችሁ🔑
✅ከተሞች ከሚገጥማቸው ፈተናዎች መካከል የከተሞች ድቀት ወይም እርጅና አንዱና ዋናው ችግር ነው፡፡
✅የሀላባ ቁሊቶ ከተማ በከተማው መሀል አከባቢ በ1956-60ዎቹ ጀምሮ በግለሰቦች የተያዘ ቦታ በመልሶ ማልማት ድንቅ ስራ እተሰራ መሆኑን ማየት ችለናል፡፡
✅ለክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መረጃ የሰጡት የሀላባ ዞን የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ሀላፊ አቶ አንዋር ሲርጋፋ ከተማዋ የተቆረቆረችው ከዛሬ 100 ዓመት በላይ በመሆኑ በርካታ የደቀቁ ቦታዎች አሉ ብለዋል፡፡
✅ይሄንን የደቀቁ ቦታዎች መልሰን ማልማት እንዳለብን ከህብረተሰቡ ጋር መተማመን በመፍጠር እየተሰራ እንደሆነ አቶ አንዋር ገልጸዋሉ ፡፡
✅ከክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ጋር በመቀናጀት ግለሰቦቹ ሳይፈናቀሉ ባሉበት በማህበር ተደራጅተው በአካውንታቸው ቆጥበው መሬቱ ተሸንሽኖ ለኮመርሻል፣ ለአረጓዴ ልማት እንዲሁም ለኢንቨስትመንት እንዲህ በሚያምር መልኩ እንዲውል ተደርጓል ይላሉ አቶ አንዋር፡፡
✅ነዋሪዎቹም ከታች በፎቶ ላይ እንደሚናየው የሚያምር ገጽታ ያለው የመኖሪያ ቤት እየተገነባላቸው እንደሆነ አስተያየታቸውን ገልጿሉ፡፡
✅የተረፈው መሬትም ለተለያዩ አገልግሎቶች በማዋል የደቀቀውን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ህዝቡና መንግስት ማግኘት የሚገባውን ገቢ እያገኘ ይገኛል፡፡
✅አሁንም በመልሶ ማልማቱ በርካታ የሚሰሩ የከተማው ቦታዎች እንዳሉ የስራ ኃላፊው አቶ አንዋር ሲርጋፋ ተናግረዋል፡፡
✅የደቡብ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ የመሬት ልማት ማነጅመንት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ዝናቡ ተካቤ እንደ ቢሮ በተለያዩ ጊዜያት ግንዛቤ ተሰጦ በትኩረት እየተሰሩ ካሉ ስራዎች አንዱ የከተማ መልሶ ማልማት ነው ብለዋል።
✅ከሀላባ ቁሊቶ ከተማ መልሶ ማልማት ስራ ለሎች ከተማ ተሞክሮ መውሰድ አለባቸው ሲሉ ዋና ዳይሬክተሩ አክለው ገልጸዋል።
✅ይህ ተግባር የከተማ ገጽታን የሚቀይር፣ ገቢን የሚያሳድግና ለዜጎች የስራ ዕድልን የሚፈጥር ነው።
✅እንደ ኢንጅነር ዝናቡ ገለጻ ከደቀቁ የከተማ ቦታዎች የሚነሱ ሰዎች ካሳ ወይም ምትክ ቦታ መስጠት ተገቢ መሆኑን አስታውቀዋል።
✅በመልሶ ማልማት ስራ ሌሎች ከተሞችም እንደ ሀላባ ቁሊቶ ከተማ መረባረብ እንዳለባቸው ኢ/ር ዝናቡ አስገንዝበዋል።
✅ዋና ዳይሬክተሩ ቀጥሎ ለህብረተሰቡንና ለአመራሩ ግንዛቤ በማስፋት ወደ ሌሎች ከተሞች ማስፋፋት ተገቢ ነው ይላሉ።
✅በዲላ ከተማ፣ ወላይታ ዞንና ጉራጌ ዞን ከተሞችም ተመሳሳይ ስራዎች እንዳሉ ጠቁመው በሌሎች ከተሞች የማስፋቱን ስራ ክልሉ ልዩ ትኩረት ይሰጣል ሲሉም አክለው ገልጸዋል።
👉መረጃው የደቡብ ክልል ከተማ ልማትና ቤቶች ቢሮ ነው።