FDRE Ministry of Justice/ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር

FDRE Ministry of Justice/ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from FDRE Ministry of Justice/ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር, Government Organization, Bambis, Jomo Kenyatta Avenue, Addis Ababa.
(1)

Our mission is to ensure that quality laws are enacted and implemented in order to build an effective and efficient criminal, civil, and administrative justice system that protects the interests of the Ethiopian government and people.

የጤና አገልግሎት ማስታወቂያ ዝግጅትና ሥርጭትመመሪያ ቁጥር 1134/2018 የያዛቸው አንኳር ጉዳዮች    መግቢያየጤና አገልግሎት አስተዳደር እና ቁጥጥር አዋጅ ቁጥር 1362/2017 በጤናው ዘ...
16/06/2026

የጤና አገልግሎት ማስታወቂያ ዝግጅትና ሥርጭትመመሪያ ቁጥር 1134/2018 የያዛቸው አንኳር ጉዳዮች
መግቢያ
የጤና አገልግሎት አስተዳደር እና ቁጥጥር አዋጅ ቁጥር 1362/2017 በጤናው ዘርፍ ያሉ አዳዲስ ጽንሰ-ሃሳቦችን አካቶ በመውጣት በሥራ ላይ ይገኛል። ከዚህ ጎን ለጎን አሁን ባለው የቴክኖሎጂ እና ማኅበራዊ ሚዲያ መስፋፋት ምክንያት አገልግሎት ሰጪ የጤና ተቋማት ወደ ማኅበረሰቡ የሚደርሱባቸው አማራጮች ሰፊ ናቸው። በመሆኑም ጤናን የተመለከተ የተሳሳተ ወይም የተጋነነ ማስታወቂያ በሰው ሕይወት ላይ ሊቀለበስ የማይችል አደጋ ከማስከተሉም ባሻገር በማኅበረሰቡ ዘንድ የተዛባ አመለካከት ይፈጥራል። አዋጅ ቁጥር 1362/2017 የጤና አገልግሎት ማስታወቂያን አስመልክቶ ዝርዝር መመሪያ እንደሚወጣ በአንቀጽ 48 ሥር የተደነገገ ሲሆን በዚህም መሠረት የጤና አገልግሎት ማስታወቂያ መመሪያ ቁጥር 1134/2018 ሊወጣ ችሏል። የመመሪያው ዓላማም የጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ግልጽነትና ተጠያቂነት ባለው መልኩ እንዲመሩ ማስቻል፣ የጤና አገልግሎት ማስታወቂያ የሚያዘጋጁና የሚያስተላላፉ አካላት ሙያዊ ሥነ ምግባርን የተከተለ እና የማኅበረሰቡን ባህል የጠበቀ ሥራ ለመሥራት የሚያስችል ሥርዓት መዘርጋት የሚሉት ናቸው። በዚህ ጽሑፍ ቁጥጥር ስለሚደረግባቸው የጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች፣ የተከለከሉ ተግባራትና የሚያስከትሉት ተጠያቂነት በአጭሩ ይዳሰሳል።

የጤና አገልግሎት ማስታወቂያ ምንነት
የጤና አገልግሎት ማስታወቂያ ማለት ከጤና አገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የጤና ተቋም ስም፣ አርማ፣ የንግድ ምልክት ወይም ዓላማ እንዲተዋወቅ ለማድረግ በማስታወቂያ ማሰራጫ መንገድ አማካኝነት የሚሰራጭ ማስታወቂያ አንደሆነ በመመሪያው አንቀጽ 2(2) ሥር ተመልክቷል። ስለሆነም የጤና አገልግሎት ማስታወቂያ የጤና ተቋማት የሚሰጧቸውን የሕክምና እና ጤና እንክብካቤ አገልግሎቶችን በተለያዩ ዘዴዎች ማለትም በሕትመት አማራጭ፣ በስርጭት ማለትም በቴሌቪዥንና ራዲዮ እንዲሁም በዲጂታል ሚዲያ አማራጮች መረጃ የሚያሰራጩበት ዘዴ ነው።

የጤና አገልግሎት ማስታወቂያ ዝግጅት ታሳቢ ሊያደርጋቸው ስለሚገቡ ሁኔታዎች
የጤና አገልግሎት ማስታወቂያ ዝግጅት ታሳቢ ሊያደርጋቸው የሚገቡ ጉዳዮች በመመሪያ ተካተዋል፡፡ ይኸውም፡-
 የቋንቋ አጠቃቀም
በመመሪያው አንቀጽ 4 መሠረት የጤና አገልግሎት ማስታወቂያ የታዳሚው ኅብረተሰብ
የሚናገረውን ቋንቋ እና አገላለጽ፣ አካል ጉዳተኞችንና ልዩ ፍላጎት ያላቸው የማኅበረብ ክፍሎችን ተጠቃሚነትና አካታችንት እንዲሁም አሻሚ ያልሆነ ወይም የሙያ ቃላት ያልበዙበት መሆን አለበት።
 የይዘት /Content/
የጤና አገልግሎት ማስታወቂያ ይዘት የጤና ፖሊሲን ያከበረ፣ የማኅበረሰቡን ጤንነት ወይም ደህንነት የጠበቀ፣ መልእክቱ የሚተላለፍለትን ታዳሚ ታሳቢ ያደረገ፣ የማኅበረሰቡን ባህልና እሴት የጠበቀ እና አገልግሎቱ በጤና ተቋሙ ስለመሰጠቱ የሚያሳይ መሆን እንዳለበት በአንቀጽ 5 ተመልክቷል፡፡በተጨማሪም የጤና ተቋሙን ሥም፣ ደረጃ፣ በደረጃው መሠረት የሚሰጠውን አገልግሎት እና አገልግሎቱ የሚሰጥበትን አድራሻ ያካተተ መሆን አለበት። ጤና ተቋሙ ስላገኘው እውቅና ወይም ሽልማት የሚያስተዋውቅ ከሆነም ሽልማቱ ወይም እውቅናው የተሰጠበትን ጊዜ እና ምክንያት፣ ሽልማቱን የሰጠው ተቋም እና ስለ ሽልማቱ ያሉ ሌሎች መረጃዎችን ያካተተ መሆን አለበት፡፡

