የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ- Addis Ababa Labor and Skill Bureau

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ- Addis Ababa Labor and Skill Bureau

የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ- Addis Ababa Labor and Skill Bureau በክህሎት የበለፀገ እና ሥራን ባህሉ ያደረገ ትውልድ ለኢትዮጵያችን ብልፅግና መሠረት ነው!!
(1)

18/06/2026
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከፍትሕ ቢሮ የትብብር ጥምረት ጽሕፈት ቤት ጋር በመሆን፤ ባለፉት 11 ወራት 807 ሺህ ዜጎችን በግንዛቤ ፈጠራ ተደራሽ የማድረግ፣ ለ740 ስ...
18/06/2026

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከፍትሕ ቢሮ የትብብር ጥምረት ጽሕፈት ቤት ጋር በመሆን፤ ባለፉት 11 ወራት 807 ሺህ ዜጎችን በግንዛቤ ፈጠራ ተደራሽ የማድረግ፣ ለ740 ስደት ተመላሾች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችለዋል ፡፡

🇪🇹ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ|አበባ🇪🇹

📊 የሥራና ክህሎት ቢሮ ዓበይት ስኬቶች በቁጥር፡-
📢 የ127% የግንዛቤ ፈጠራ ስኬት፡- ሕገ-ወጥ ስደትንና የሰዎች ዝውውርን አስከፊነት ለሕብረተሰቡ ለማስገንዘብ 635,379 ሰዎችን ተደራሽ ለማድረግ አቅደን፣ ዕቅዱን በከፍተኛ ደረጃ በማሳለጥ 807,384 ዜጎችን በተለያዩ መድረኮችና የሚዲያ አማራጮች ተደራሽ ማድረግ ተችሏል።

💼 የሥራ ዕድል ፈጠራ፡- ለ716 ስደት ተመላሾች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ፣ ለ740 ተመላሾች (235 ወንዶችና 505 ሴቶች) የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረግ የተቻለ ሲሆን፣ ለ68 ዜጎች ደግሞ የመሥሪያ ቦታ (የገበያ ሼድ) ተሰጥቷቸዋል።

🤝 አጋርነትና ቅንጅት፡- ከዓለም አቀፉ የሥራ ድርጅት (ILO)፣ UN Habitat እና ሳፋሪኮም (Safaricom) ጋር በመተባበር የ200 (60 ፕርሰንት ስደት ተመለሽ 㙀ENA 40 host community )ስደት ተመላሾችን ሕይወት የሚቀይሩ 100 ዘመናዊ ሱቆች ግንባታ በሂደት ላይ ይገኛል። በተጨማሪም ከባለድርሻ አጋር ድርጅቶች (እንደ Good Samaritan, TaYA, DEC, CARITAS እና ሌሎች) ጋር የመግባቢያ ሰነድ (MOU) ተፈርሟል።

⚖️ የአጠቃላይ የትብብር ጥምረቱ ስትራቴጂካዊ ስራዎች (በፍትሕ ቢሮ የሚመራ)፦
በፍትሕ ቢሮ የትብብር ጥምረት ጽ/ቤት ኃላፊ በአቶ ዮሐንስ ብርሃኑ አስተባባሪነት፣ ጥምረቱ በ5 ዋና ዋና ስትራቴጂካዊ ግቦች ላይ ውጤታማ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። እነዚህም፡-

የግንዛቤ ሥራዎችን በአደባባይ፣ በሚዲያና በመድረክ በስፋት መስጠት፣

ወንጀል መከላከልና ሕግ ማስከበር ሥራዎች፣

የፍልሰት ጉዳዮች ምክር ቤትና የትብብር ጥምረት አደረጃጀትን ማጠናከር፣

የወንጀል ጥቆማዎችን በነፃ ስልክ ጥሪ 6073 መቀበልና መረጃ መስጠት፣

የወንጀል ተጋላጭነት ቦታዎችን የመለየት ጥናትና የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎች ናቸው።

