01/06/2026
በምሽት ተሰልፈው ለሚገኙ መራጮች ወ/ሮ መሪማ ታደሰ በነፃ ምግብና ውኃ እያቀረቡ ነው
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ መሪማ ታደሰ፤ የምርጫ ቦርድ የድምፅ መስጫ ሰዓቱን ማራዘሙን ተከትሎ በምሽት ተሰልፈው ድምፃቸውን ለመስጠት እየተጠባበቁ ላሉ ነዋሪዎች በራሳቸው ተነሳሽነት ምግብና ውኃ በነፃ እያቀረቡ ነው፡፡
ወ/ሮ መሪማ መራጩ ሕዝብ ሳይሰለችና ሳይደክም የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ ለማበረታታት ቆሎ፣ ውኃ፣ ዳቦ እና ሌሎች ቀለል ያሉ ምግቦችን እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡
በአሁኑ ወቅትም በክፍለ ከተማው የምርጫ ክልል 28 ሥር በሚገኙት የምርጫ ጣቢያዎች በርካታ መራጮች አሁንም ድረስ ተሰልፈው ተራቸውን እየተጠባበቁ መሆናቸው ታውቋል፡፡