በአንፃሩ “የሁሉም ምርጫ”፣ “ተቀዳሚ ምርጫ” መሰል ግነት የበዛባቸው አገላለጾችን መጠቀም የለበትም። ከዚህ ጋር ተያይዞ የአንድ የጤና ተቋምን የጤና አገልግሎት ማስታወቂያ የሚያሰራጭ ወይም የሚያዘጋጅ ሰው የጤና ተቋሙ አግባብነት ካለው አካል የተሰጠ ሕጋዊ የብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ያለው ስለመሆኑ የማረጋገጥ ኃላፊነት እንዳለበት በመመሪያው አንቀጽ 13 ስር ተደንግጓል።

 ሥነ-ምግባር /Ethics/
በመመሪያ አንቀጽ 6 መሠረት የቴና አገልግሎት ማስታወቂያ
• የሌሎች ጤና ተቋማትን አገልግሎት እና የጤና ባለሙያዎችን ክብር የማይነካ
• በጤና ተቋሙ ውስጥ አገልግሎት የሚሰጡ ባለሙያዎች ከሌሎች ባለሙያዎች የተሻሉ እና የተለየ የሙያ ብቃትና እውቀት ያላቸው አስመስሎ ከመግለጽ የተቆጠበ
• አገልግሎት ለመስጠት ልዩ የሆነ ንጥረ ነገር እንደሚጠቀም ወይም የተለየ ፈውስ የሚገኝበት ተቋም እንደሆነ አስመስሎ የማይገልፅ
• ተገልጋዮች የጤና ተቋሙን አገልግሎት ካላገኙ በጤናቸው ላይ ጉዳት እንደሚያደርስ የሚያሳይ (ፍርሃትን የሚፈጥር) አለመሆን
• የተገልጋይን ክብርና ሥነ-ልቦና የማይነካ እንዲሁም
• በዓለም ዓቀፍ እና በብሔራዊ ሕጎች ጥበቃ የሚደረግላቸውን እንደ ቀይ መስቀል፣ ቀይ ጨረቃ ወይም ቀይ ክሪስታል ሥሞች፣ አርማዎች ወይም ምልክቶችን ወይም የሌሎች ተቋማት፣ ሎጎዎች ከሚመለከተው አካል ፈቃድ ሳይይር በቀጥታ ወይም አሳሳች በሆነ መልኩ የማይጠቀም መሆን ይጠበቅበታል፡፡
 ምስክርነት /Testimony/
የጤና ተቋም የታካሚ ምስክርነትን የሚያካት ከሆነ በምስክርነት የሚሳተፈው ሰው ፈቃደኝነቱን በጽሑፍ መስጠትና በእርግጥም አገልግሎቱን በትክክል ያገኘ ሰው መሆን ያለበት ሲሆን በምስክርነት የሚሳተፈው ሰው ለአካላ መጠን ያልደረሰ ወይም የአዕምሮ ጤና ችግር ያለበት ወይም በራሱ መወሰን የማይችል ከሆነም ወላጅ፣ አሳዳጊ፣ ሞግዚት ወይም በሕግ ሥልጣን የተሰጠው ሰው የጽሑፍ ፈቃዱን መስጠት እንዳለበት በመመሪያው አንቀጽ 7 ተመልክቷል፡፡ በተጨማም የሚሰጠው ምስክርነት የተሰጠውን ህክምና የሚመለከት መሆን የለበትም፡፡
ሕጋዊ ክልከላዎችን መተላለፍ የሚያስከትለው የሕግ ተጠያቂነት
በአዋጅ ቁጥር 1362/2017 አንቀጽ 48 ሥር እንደተደነገገው የጤና አገልግሎት ማስታወቂያ በመገናኛ ብዙኃን ወይም በሌላ ዘዴ ሲተላለፍ ትክክለኛ፣ ተገቢ ወይም ወቅታዊ መሆን እንዲሁም የጤና ሙያን ሥነ ምግባር፣ የጤና ባለሞያውን ከብርና የሙያውን ሳይንሳዊ ይዘት የጠበቀ መሆን አለበት። እነዚህን ክልከላዎች መተላለፍ አስተዳደራዊ እና የወንጀል ተጠያቂነት የሚያስከትል ነው።

