Ethiopian Health Insurance Service

Ethiopian Health Insurance Service to promote Health Insurance in Ethiopia Ethiopian Health Insurance Service

የጤና መድህን አስተማማኝ ጋሻ እና ድልድይ28/09/2018 ዓም ኢጤመአበለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ስር በሚገኝ አንድ ምስኪን ጎጆ ውስጥ፣ ህይወት በፈተና እና በውጣ ውረድ የተሞላች ነበረ...
04/06/2026

የጤና መድህን አስተማማኝ ጋሻ እና ድልድይ
28/09/2018 ዓም ኢጤመአ
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ስር በሚገኝ አንድ ምስኪን ጎጆ ውስጥ፣ ህይወት በፈተና እና በውጣ ውረድ የተሞላች ነበረች። ወይዘሮ የሺ ጌታነህ ከአንድ ልጃቸው እና ከባለቤታቸው ጋር የሚኖሩ የዕለት ጉርሳቸውን ለማሟላት በቀን ስራ የሚደክሙ ጠንካራ እናት ናቸው። ነገር ግን፣ በአንድ ወቅት በቤተሰባቸው ላይ ድንገት የተጋረጠው ከባድ ፈተና የኑሯቸውን ምሰሶ ሊነቀንቀው፣ ተስፋቸውንም ሊያጨልመው ተቃርቦ ነበር።
ማዕበሉ የጀመረው የቤተሰቡ እራስ በሆኑት በባለቤታቸው ድንገተኛ መታመም ነበር። ጥበቃ ስራ ተቀጥረው መስራት ጀምረው ገና አንድ ወር እንኳ ሳይሞላቸው ነበር ህመሙ ከአልጋ የጣላቸው። ያኔ ወይዘሮ የሺ፣ የባለቤታቸው ህይወት በአስጊ ሁኔታ ውስጥ መውደቁንና በወቅቱ የተሰማቸውን የፍርሃትና የሰቀቀን ስሜት ዛሬም ድረስ በቅዠት አዘል ትውስታ ያስታውሱታል።
የባለቤታቸው ጤና እያሽቆለቆለ ሲሄድ፣ ወይዘሮ የሺ ግራ በመጋባትና በጭንቀት ተከበው በአቅራቢያቸው ወደሚገኝ ጤና ጣቢያ አቀኑ። ሆኖም የህመሙ ክብደት ከጤና ጣቢያው አቅም በላይ በመሆኑ፣ በሌሊት ሰባት ሰዓት ላይ በጭለማው መሃል ወደ የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ይዘውት ለመምጣት ተገደዱ። በሆስፒታሉ ግድግዳዎች መሃል የተስፋና የጭንቀት ቀናትን እየቆጠሩ ዘጠኝ ቀናት ነጎዱ።
ለእነ ወይዘሮ የሺ፣ የዕለት ኑሮን መግፋት ቀርቶ የቤት ኪራይ መክፈል ራሱ እንደ ተራራ የከበደ የዘወትር ፈተናቸው ነው። በእንዲህ ያለ አቅም አጥቶ የመጨነቅ አዙሪት ውስጥ፣ ታሞ የተኛን ሰው በከፍተኛ የህክምና ተቋም ውስጥ ማከም ለእነሱ ማሰብ እንኳ የማይቻል ህልም ነበር። ወይዘሮ የሺ ያንን የጭንቀት ወቅት ሲያስታውሱ፣ የጤና መድህን ባይኖር ኖሮ ባለቤታቸው ቤት ውስጥ ከመሞት ውጪ ሌላ አማራጭ እንዳልነበራቸው በቁጭት ይገልጻሉ። ወደ ህክምና ተቋም የሚመጡበት አምስት ሳንቲም እንኳ በእጃቸው አልነበረም። እንዲያውም ሆስፒታል ውስጥ የነጻ ምግብ አገልግሎት መኖሩን ሳያውቁ፣ ምንም ሳይቀምሱ ውለው ያደሩባቸው የረሃብና የጭንቀት ቀናት ነበሩ። በኋላ ግን በሆስፒታሉ ሰብአዊ ድጋፍ ምግብ ማግኘት በመቻላቸው ያንን ከባድ ቀን ሊሻገሩት ችለዋል።
በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በቆዩባቸው በእነዚያ ዘጠኝ ቀናት፣ ባለቤታቸው አስፈላጊው ምርመራ ሁሉ ተደርጎለት የጨጓራ እና የደም ማነስ ህመም እንዳለበት ተረጋገጠ። በአሁኑ ወቅትም ተገቢውን ህክምና እና ክትትል እያገኘ፣ የጤናው ሁኔታ በፍጥነት ወደ ተሻለ ደረጃ ላይ ይገኛል።
"ለመሆኑ ይህ ሁሉ የህክምና ወጪ እንዴት ሊሸፈን ቻለ?" የሚለው ጥያቄ ሲነሳ፣ የወይዘሮ የሺ ምላሽ የጤና መድህን ለዜጎች፣ በተለይም አቅም ለሌላቸው ወገኖች ያለውን የላቀ እና ህይወት አዳኝ ፋይዳ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው። ወይዘሮ የሺ በኩራትና በምስጋና መንፈስ፦ "የጤና መድህን አለኝ፤ እስካሁን ድረስ አንድም ሳንቲም ክፍያ አልተጠየቅኩም። የጤና መድህን የባለቤቴን ህይወት እየታደገው ነው" በማለት ምስክርነታቸውን ይሰጣሉ።
ይህ ታሪክ የአንድ ቤተሰብ ምስክርነት ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም የጤና መድህን አገልግሎት በጭንቀትና በችግር ማዕበል ውስጥ ለሚወድቁ ምስኪን ዜጎች እንዴት ያለ አስተማማኝ ጋሻ እና ድልድይ መሆኑን ያረጋገጠበት እውነተኛ ማሳያ ነው እንጂ።"Youtube: https://www.youtube.com/-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram: https://t.me/buu