🗣 የዕውቅና አስተያየት፦
ከትብብር ጥምረት ጽ/ቤት ጋር መድረኩን ያመቻቹት የሆፕ ፎር ጀስቲስ ካንትሪ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሶስና ይርጋ እንደገለጹት፤ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ወንጀልን ለመቅረፍ ባለድርሻ አካላትን አቀናጅቶ መሥራት የሚጠይቅ ሲሆን፣ ጥምረቱ ከሌሎች አቻ ክልሎች ጋር ጭምር የጀመራቸው የቅንጅት ሥራዎችና የሥራና ክህሎት ቢሮ ያሳያቸው ተጨባጭ አፈጻጸሞች ለሌሎችም እንደ መልካም ተሞክሮ ሊወሰዱ የሚችሉ ናቸው።

ቢሮአችን በቀጣይም ከተመዘገቡት ጠንካራ ስኬቶች በመነሳትና ክፍተቶችን በመሙላት፣ ከፍትሕ ቢሮና ከሁሉም የትብብር ጥምረት አባላት ጋር በመሆን የዜጎችን ደህንነትና ዘላቂ ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራውን አጠናክሮ ይቀጥላል።

https://aabols.gov.et/qr.html

18/06/2026
በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት 70ሺ ለሚሆኑ የከተማዋ ነዋሪዎች የሥራ እድል እንደሚፈጠር ተገለጸ፡፡🇪🇹ሰኔ 9/2018 ዓ.ም🇪🇹 የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት  በዋናነት ያለፈ...
16/06/2026

በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት 70ሺ ለሚሆኑ የከተማዋ ነዋሪዎች የሥራ እድል እንደሚፈጠር ተገለጸ፡፡

🇪🇹ሰኔ 9/2018 ዓ.ም🇪🇹

የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት በዋናነት ያለፈውን ዓመት አፈጻጸም በማጠናከርና በዘላቂነት ላይ የተመሠረተ የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማፋጠን በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ አስታውቋል።

በዚህም መሠረት 175,000 አዳዲስ አማራጭ የሥራ ዕድሎችን በጥናት የመለየት፣ 70,000 የከተማ ነዋሪዎችን በአዳዲስ የስራ ዕድል ተጠቃሚ የማድረግ፣ እንዲሁም በከተማ ግብርና፣ ኢንዱስትሪ እና አገልግሎት ዘርፎች ሰፊ የሥራ ዕድልን የማስፋት ሥራዎች በቅድሚያ ይከናወናሉ።

ለዚህ ስኬታማነትም 630,000 የከተማ ነዋሪዎችን በማሳተፍ የሚከናወኑ የግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄዎችና መድረኮች በወረዳ፣ በብሎክና በክፍለ ከተማ ደረጃ ተዘጋጅተው ወደ ተግባር ይገባሉ።

የኢንተርፕራይዞችን አቅም በማሳደግ ረገድ አዳዲስ 2,000 ኢንተርፕራይዞችን በማደራጀት 14,000 አንቀሳቃሾችን ወደ ሥራ ለማስገባት ታቅዷል። የፋይናንስ አቅርቦትን በተመለከተም 660 ሚሊዮን ብር ብድር፣ የመሳሪያ ሊዝ አገልግሎት፣ እና ለ925 ኢንተርፕራይዞች የመስሪያ ቦታ የማመቻቸት ሥራዎች በዋናነት ይከናወናሉ።

በተጨማሪም ከተማዋን ሊቀይሩ በሚችሉ የአካባቢ ልማት ሥራዎች ላይ 208,118 ተጠቃሚዎችን በማሳተፍ የመንግስት ማቺንግ ፈንድ ክፍያዎችን መፈጸምና ተጠቃሚዎች የባንክ ሂሳብ እንዲኖራቸው የማድረግ የኑሮ ደረጃ ማሻሻያ ስራዎች በቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቷቸዋል።