አስተዳደራዊ ቅጣት
በአዋጁ አንቀጽ 53 መሠረት በአዋጁ እና አዋጁን ተከትለው በሚወጡ ሕጎች የተደነገጉ ክልከላዎችን ተላልፎ መገኘት እንደተፈፀመው ጥፋት ክብደት ከማስጠንቀቂ ጀምሮ እስከ ፈቃድ መሰረዝ የሚደርስ አስተዳደራዊ እርምጃ ሊያስወስድ እንደሚችል የተደነገገ እንደመሆኑ ከጤና አገልግሎት ማስታወቂያ ጋር በተያያዙ ድንጋጌዎችን መጣስ አስተዳደራዊ ተጠያቂነት የሚያስከትል ይሆናል፡፡ በዚህም በመመሪያው አንቀጽ 11 መሠረት
• ክልከላ የተደረገባቸውን የቋንቋ፣ ይዘት እና ሥነ ምግባር መስፈርቶችን በመጣስ የጤና አገልግሎት ማስታወቂያ ያስተላለፈ ወይም እንዲተላለፍ ያደረገ የጤና ተቋም ከብር ከአስራ አምስት ሺ እስከ ብር ሀምሳ ሺ በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ
• ፍቃደኝነቱን በጽሑፍ ያልሰጠ ወይም አገልግሎቱን በትክክል ያላገኘ ሰውን የጤና አገልግሎት ማስታወቂያ ላይ በምስክርነት ያሳተፈ የጤና ተቋም ከብር ሀያ ሺ እስከ ብር ሀምሳ ሺ ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ
• አካለ መጠን ያልደረሰን ልጅ ወይም በራሱ መወሰን የማይችል ሰውን ከወላጅ፣ አሳዳጊ፣ ሞግዚት ወይም በሕግ ሥልጣን ከተሰጠው ሰው የጽሑፍ ፈቃድ ሳያገኝ በምስክርነት ያሳተፈ የጤና ተቋም ከብር ሀምሳ ሺ እስከ ብር መቶ ሺ በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ የሚቀጣ ይሆናል፡፡
በተጨማም
• ማንኛውም አስተላላፊ የሚያስተላልፈው የጤና መረጃ ትክክለኛ ስለመሆኑ ከሚመለከተው አካል ሳያረጋግጥ ካስተላለፈ፣ መረጃው ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን ሳያረጋግጥ ካስተላለፈ፣ ወቅታዊ የኅብረተሰብ የጤና አደጋና ወረርሽኝን ቅድሚያ መስጠትን ከጣሰ ከብር አስር ሺ እስከ ብር ሰላሳ ሺ በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል።

የወንጀል ቅጣት
ምንም እንኳን መመሪያው አስተዳደራዊ ቅጣቶችን ብቻ የደነገገ ቢሆንም ክልከላዎችን መተላለፍ የወንጀል ተጠያቂነትን እንደሚያስከትል በአዋጅ ቁጥር 1362/2017 አንቀጽ 55 (17) ሥር ተደንግጓል። በዚህም መሠረት ስለጤና አገልግሎት ማስታወቂያ የተደነገገውን ተላልፎ የተገኘ ማንኛውም
 የጤና ባለሙያ ከ6 ወር በማያንስና ከ1 ዓመት በማይበልጥ እሥራት
 የማስታወቂያ ድርጅት፣ የሚዲያ ተቋም ወይም የጤና ተቋም ከብር ሀምሳ ሺ በማያንስና ከብር አንድ መቶ ሺ በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል።

የቅሬታ አቀራረብና አፈታት
መመሪያውን ተመስርቶ አስተዳደራዊ ቅጣት የተወሰነበትና በውሳኔው ቅር ከተሰኘ አካል ከመመሪያ ጋር በተያያዘ ቅሬታ የሚቀርብበትን ሥርአት አስመልክቶ በፌደራል አስተዳዳር ሥነ ሥርአት አዋጅ ቁጥር 1183/2012 በተመለከተው መሠረት ወይም አግባብ ባለው የክልል ሕግ መሠረት ውሳኔውን ለሰጠው አግባብ ያለው አካል ቅሬታውን ማቅረብ እንደሚችል በመመሪያው አንቀጽ 12 ሥር ተደንግጓል።

ማጠቃለያ
የጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች የሙያ ሥነ ምግባርን የተከተሉ፣ የሕክምና ሳይንሳዊ ሂደትን ያከበሩ፣ የማኅበረሰቡን ባሕልና እሴት የጠበቁ ሊሆኑ ይገባል፡፡ በዚህ መነሻነትም የጤና አገልግሎት ማስታወቂያው ሊኖራቸው ስለሚገባው የቋንቋ አጠቃቀም፣ የይዘት እና የሥነ ምግባር ሁኔታ በመመሪያው የተደነገገ እንደመሆኑ የጤና ተቋማትም ሆኑ የጤና አገልግሎት ማስታወቂያ የሚያስተላለፉ አካላት በመመሪያው የተቀመጡ ጥብቅ መስፈርቶችን መከተል ይጠበቅባቸዋል።

በንቃተ ሕግና ሥልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ

የፍትሕ ሚኒስቴርን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆችን እና ድረ-ገፅን ይቀላቀሉ
Website
https://www.justice.gov.et
Facebook
https://www.facebook.com/MOJEthiopia/
(x) Twitter
https://x.com/MOJEthiopia
YouTube channel
https://youtube.com/...3701...
Telegram
https://t.me/fdreattorneyGeneral_externabo

ለኢ.ፌ.ዲ.ሪ መከላከያ ሚኒስቴር የመከላከያ ፍትሕ ዋና ዳይሬክቶሬት ኃላፊዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ነው*********************በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትሕ ሚኒስቴር የንቃተ ሕግና...
15/06/2026

