08/04/2026
በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እና የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ
ADDIS KETEMA W11 CRRSA: መጋቢት 30/2018 ዓ.ም
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ በተዘጋጀ የንቅናቄ ሰነድ ዙሪያ ከጽ/ቤቱ ሰራተኞች ጋር ውይይት አድርጓል፡፡
የጽ/ቤቱ የኩነት ዘርፍ ቡድን መሪ አቶ እዮብ ወ/አማኑኤል የንቅናቄ መድርኩን ዓላማ፣የአገልግሎትና አሰጣጥ ጽንሰ-ሀሳብ፣ ለአገልግሎት አሰጣጡ ምቹ ሁኔታ ከመፍጠር አንጻር፣የአገልግሎት ሰጪውና ተቀባዩ መብትና ግዴታዎች በዝርዝር አስረድተዋል፡፡
አገልግሎት እውቀትን እና ሙያን መሰረት አድርጎ የተገልጋይን ፍላጎት ለማሟላት የሚደረግ ጥረት ነው ያሉት አቶ እዮብ የተገልጋይን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ዓላማ ተኮር ተግባር የሚሰጡ አገልግሎቶች ስኬታማና ኢኮኖሚያዊ ቅልጥፍናን በተላበሰ መልኩ የሚከናወን በጊዜ፣ በመጠን፣ በጥራትና በወጪ የሚለካ፣የተገልጋይ እርካታ ሊለኩ የሚችሉ፣ በአገልግሎት ተቀባዩ ዘንድ እሴት የሚጨምሩ መሆን እንዳለበት ገልፀዋል፡፡
መዲናችን አዲስ አበባ የያዘችውን የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ በማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ ነው ያሉት አቶ እዮብ መንግስት ያወጣቸውን ፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎች እና ፕሮግራሞች በመፈፀምና በማስፈፀም ረገድ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ሚና የማይተካ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በየደረጃው የሚስተዋሉ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን በመለየት መፍታት፣ለተገልጋዩ ማህበረሰብ እና ለአገልግሎት አቅራቢው ተቋም መብትና ግዴታ ዙሪያ ግንዛቤ ለመፍጠር፣የመንግስት ተቋማት አገልግሎት አሰጣጣቸው እንዲሻሻል በማድረግ የተገልጋይ እርካታን ማሳደግ የሰነዱ ዋና ዓላማ መሆኑን አቶ እዮብ አስረድተዋል፡፡
የጽ/ቤቱ ሰራተኞች ደንበኞችን በቅንነት በታማኝነትና በትጋት በማገልገል የተጣለባቸውን ኃላፊነት መወጣት እንደሚገባ በመድረኩ መልዕክት ተላልፏል፡፡
***
👉አዲስ ከተማ ወረዳ 11 የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት
ለበለጠ መረጃ:
✅ፌስቡክ(Facebook):https://www.facebook.com/profile.php?id=61563255924975
✅ቴሌግራም(Telegram):https://t.me/addisketemaw11crrsa
✅ቲክቶክ(Tiktok):https://www.tiktok.com/.ketema.were?_t=ZM-8zVfRON9tuo&_r=1
✅ኢንስታግራም(Instagram):https://www.instagram.com/addis_k_wereda11_crrsa_office/
✅ትዊተር(Twitter):https://x.com/AdA_K_W11_CRRSA?t=6s06OHhfEvSQefw8JA0y_w&s=35