የክህሎት ሥልጠናን በተመለከተ የመንግስት ኮሌጆች 8,526 ተመራቂዎችን በብቃት አስመርቆ ለሥራ ገበያው የማስተሳሰር ሥራ ይከናወናል። የሥልጠና ጥራትን ለማረጋገጥም 2,773 አሰልጣኞችን በፕሮጀክት ቤዝድ ስልጠና ማብቃት፣ 312 አመራሮችን በስልጠና ማብቃት እና 150 አዳዲስ አሰልጣኞችን በመቅጠርና በመመደብ የሰው ኃይል አቅምን የማጠናከር ስራ ይሰራል።

ከኢንዱስትሪዎች ጋር ተጠናከረ ትስስር በመፍጠር 80% የሚሆኑ ተመራቂዎችን ከሥራ ጋር የማገናኘትና አዳዲስ መመሪያዎችን በማጽደቅ የአሰራር ማነቆዎችን የመፍታት ሥራዎች በዘላቂነት ይሰሩበታል።

የከተማውን የኢንዱስትሪ ሰላም ለማስጠበቅ በ4,900 ድርጅቶች ላይ የሥራ ሁኔታዎች ቁጥጥር ይካሄዳል። የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎችን ለ800 አመራሮችና ፈጻሚዎች በመስጠት፣ እንዲሁም 150 አዳዲስ የሠራተኛ ማህበራትን በማደራጀት የኢንዱስትሪ ሰላምን የማስጠበቅና የሠራተኛውን ጥቅማ ጥቅም የማስከበር ተግባራት በሦስቱ ወራት ውስጥ በልዩ ትኩረት ይፈጸማሉ።



ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ

https://aabols.gov.et/qr.html

16/06/2026

የፖሊሲ ጉዳይ ቅኝት - ሰኔ 9፣ 2018 ዓ.ም

በበጀት ዓመቱ ከ10 ሺህ በላይ ኢንተርፕራይዞች ተሸጋገሩ፤ በቦሌ ሰሚት በሳይንስና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የታገዘ አዲስ የልማት ተአምር ያስመዘገበው የ“ፍሬህይወት ዘሮባቤል” ማህበር...
16/06/2026

በበጀት ዓመቱ ከ10 ሺህ በላይ ኢንተርፕራይዞች ተሸጋገሩ፤ በቦሌ ሰሚት በሳይንስና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የታገዘ አዲስ የልማት ተአምር ያስመዘገበው የ“ፍሬህይወት ዘሮባቤል” ማህበር አርአያነት ተበሰረ

🇪🇹ሰኔ 9 ቀን 2018 አዲስ አበባ (የቢሮ ጋዜጠኛ)

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በበጀት ዓመቱ ውስጥ ከጥቃቅን ጀምሮ እስከ መካከለኛ ደረጃ የሚገኙ ከ10 ሺህ በላይ ኢንተርፕራይዞች የዕድገት ደረጃ ሽግግር ማድረጋቸውንና ይህም ከባለፉት ዓመታት እጅግ የላቀ አፈጻጸም የተመዘገበበት ስኬት መሆኑን የኢንተርፕራይዝ እና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ አስታወቀ። ዘርፉ የኢንተርፕራይዞችን አቅም ለማሳደግና የአሠራር ሥርዓታቸውን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማጥለቅ ታላቅ ሳይንሳዊ የምክክርና የተሞክሮ ማስፋፊያ መድረክ አካሂዷል።