ለኢ.ፌ.ዲ.ሪ መከላከያ ሚኒስቴር የመከላከያ ፍትሕ ዋና ዳይሬክቶሬት ኃላፊዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ነው
*********************
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትሕ ሚኒስቴር የንቃተ ሕግና ሥልጠና ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት በወንጀል ሕግና በወንጀል ሥነ-ስርዓት ሕግ እንዲሁም በፍትሐብሔር ሥነ-ስርዓት እና ማስረጃ ምዘና ላይ ያተኮረ ስልጠና ለኢ.ፌ.ዲ.ሪ መከላከለያ ሚኒስቴር የመከላከያ ፍትሕ ዋና ዳይሬክቶሬት ከተለያየ እዝ ለተውጣጡ ኃላፊዎች ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም መስጠት ጀምሯል፡፡

ስልጠናው በወታደራዊ ፍትሕ ላይ ለሚሰሩ ዐቃቢያነ ህግ በወንጀል ምርመራና ማስረጃ አሰባሰብ እንዲሁም በተጠርጣሪ አያያዝና ሰብዓዊ መብት አጠባባቅ ክህሎትን ለማጠናከር በተጨማሪም በፍትሐብሔር ጉዳዮች የመንግስትንና የሕዝብን ጥቅም በማስጠበቅ ላይ ያተኮረ የአቅም ግንባታ ስልጠና እንደሆነ ተገልጿል፡፡

ስልጠናው የሶስት ቀናት ቆይታ ያለው ሲሆን የወንጀል ፍትሕ ስርዓትና የወንጀል ህግ እንዲሁም የወንጀል አፈፃፀም ደረጃዎች፣ የወንጀል ምርመራ ምንነትና የሚመራባቸው የህግ ስርዓቶች በተጨማሪም የተጠርጣሪ አያያዝ ፣ቃል አቀባበልና አቆያየት የሚሉት በዛሬ ውሎ የተዳሰሱ ሲሆን፤ በቀጣይ ቀናት የወንጀል ምርመራ ኃላፊነትን አለመወጣት ስለሚያስከትለው ተጠያቂነት እና በምርመራ ወቅት የሚያጋጥሙ ችግሮችና የመፍትሄ ሀሳቦች በፍትሐብሔር ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ምዘና ላይ ትኩረት በማድረግ ውይይቶች እንደሚቀጥሉ ተጠቁሟል፡፡

በመድረኩ መክፈቻ ላይ እንደተገለፀው የፍትሕ ሚኒስቴር ከመከላከያ ሚኒስቴር ጋር ያለውን ተቋማዊ ግንኙነት አጠናክሮ እንደሚቀጥል የተገለፀ ሲሆን፤ ከአሁን በፊት በተመሳሳይ ርዕሰ ጉዳይ ለኢ.ፌ.ዲ.ሪ መከላከለያ ሚኒስቴር የመከላከያ ፍትሕ ዋና ዳይሬክቶሬት ዐቃብያነ ሕግ እና የህግ ባለሙያዎች ስልጠና መሰጠቱ ተወስቷል፡፡

በፍትሕ ሚኒስቴር ለሚገኙ አካል ጉዳተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ዐቃቢያነ ሕግ የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተሰጠ***********************የአቅም ግንባታ ሥልጠናው በአመራር ብቃትና ውሳኔ ሰጪነ...
15/06/2026

በፍትሕ ሚኒስቴር ለሚገኙ አካል ጉዳተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ዐቃቢያነ ሕግ የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተሰጠ
***********************
የአቅም ግንባታ ሥልጠናው በአመራር ብቃትና ውሳኔ ሰጪነት፣ በውጥረትና ስሜት አስተዳደር እንዲሁም በተግባቦት ክህሎቶች ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ አካል ጉዳተኛ ሠራተኞች በተቋሙ ውስጥ ያላቸውን የአመራርና ውሳኔ ሰጪነት ሚና ለማሳደግ፣ በአካል ጉዳትና በሥራ ጫና ምክንያት የሚፈጠሩ ውጥረቶችን በአግባቡ የመቆጣጠር ክህሎታቸውን ለማሻሻል እና ከሥራ ባልደረቦቻቸው ጋር ያላቸውን የላቀ የተግባቦት መስተጋብር ለማጎልበት ታስቦ የተዘጋጀ ነው።

ፍትሕ ሚኒስቴር ለአካል ጉዳተኛ ሠራተኞችና ተገልጋዮች ጥራት ያለው፣ አካታችና ተደራሽ የፍትሕ አገልግሎትን ለማረጋገጥ በተቋሙ የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ውስጥ አካቶ እየሠራ ይገኛል። ይህ ሥልጠናም የአካል ጉዳተኛ ሠራተኞችን ሁለንተናዊ አቅም በማጎልበት እምቅ ችሎታቸውን እንዲያወጡ ምቹ ዕድል የሚፈጥር መሆኑ ተገልጿል።

ከሥልጠናው ማጠናቀቂያ በኋላ በተቋሙ የዘርፉ ከፍተኛ አመራር በተገኙበት ከሰልጣኞች ጋር የውይይት መድረክ የተካሄደ ሲሆን፣ በዚህም ወቅት የተለያዩ አስተያየቶችና ጥያቄዎች ተነስተው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

በውይይቱ ወቅት እንደተጠቆመው፤ የአካል ጉዳተኛ ሠራተኞችና ተገልጋዮች ጉዳይ ስትራቴጂያዊ ምላሽ የሚያስፈልገው በመሆኑ፣ በተቋሙ የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ውስጥ በራዕይ፣ ተልዕኮ፣ እሴቶችና ዋና ተግባራት ላይ በማያሻማ መልኩ በግልጽ ተቀምጦ እየተተገበረ ይገኛል። ይህንን ውጤታማ ለማድረግም አዳዲስ አደረጃጀቶችን በማዋቀርና ነባሮችን በማጠናከር ተቋማዊ ሪፎርም መደረጉ ተመልክቷል።

