12/08/2020
.....የቀጠለ
Via Girum Solomon
ላም የጠፋበት ሰውዬ እና ልጁ
አባት ፡ እንዴ ወዴት ወዴት ነው?
ልጅ ፡ እሷን ፍለጋ! የምተርክላትን ላም ?
አባት ፡ አሄ! የት ነው ባክህ ምትፈልገው?
ልጅ፡ ሰው ፍለጋ ሲወጣ እኮ ለማግኝት ብሎ እንጂ የት እንደሆነ አያቅም። የት እንደሆነ ቢያቅማ ቀድሞውንም አልጠፋበትም ነበር።
አባት ፡ ፓ! እኔ በስንት አሉ በተባሉ ሰዎች አስፈልጌ ያላገኘኋትን አንተ ቱታና ቦቲ ስላረክ ምታገኛት መሰለህ?
ልጅ ፡ እሱ እኮ ነው ችግሩ የጠፋብህ አንተ። የፈለጉት ሌሎች። ማንያቃል ይሄኔ እኮ ፈልጉ ያልካቸው ደብቀዋት ወተትዋን እየጠጡ ይሆናል እኮ። ሌላው ስለ አለባበሴ ለጠየከኝ ያው ሽርሽር አይደለም። ፍለጋ ነው። የተመቸኝ ቦታ ብቻ አይደለም ምፈልጋት። ስለዚህ ለመንገድ እንዲመቸኝ ነው።
አባት ፡ እረ ተው ሰው ምን ይልሃል? የት ይደርሳል የተባለ ዛፍ አሉ?
ልጅ ፡ ሚገርምህ እሱ ነበር እስከዛሬ ድረስም ጠፍንጎ የያዘኝ። ዛሬ ላይ ግን አንድ የገባኝ እውነት ሰው የጠፋበት ነገር ዋጋ እንዳለው ካወቀ ለዛ ነገር መስዋት መክፈል ብዙ አያሳስበውም።
አባት ፡ አሁን እስቲ እዚህ ያንተ እኩዮች እኔን ብለው ከየት ድረስ መተው ይማራሉ አንተ ግን?
ልጅ ፡ አባዪ! እኔ እኮ ከገባኝ ቆየ። ከዛሬ ነገ አንድ ቀን መጥታ ወተትዋን ጠጣሁ እያልኩ በምናብ ሞትኩኝ እኮ። አንተም ብትሆን በፊት ትተርክበት የነበረበትን መንገድ ዘመናዊ እና ለጆሮ አማላይ ማድረጉ ላይ ነው ያተኮርከው እንጂ ላምዏን ጭራሽ እረስተሃታል።
አባት ፡ ግድ የለም በተከበርኩበት ልታዋርድኝ ነው አይደል ቆርጠ የተነሳህው?
ልጅ ፡ ክብር እኮ ‘እንዲ ነበረኝ’ በማለት ውስጥ አይደለም ያለው በመሆን ውስጥ ነው መገኛው። ደግሞስ ካሰብከው እኮ የኔ ፍለጋ መውጣት ጥቅም አለው እንጂ ጉዳት የለውም። ካገኘኋት እኔም አንተም እዲሁም የሰው ልጅ ጭምር ነው ሚከብረው። በዛላይ እስከዛሬ ምታወራው እውነት እንደነበር ማረጋገጫ ይሆንልሃል።
አባት ፡ አቤቱ ፈጣሪዬ ምን ጉድ ነው የሰጠህኝ... በል እዲያ ከሆነ ነገሩ፣ በል ብቻህን አትሄድም እኔም ልብስ ቀይሬ መጣሁ።
ከባዶም ቢሆን ተነስተን ፍለጋ መውጣት ከፊታችን ያለ ምርጫ ነው። ጥቂት ልንሆን እንችላለን ግን ብቻችንን አይደለንም። እኛ ኢትዮጵያዊያኖች በድቅድቅ ጨለማ ብረሃን ይዘን እንወጣለን። ለሰው ልጅ የሚሆን ሃሳብ ከጓዳችን ዘንድ አለ።
ለበለጠ ስለነዚህ ሃሳቦች ጥልቅ ትንታኔ በመልከዓ ሃሳብ ሬዲዪ ዝግጅት ዛሬ ከቀኑ 8 ሰዓት እስከ 9፡30 ይጠብቁ