X (formerly Twitter) (https://twitter.com/service4E)
Ethiopia Health Insurance Service () / X

የሽኩር እና የአባቱ የትንሳኤ ጉዞ27/09/2018 ዓም ኢጤመአበተንታ አጅባር ከተማ ውስጥ የሚኖረው ወጣት ሽኩር ፈጠነ፣ የዕለት ተዕለት ህይወቱን የሚገፋው በቀን ስራ በሚያገኛት አነስተኛ ገቢ...
04/06/2026

የሽኩር እና የአባቱ የትንሳኤ ጉዞ
27/09/2018 ዓም ኢጤመአ
በተንታ አጅባር ከተማ ውስጥ የሚኖረው ወጣት ሽኩር ፈጠነ፣ የዕለት ተዕለት ህይወቱን የሚገፋው በቀን ስራ በሚያገኛት አነስተኛ ገቢ ነበር። እሱና መላው ቤተሰቡ እንደ ማንኛውም አርሶ አደርና ወዝ አደር ቤተሰብ፣ ከእጅ ወደ አፍ በሆነ ህይወት ለዕለት ጉርሳቸው የሚሯሯጡ ምስኪን ሰዎች ናቸው። ይሁን እንጂ የድህነት ኑሮ የቱንም ያህል ቢበረታባቸውም፣ በመካከላቸው የነበረው ፍቅርና መተጋገዝ ግን የላቀ ነበር።
አንድ ቀን ግን በቤተሰቡ ላይ ያልታሰበ ከባድ ፈተና ወደቀ። የወጣት ሽኩር አባት ባጋጠማቸው ድንገተኛ የመውደቅ አደጋ ሳቢያ ክፉኛ ተጎዱ። ሽኩር አባቱን ይዞ በአቅራቢያቸው ወደሚገኘው የአጅባር ከተማ ጤና ጣቢያ ፈጠነ። በጤና ጣቢያው ለተወሰኑ ቀናት ህክምና እየተደረገላቸው ቢቆዩም፣ የአባቱ ሁኔታ ግን ሊሻሻል አልቻለም። ህመሙ እየቀጠለ፣ የሽኩርም ስጋት እየጨመረ መጣ።
የጤና ጣቢያው ባለሙያዎች የሁኔታውን አሳሳቢነት አይተው፣ አባቱን ይበልጥ ወደተሻለ ህክምና መውሰድ እንዳለባቸው ወሰኑ። በዚህም ምክንያት ከአጅባር 120 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ወደሚገኘው ደሴ እስፔሻላይዝድ አጠቃላይ ሆስፒታል የሪፈር ደብዳቤ ተጻፈላቸው።
ለሽኩር ያ 120 ኪሎ ሜትር ርቀት ብቻ ሳይሆን፣ ወደፊት የሚጠብቀው የህክምና ወጪም ትልቅ ተራራ ሆኖ ታየው። "የቀን ሰራተኛ ሆኜ፣ ይሄን ሁሉ የሆስፒታል ወጪ እንዴት እሸፍናለሁ?" የሚለው ስጋት በጭንቅላቱ ውስጥ ይመላለስ ነበር። ሆኖም ግን፣ በአስቸጋሪው ሰዓት ከጎናቸው የቆመ አንድ ትልቅ ጋሻ ነበራቸው—የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን (CBHI)።
"የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባል ባንሆን ኖሮ፣ ይህን የአባቴን የህክምና ወጪ የመሸፈን አቅም ፍፁም አልነበረንም" ይላል ሽኩር ያንን የጭንቅ ሰዓት ሲያስታውስ። ወደ ደሴ እስፔሻላይዝድ አጠቃላይ ሆስፒታል ከገቡ በኋላ፣ አባቱ አስፈላጊውን ከፍተኛ ህክምና በሰላም ማግኘት ጀመሩ። ሽኩር ስለ ገንዘብ እጥረት ሳይጨነቅ፣ ሙሉ ትኩረቱን አባቱን በማስታመም ላይ ብቻ አደረገ።
ዛሬ ያ ሁሉ ጨለማ አልፏል። በሆስፒታሉ ውስጥ የተደረገላቸው ህክምና ተሳክቶ የአባቱ ጤንነት በከፍተኛ ሁኔታ ተመልሷል። ሽኩር በሆስፒታሉ ቅጥር ግቢ ውስጥ ቆሞ፣ ፊቱ በፈገግታ ተሞልቶ፣ ፈጣሪውን እያመሰገነ ስለ አባቱ መሻሻል እንዲህ ሲል ምስክርነቱን ይሰጣል፦
"አባቴ አርሶ አደር ነው፤ እኔም በቀን ስራ የምተዳደር ሰው ነኝ። ሁላችንም ለዕለት ጉርስ የምንሯሯጥ ብንሆንም፣ ህመም ሲገጥመን ግን የጤና መድህን አለልን! ቤተሰባችን በአጠቃላይ የዚህ መድህን ተጠቃሚ በመሆናችን አባቴ ዛሬ ከሞት ተርፎ ህይወቱ ሊታደግ ችሏል።"
ይህ ታሪክ የጤና መድህን ለድሆች ቤተሰቦች እንዴት የህክምና ዋስትና እንደሚሆን የሚያሳይ ህያው ምስክርነት ነው።"Youtube: https://www.youtube.com/-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram: https://t.me/buu