በመጨረሻም፤ እንዲህ ዓይነት የውይይት መድረኮች ሠራተኞች ከሥራ ጋር ተያይዞ የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች በአፋጣኝ ለመፍታት ከማስቻላቸውም ባሻገር፣ በሠራተኞችና በከፍተኛ አመራሩ መካከል የጠበቀ መቀራረብ፣ መተባበርና መግባባት የሚፈጥሩ በመሆኑ ቀጣይነት ሊኖራቸው እንደሚገባ ተጠቁሟል።

የፍትሕ ሚኒስቴርን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆችን እና ድረ-ገፅን ይቀላቀሉ
Website
https://www.justice.gov.et
Facebook
https://www.facebook.com/MOJEthiopia/
(x) Twitter
https://x.com/MOJEthiopia
YouTube channel
https://youtube.com/...3701...
Telegram
https://t.me/fdreattorneyGeneral_externabo

በይቅርታ አሰጣጥ ሥርዓት እና በቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሄደ************************የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትሕ ሚኒስቴር  ከአውሮፓ ሕብረት ጋር በመተባበር ከክልል ፍት...
13/06/2026

በይቅርታ አሰጣጥ ሥርዓት እና በቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሄደ
************************
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትሕ ሚኒስቴር ከአውሮፓ ሕብረት ጋር በመተባበር ከክልል ፍትሕ ቢሮዎች እና ከማረሚያ ቤቶች የሥራ ኃላፊዎች ጋር በይቅርታ አቀራረብና አሰጣጥ መመሪያ እንዲሁም በጋራ ዕቅድ ዝግጅት ላይ ያተኮረ ውይይት ሰኔ 06 ቀን 2018 ዓ.ም በአዳማ ከተማ አካሂዷል።

የፍትሕ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ ውጤታማ የማረምና ማነፅ ሥርዓት መገንባት ወሳኝ በመሆኑ፣ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በ5 ዓመት ስትራቴጂካዊ ዕቅዱ ውስጥ ለዚህ ዘርፍ ልዩ ትኩረት መስጠቱ የተገለፀ ሲሆን፤ ይህም ከፌዴራል እስከ ክልል ያለውን ወጥ ያልሆነ አሰራር በማስቀረት የተቀናጀና ተመጋጋቢ አሰራር እንዲሰፍን ያስችላል ተብሏል።

በመድረኩ ሰፋ ያለ ማብራሪያ የተሰጠበት የይቅርታ አቀራረብና አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 1133/2018 መንግሥትን፣ ማኅበረሰቡንና ተጎጂ ወገኖችን ታሳቢ ያደረገ እና ቀደም ሲል በነበረው አሰራር ላይ የታዩ ክፍተቶችን በመሙላት፣ የይቅርታ አሰጣጥ ሂደቱ ግልጽ፣ ፍትሐዊ እና ወጥ በሆነ መንገድ እንዲመራ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተመላክቷል።

የማረምና ማነፅ ሥራው ሰፊና ጥንቃቄ የተሞላበት ተግባር በመሆኑ፣ ስራውን በበላይነት የሚመራና የሚያስተባብር ዳይሬክቶሬት ተቋቁሞ ወደ ሥራ የገባ ሲሆን፣ ይህም ተቋማዊ ዝግጁነት ጥፋተኞች ታርመውና ታንፀው ወደ ማኅበረሰቡ እንዲቀላቀሉ ለሚደረገው ጥረት ትልቅ አቅም እንደሚሆን ተጠቁሟል።

በተያያዘም በአገር አቀፍ ደረጃ ባሉ የፍትሕ ተቋማት መካከል መሰረታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ወጥ የሆነ የ"አንድ ዕቅድና አንድ ሪፖርት" ሥርዓትን ለመዘርጋት የሚያስችል ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የሥራ ኃላፊዎችና ተሳታፊዎች በቀረቡት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ካደረጉ በኋላ የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል። በመጨረሻም በተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ቀጣይ የሥራ አቅጣጫ ተሰጥቶ መርሃ ግብሩ ተጠናቋል።

የፍትሕ ሚኒስቴርን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆችን እና ድረ-ገፅን ይቀላቀሉ
Website
https://www.justice.gov.et
Facebook
https://www.facebook.com/MOJEthiopia/
(x) Twitter
https://x.com/MOJEthiopia
YouTube channel
https://youtube.com/...3701...
Telegram
https://t.me/fdreattorneyGeneral_externabo

ሁሉንም ዓይነት አድሏዊ የዘር ልዩነቶችን ለማስወገድ በተደረገው ዓለም አቀፍ ስምምነት የተጠቃለለ ወቅታዊ አገራዊ የአፈፃፀም ረቂቅ ሪፖርት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደረገ  ****...
12/06/2026

