30/07/2023
Share # share
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መቀመጫን በሚመለከት በማህበራዊ ሚዲያ የተለያዩ መረጃዎች እየወጣ ይገኛል ። በዚህም አድስ እየተደራጀ ባለው ክልል ውስጥ ከሚገኙ ከተሞች የተሻለ ማእከላዊነት፣ መሰረተ-ልማት እንዲሁም በክልሉ የታቀፉ ብሄረሰቦች ከዚህ ቀደምም በሰላም ሰርቶ የሚኖርባት ከተማ በመሆኗ ሆሳዕና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መቀመጫ ሆና እንደምትመረጥ ጥርጥር የለንም። የሀዲያ ወጣቶች ማህበር ጉዳዩ መለው የሀዲያ ህዝብ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ህደቱን በንቃት እየተከታተለ ስሆን በህደቱ አድሎ እንዳይፈጸምና የሀዲያን ጥቅም የሚያስነካ ተግባር እንዳይኖር ሀዲያን በመወከል ለሚደራደሩ አካለት በሀዲያ ህዝብ ስም አደራ እንላለን። ውሳኔውን መላው የሀዲያ ህዝብ በትዕግሥት እየተጠባበቀ ስሆን የሀዲያን ጥቅም የሚፃረሩ ከፍትሃዊ አሰራር ውጪ የሚሆኑ ውሳኔዎች የሚኖሩ ከሆነ በሀዲያ ህዝብ ዘንድ ተቀባይነት የማያገኝ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን።
የሀዲያ ወጣቶች ማህበር