ለሦስት ተከታታይ ቀናት በተካሄደው በዚህ መድረክ ላይ፣ በከተማ ግብርና (በእንስሳት እርባታ) ዘርፍ እጅግ የላቀና አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂን በመጠቀም አዲስ ተስፋ የፈነጠቀውን የ«ፍሬህይወት ዘሮባቤል እና ጓደኞቻቸው የወተት ከብት እርባታ ህብረት ሽርክና ማህበር»ን ምርጥ ተሞክሮ ሳይንሳዊ በሆነ ዘዴ በተግባር እንዲሰፋ ተደርጓል።
 የፖሊሲ ሪፎርም እና የኢንተርፕራይዞች ታሪካዊ ሽግግር
የቢሮ የኢንተርፕራይዝ እና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ላይ የተሞክሮ ቅመራና የእድገት ደረጃ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ኑሩ ሁሴን መሐመድ አሊ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ የመድረኩ ዋና ዓላማ የፖሊሲ ሪፎርሞችን ማውረድና የተመረጡ ምርጥ ተሞክሮዎችን በሳይንሳዊ መንገድ ወደ ሌሎች ኢንተርፕራይዞች ማስፋት ነው። በበጀት ዓመቱ እስከ 11 ወራት ባለው ሪፖርት ብቻ 162 ከፍተኛ ብቃት ያላቸው ሞዴል ኢንተርፕራይዞች መፍራት መቻላቸውን የጠቆሙት አቶ ኑሩ፣ መንግስት ለዚህ ስኬት በርካታ የፋይናንስ ድጋፍ፣ የመሳሪያ ሊዝ አቅርቦት፣ የምርታማነት ልኬት እገዛና የገበያ ትስስር ማመቻቸቱን ገልጸዋል።

ይሁን እንጂ አሁንም ቢሆን ከመንግስት ድጋፍ ውስንነት፣ ከራሳቸው ከኢንተርፕራይዞቹ የግንዛቤ ክፍተት እና ሰነዶችን ለጥቅም ማግኛ ብቻ ከመጠቀም ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን በጽናት መታገል እንደሚገባ አቶ ኑሩ አሳስበዋል። “የመድረኩ ዋና ዓላማ 'መስራት ይቻላል' የሚለውን እሳቤ በተግባር ማሳየት ነው” ያሉት ዳይሬክተሩ፣ በቀጣይም ይህ ምርጥ ተሞክሮ መሬት ላይ መውረዱን ባለሙያዎች በቅርብ ክትትል እንደሚያረጋግጡ በቁርጠኝነት ገልጸዋል።

 ከቀውስ ወደ ስኬት ማማ፦ የፍሬህይወት ዘሮባቤል ማህበር የልማት ተአምር
በመድረኩ ማጠቃለያ ቀን 125 በእንስሳት እርባታ ዘርፍ የተደራጁ ኢንተርፕራይዞችና ባለሙያዎች በተገኙበት፣ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ሰሚት ኮንዶሚኒየም አካባቢ የሚገኘውና በጠንካራዋ ሴት ወይዘሮ ፍሬህይወት ዘሮባቤል የሚመራው ማህበር ተሞክሮ በቪዲዮና በፕረዘንቴሽን ቀርቦ ተተንትኗል። በአንድ ወቅት ፈታኝ በነበረው የስራ አጥነት እና የወደፊት ተስፋ ማጣት ውስጥ የነበረችው ወይዘሮ ፍሬህይወት፣ ዛሬ የወተት ከብት እርባታን ሙሉ በሙሉ በሳይንስና በጥናት ላይ የተመሰረተ ማራኪ የኢንቨስትመንት መስመር አድርጋዋለች።
 የሳይንሳዊ ዘር (Sexed Semen) ቴክኖሎጂ ድል
ማህበሩ ስራ ሲጀምር የወንዶች ጥጃዎች ብቻ መወለድ እና የዝርያ እጥረት ለከፍተኛ ኪሳራ ዳርጎት እንደነበር ያስታወሰችው ወይዘሮ ፍሬህይወት፣ ላሞችን ከውጭ ሀገር በአውሮፕላን ለማስገባት የሚጠይቀው ከፍተኛ ወጪ (ከ1,000 እስከ 6,000 የአሜሪካ ዶላር) ትልቅ ማነቆ ሆኖባቸው እንደነበር ገልጻለች።
ይህንን ፈተና ለመስበር ማህበሩ የጥጃውን ጾታ አስቀድሞ መወሰን የሚያስችለውን የሳይንሳዊ ዘር (Sexed Semen) ቴክኖሎጂን በድፍረት ስራ ላይ አውሏል። ቀደም ሲል ያልተለየው መደበኛ ዘር እስከ 500 ብር ይሸጥ የነበረ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ጾታው የተለየው ምርጥ ዘር ከ1,500 እስከ 2,000 ብር በሚደርስ ተመጣጣኝ ዋጋ ለመንግስት በመክፈል ማህበሩ በስፋት እየተጠቀመበት ይገኛል። በዚህም ተአምራዊ በሆነ መንገድ በአንድ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ 13 ምርጥ የሴት ጊደር ጥጃዎችን ማፍራት ችለዋል።