ሁሉንም ዓይነት አድሏዊ የዘር ልዩነቶችን ለማስወገድ በተደረገው ዓለም አቀፍ ስምምነት የተጠቃለለ ወቅታዊ አገራዊ የአፈፃፀም ረቂቅ ሪፖርት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደረገ
*******************
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የፍትሕ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ጋር በመተባበር የሁሉንም ዓይነት አድሏዊ የዘር ልዩነቶችን ለማስወገድ በተደረገ ዓለም አቀፍ ስምምነት (Convention on the Elimination of Racial Discrmination) የተጠቃለለ ወቅታዊ አገራዊ የአፈፃፀም ረቂቅ ሪፖርት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሰኔ 5/2018 ዓ.ም ውይይት አካሂዷል፡፡

አገራዊ የአፈጻፀም ሪፖርት ማዘጋጀት በስምምነቱ መሰረት የግል ግምገማ ለማካሄድ፣ ዓለም አቀፍ ግዴታን ለመወጣት፣ በሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተሳትፎ ለማድረግ፣ ትክክለኛውን የአገሪቱን የስብአዊ መብት ገፅታ ለዓለም አቀፉ ህብረተሰብ ለማስገንዘብ፣ አገራዊ ምክክርን ለማጎልበት፣ ከልማት አጋሮች ጋር በትብብር ለመስራት፣ የዓለም አቀፍ ባለሙያዎችን ምክክር እንዲሁም የተለያዩ አገራትን ለምድ ለማግኘት እና ችግሮችን ለመለየት የራሱ የሆነ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል፡፡

በውይይቱ ወቅት በተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ሥርዓት ውስጥ የዘር መድሎን መከላከል አንደኛውና ዋነኛው መሠረት መሆኑ የተወሳ ሲሆን፣ ይህንን የመብት ጥሰት በሁሉም ደረጃ ለመከላከልና ኢትዮጵያ የተቀበለቻቸውን ስምምነቶች በማክበርና በማስከበር ረገድ መንግሥት የበኩሉን ኃላፊነት እየተወጣ እንደሚገኝ በመጠቆም፡ ይህንን አገር አቀፍ የአፈጻፀም ሪፖርት ምሉዕ፣ ወቅታዊና ተዓማኒ ለማድረግም መንግሥታዊ አካላት እና መንግስታዊ ያልሆኑ የሲቪል ማኅበረሰብ ተቋማት መረጃዎችንና ሙያዊ ምክረ-ሐሳቦችን በግብዓትነት በማቅረብ የሚጠበቅባቸውን አገራዊ ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች በስምምነቱ መሠረት የፈራሚ አገራትን ዋና ዋና ግዴታዎች በስፋት የዳሰሱ ሲሆን ፈራሚ አገራት የዘር መድሎ ድርጊቶችን በቀጥታ ከመፈጸም መቆጠብ፣ በሌሎች አካላት እንዳይፈጸም የመከላከልና የቁጥጥር ሥርዓት መዘርጋት፣ እንዲሁም ለጥሰቱ ተጋላጭ የሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎችን በልዩ ሁኔታ የመጠበቅ ኃላፊነት እንዳለባቸው በማብራራት ሰብዓዊ መብቶችን የሚያስከብሩ ተቋማትን ማጠናከርና በዘር ላይ የተመሠረቱ ማናቸውንም ዓይነት የጥላቻ ቅስቀሳዎችን በሕግ መከላከል የስምምነቱ መሠረታዊ ጉዳዮች መሆናቸው ተገልጿል።

በመጨረሻም ቀደም ሲል ከኢትዮጵያ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቀርቦ ከነበረው የአፈጻጸም ሪፖርት የተገኙ ግብረ-መልሶችንና ምክረ-ሃሳቦችን እንዲሁም ወቅታዊውን የአገሪቱን ተጨባጭ ሁኔታ መሠረት በማድረግ በተዘጋጀው በዚህ ረቂቅ የአፈጻፀም ሪፖርት ላይ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን ከተሳታፊዎች የተሰበሰቡ ጠቃሚ አሳቦችና ገንቢ አስተያቶች በግብዓትነት ተይዘው እንዲሁም ቀጣይ ሥራዎች ተመላክተው ውይይቱ ተጠናቋል።

የፍትሕ ሚኒስቴርን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆችን እና ድረ-ገፅን ይቀላቀሉ
Website
https://www.justice.gov.et
Facebook
https://www.facebook.com/MOJEthiopia/
(x) Twitter
https://x.com/MOJEthiopia
YouTube channel
https://youtube.com/...3701...
Telegram
https://t.me/fdreattorneyGeneral_externabo

ባህላዊ ጥበብን ከሰብዓዊ መብት እሴቶች ጋር በማጣጣም ለሁሉም ዜጎች ፍትሕን ተደራሽ ማድረግ የጋራ ኃላፊነት እንደሆነ ተመላከተ***********************በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክል...
12/06/2026

ባህላዊ ጥበብን ከሰብዓዊ መብት እሴቶች ጋር በማጣጣም ለሁሉም ዜጎች ፍትሕን ተደራሽ ማድረግ የጋራ ኃላፊነት እንደሆነ ተመላከተ
***********************
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በሚገኙ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ውስጥ ለሚያገለግሉ ሽማግሌዎች የሰብዓዊ መብት ጥበቃን መሠረት ያደረገ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና በቦንጋ ከተማ መሰጠት ተጀምሯል።

በመድረኩ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች በማኅበረሰቡ ዘንድ ያላቸውን ተቀባይነትና በፍትሕ አገልግሎት ተደራሽነት የሚያበረክቱት ሚና የተወሳ ሲሆን፣ የሽማግሌዎች ውሳኔዎች ከሰብዓዊ መብት መርሆች፣ ከሕገ መንግሥታዊ እሴቶች እና ከፍትሕ መርሆች ጋር ተጣጥመው እንዲተገበሩ የአቅም ግንባታ ሥራዎች ወሳኝ መሆናቸው ተገልጿል።

ሥልጠናው በባህላዊ ፍርድ ሥርዓቶች ውስጥ የሚያገለግሉ ሽማግሌዎች በሰብዓዊ መብት ጥበቃ፤ በተጋላጭ ቡድኖች መብቶች አክብሮት፤ በፍትሐዊ የውሳኔ ሂደት እና በዘመናዊ የፍትሕ መርሆች ዙሪያ ያላቸውን ግንዛቤና ክህሎት ለማጎልበት ያለመ መሆኑ ተገለጿል፡፡

ባህላዊ ፍርድ ቤቶች በማኅበረሰቡ ውስጥ የሚነሱ አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ በመፍታት የማኅበራዊ አንድነትን እና መተማመንን በማጠናከር ከፍተኛ አስተዋፅኦ የሚያበረክቱ በመሆናቸው፣ እነዚህን ተቋማት በእውቀትና በክህሎት ማጠናከር የፍትሕ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እና የዜጎችን መብት ለማስከበር የሚያስችል ጉልህ እርምጃ መሆኑ ተጠቁሟል።

የሥልጠናው አፈጻጸም በፍትሕ ሚኒስቴር፤ በተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) እና በሂል (Hill) በጋራ ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ፣ አካታች እና ሰብዓዊ መብትን ያከበረ የፍትሕ ሥርዓት ለመገንባት ከሚደረጉ ጥረቶች አንዱ መሆኑ ተገልጿል።

በመርሃ-ግብሩ ላይ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትሕ ሚኒስቴር የተቋም ግንባታ እና ሪፎርም ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶክተር ኤርሚያስ የማኔብርሃንን ጨምሮ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት፤ የክልሉ ፍትሕ ቢሮ ኃላፊዎች፤ የፍትሕ ዘርፍ ባለሙያዎች እና ሌሎች አመራሮች ተገኝተዋል።

የፍትሕ ሚኒስቴርን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆችን እና ድረ-ገፅን ይቀላቀሉ
Website
https://www.justice.gov.et
Facebook
https://www.facebook.com/MOJEthiopia/
(x) Twitter
https://x.com/MOJEthiopia
YouTube channel
https://youtube.com/...3701...
Telegram
https://t.me/fdreattorneyGeneral_externabo

የፍትሕ ሚኒስቴር የባህል ፍርድ ቤቶች ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ************************* የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትሕ ሚኒስቴር ከUni...
11/06/2026

የፍትሕ ሚኒስቴር የባህል ፍርድ ቤቶች ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ
*************************
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትሕ ሚኒስቴር ከUnited Nations Development Programme እና Hague Institute for Innovation of Law ጋር በመተባበር ለደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ሺሺንዳ ሞዴል ባህላዊ ፍርድ ቤት የቢሮ ዕቃዎች እና ለሽማግሌዎች የአቅም ግንባታ የሥልጠና የወጪ ድጋፍ አደረገ።

የሞዴል የባህል ፍርድ ቤቱ ይፋዊ የሥራ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር የፍትሕ ሚኒስቴር የተቋም ግንባታና ሪፎርም ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኤርምያስ የማነብርሃንን ጨምሮ የሺሺንዳ ከተማ ከንቲባ፤ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት፤ የክልሉ ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ እንዲሁም የማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር በተገኙበት ሰኔ 4/2018 ዓ.ም ተካሂዷል፡፡

በመርሃ-ግብሩ ወቅት እንደተገለፀው በክልሉ 700 ቀበሌዎች ላይ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች የተቋቋሙ ሲሆን፤ በበጀት ዓመቱ ብቻ 1‚700 በላይ መዛግብቶችን መታየት ችለዋል፡፡

የፍትሕ ሚኒስቴርም በክልሉ የባህል ፍርድ ቤቶች ተደራሽነትን ለማረጋገጥ እና የተቋቋሙትን አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚደረገውን እንቅስቃሴ ከአጋር አካላቶቹ ጋር በመሆን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳታውቋል፡፡

በነገው እለትም የድጋፉ አካል የሆነው የባህል ፍርድ ቤት ሽማግሌዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና መርሃ-ግብር እንደሚጀምር ተጠቁሟል፡፡

በኢትዮጵያ እና ናይጄሪያ መንግስታት መካከል ፍርደኞችን ለማስተላለፍ የሚያስችል የሁለትዮሽ ስምምነት አደረጉ************************በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና...
11/06/2026

በኢትዮጵያ እና ናይጄሪያ መንግስታት መካከል ፍርደኞችን ለማስተላለፍ የሚያስችል የሁለትዮሽ ስምምነት አደረጉ
************************
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በናይጄሪያ ፌዴሬሽን መካከል ፍርደኞችን ለማስተላለፍ የሚያስችል የሁለትዮሽ ስምምነት የፊርማ ሥነ ሥርዓት ሰኔ 03 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተከናውኗል።

በኢትዮጵያ በኩል ስምምነቱን የፈረሙት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የፍትሕ ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሐና አርዓያስላሴ ሲሆኑ በናይጄሪያ በኩል የሀገሪቷ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግና የፍትሕ ሚኒስትር ክቡር ሚ/ር Lateef Olasunkanmi Fagbemi ናቸው።