 "ነፍስ እውቀት የሌለባት ትሆን ዘንድ መልካም አይደለም" — አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ለእርባታ
የማህበሩን የእድገት አቅጣጫና ስልታዊ የቢዝነስ ፕላን የሚያዘጋጀው ወጣቱ ባለሙያ ቢኒያም፣ ቅዱስ መጽሐፍ ላይ የሚገኘውን “ነፍስ እውቀት የሌለባት ትሆን ዘንድ መልካም አይደለም” የሚለውን የወርቃማ ቃል በመጥቀስ ስራቸውን ሙሉ በሙሉ በዕውቀትና በቴክኖሎጂ ላይ መመስረታቸውን በስሜት አብራርቷል።
ማህበሩ እንደ ጎግልና አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ያሉ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አማራጮችን ለመረጃ ምንጭነት ይጠቀማል። መረጃዎቹን በቀጥታ ከመተግበራቸው በፊት፣ በዘርፉ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከታተሙ የሪሰርች ወረቀቶች (Research Papers) ጋር በማጣራት (Cross-check) ያረጋግጣሉ።
ባለሙያው ቢኒያም እንደገለጸው፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እጅግ ሰፊ የሆኑ የኮርማዎችን ታሪክ በጥልቀት በማንበብና በዘርፉ የላቀ እውቀት ለሌላቸው ሰዎች ጭምር በቀላሉ በሚረዳ ቋንቋ (Layman's terms) በመተንተን ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል። ይህ የቴክኖሎጂ እገዛ ማህበሩ የሚከተሉትን ስራዎች በስኬት እንዲወጣ አስችሎታል፦
1/የላሞቹን ወተት ምርት፣ ቁመትና የደረት ስፋት ለማሻሻል ትክክለኛውን የኮርማ ዝርያ መምረጥ።
2/ የተመጣጠነ የከብት ምግብ (Balanced feed) በሳይንሳዊ መንገድ ለማዘጋጀት የሚያስችሉ ዓለም አቀፍ ሰነዶችን ማሰባሰብ።
 የምርት ዘመን ዑደት እና የአሁኑ አቅም
በውጭ ሀገራት ተሞክሮ አንዲት ላም ኢኮኖሚያዊ ጥቅም የምትሰጠው ከተወለደችበት ጊዜ ጀምሮ ቢበዛ እስከ 5 ዓመት ብቻ መሆኑን የጠቀሰው ቢኒያም፣ በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ግን በጥንቃቄ በመያዝ ላሞች እስከ 6 እና 7 ዓመታት ድረስ ምርት እንዲሰጡ እየተደረገ መሆኑን ገልጿል።
በአሁኑ ወቅት ማህበሩ በአጠቃላይ ጥጃዎችን፣ ጊደሮችን እና የሚታለቡ ላሞችን ጨምሮ 35 የከብቶች ክምችት ላይ ደርሷል። ከእነዚህም ውስጥ 10 የሚሆኑት ላሞች በአሁኑ ወቅት እርጉዝ ሲሆኑ፣ በቅርቡ ወደ ምርት ምዕራፍ ሲገቡ የማህበሩን የወተት አቅርቦት በአስደናቂ ሁኔታ በእጥፍ ያሳድጉታል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ የፍሬህይወት ዘሮባቤል ማህበር ስኬት፣ ጠንክሮ ለሚሰራ እና ቴክኖሎጂን ለሚጠቀም ማናቸውም ኢንተርፕራይዝ “መስራት እና መለወጥ ይቻላል!” የሚል ትልቅ የተስፋ ስንቅና ህያው ምስክር ሆኖ አልፏል።



ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ

https://aabols.gov.et/qr.html

Address

5 Kilo
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ- Addis Ababa Labor and Skill Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ- Addis Ababa Labor and Skill Bureau:

Share