በፈርማ ሥነ ሥርዓቱ የሁለቱ አገራት ግንኙነት ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ መሆኑ የተነሳ ሲሆን አገራቱ በተለያዩ ዘርፎች በትብብር በመስራት ላይ ስለመሆናቸው ተጠቅሷል። በፍትሕ ዘርፍ ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር የተፈረመው ስምምነት ትልቅ መነሻ እንደሚሆን እንዲሁም በዕለቱ ከተፈረመው የፍርደኞች ማስተላለፍ ስምምነት በተጨማሪ በሌሎች የሕግ ጉዳዮች በትብብር ለመስራት ሁለቱ አገራት ዝግጁነታቸውን ገልፀዋል።

ስምምነቱ በአግባቡ እንዲፈጸም ትኩረት መስጠት እንደሚገባ በፊርማ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተጠቆመ ሲሆን በዚሁ ወቅት የሁለቱም አገራት የፍትሕ ሚኒስትሮች ስምምነቱን ተፈጻሚ ለማድረግ ያላቸውን ቁርጠኝነት እና ዝግጁነት ገልጸዋል።

የፍትሕ ሚኒስቴርን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆችን እና ድረ-ገፅን ይቀላቀሉ
Website
https://www.justice.gov.et
Facebook
https://www.facebook.com/MOJEthiopia/
(x) Twitter
https://x.com/MOJEthiopia
YouTube channel
https://youtube.com/...3701...
Telegram
https://t.me/fdreattorneyGeneral_external

የናይጄሪያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግና የፍትሕ ሚኒስትር ክቡር ሚኒስትር Lateef Olasunkanmi Fagbemi እና የልኡክ ቡድናቸው የአድዋ ድል መታሰቢያ ጉብኝት በምስል።
10/06/2026

የናይጄሪያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግና የፍትሕ ሚኒስትር ክቡር ሚኒስትር Lateef Olasunkanmi Fagbemi እና የልኡክ ቡድናቸው የአድዋ ድል መታሰቢያ ጉብኝት በምስል።

ኢትዮጵያ እና ናይጄሪያ በሕግና ፍትሕ ጉዳዮች የሁለትዮሽ ትብብር ጉዳዮች ዙሪያ መከሩ****************************የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሐና አር...
10/06/2026

ኢትዮጵያ እና ናይጄሪያ በሕግና ፍትሕ ጉዳዮች የሁለትዮሽ ትብብር ጉዳዮች ዙሪያ መከሩ
****************************
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሐና አርአያስላሴ በአገራችን የስራ ጉብኝት በማድረግ ላይ ከሚገኙት የናይጄሪያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግና የፍትሕ ሚኒስትር ክቡር ሚ/ር Lateef Olasunkanmi Fagbemi ጋር በሁለቱ አገራት የጋራ ጉዳዮች በተለይም በሕግና ፍትሕ ጉዳዮች የሚደረጉ ትብብሮችን በተመለከተ የጋራ ምክክር ሰኔ 3/2018 ዓ.ም አድርገዋል።

ክቡር ሚኒስትሩ ወደ አዲስ አበባ ሲገቡ ለተደረገላቸዉ ደማቅ አቀባበል እና መስተንግዶ ምስጋናቸውን የገለፁ ሲሆን፣ ሁለቱ አገራት በተለያዩ ዘርፎች አብሮ በመስራት ሂደት ለአመታት የዘለቀ ጠንካራ እና ዉጤታማ ግንኙነት እንዳላቸው አንስተው በተለይም ከፍትሕ ዘርፉ ጋር በተያያዘ በጋራ ጉዳዮች ዙሪያ በቀጣይ አብረው ለመስራት ውይይቱ ከፍ ያለ ጠቀሜታ እንዳለው አንስተዋል።

በምክክሩም ድርድሩ የተጠናቀቀውና በዛሬው ዕለት ይፈረማል ተብሎ ስለሚጠበቀው ፍርደኞችን የማስተላለፍ ስምምነት እንዲሁም ሌሎች በሂደት ላይ የሚገኙ የሁለትዮሽ ስምምነቶችን በማጠናቀቅ ለፊርማ ዝግጁ ማድረግ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ግንኙነት በማጠናከር ረገድ ስላለው አስተዋፅኦ፤ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን በመከላከል ረገድ በሁለቱ አገራት መካከል የሚኖሩ ትብብሮች ለሁለቱም አገራት ስለሚያስገኙት ጠቀሜታ፤ ማረሚያ ቤቶችን በማሻሻል ረገድ በአገራችን በኩል ስለተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት እንዲሁም በሁለቱ አገራት መካከል የልምድ ልውውጥ ሊደረግባቸው የሚችሉ ተሞክሮዎችን በተመለከተ ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጓል።

የፍትሕ ሚኒስቴርን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆችን እና ድረ-ገፅን ይቀላቀሉ
Website
https://www.justice.gov.et
Facebook
https://www.facebook.com/MOJEthiopia/
(x) Twitter
https://x.com/MOJEthiopia
YouTube channel
https://youtube.com/...3701...
Telegram
https://t.me/fdreattorneyGeneral_external

Address

Bambis, Jomo Kenyatta Avenue
Addis Ababa
P.O.BOX1370

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 02:30 - 17:30
Wednesday 09:00 - 17:30
Thursday 09:00 - 17:30
Friday 02:30 - 17:00

Telephone

+251115515099

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when FDRE Ministry of Justice/ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to FDRE Ministry of Justice/ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር:

Share