X (formerly Twitter) (https://twitter.com/service4E)
Ethiopia Health Insurance Service () / X

የተኝቶ ህክምና አገልግሎት የክፍያ ስርዓት የሙከራ ትግበራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሄደ26/09/2018 ዓም ኢጤመአየኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት በሀገሪቱ የጤና ዘርፍ የተያዘውን ጤ...
03/06/2026

የተኝቶ ህክምና አገልግሎት የክፍያ ስርዓት የሙከራ ትግበራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሄደ
26/09/2018 ዓም ኢጤመአ
የኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት በሀገሪቱ የጤና ዘርፍ የተያዘውን ጤናማ፣ አምራችና የበለጸገ ማህበረሰብ የመፍጠር ራዕይ ለማሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ገለጸ። አገልግሎቱ በሌሎች ሀገራት ተተግብረው በተጨባጭ ውጤት የተገኘባቸውን የክፍያ ስርዓቶች በሀገር ውስጥ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል።
የኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ወርቁ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት በየካቲት 12 እና በቡታጅራ ሆስፒታሎች በሙከራ ትግበራ ደረጃ ላይ የሚገኘውን የተኝቶ ህክምና አገልግሎት የክፍያ ስርዓት ውጤታማ ለማድረግ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና ባለሙያዎች ሀገራዊ ሀላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል።
የተጀመረው አዲስ አሰራር ከእድሜው አንጻር በሙከራ ትግበራው ወቅት ተግዳሮቶች ማጋጠማቸው የማይቀር መሆኑን የገለጹት የተቋሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ያምሮት አንዱዓለም ናቸው። በመሆኑም የሚገጥሙትን ተግዳሮቶች እንደ መማሪያ በመጠቀም፣ በአስቸኳይ መሻሻል የሚገባቸውን ጉዳዮች በመመካከርና በማሻሻል በጋራ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
የአገልግሎቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ጠዓመ አረዶም በበኩላቸው፣ የጤና መድህን የፋይናንስ ስርዓት ቀጣይነትን ለማረጋገጥ ዘመኑን የዋጀ የክፍያ ስርዓትን ተግባራዊ ማድረግ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህም የሀብት ብክነትን በመቀነስ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲሁም አሰራሩን ዲጂታላይዝድ በማድረግ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ተገቢ የፋይናንስ አስተዳደርና የአገልግሎት አሰጣጥን ለማስፈን እንደሚያግዝ አስረድተዋል።
የጤና አገልግሎት ሰጪዎች ጉዳይ ጥራት ማረጋገጥ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወይዘሮ ፈለጉሽ ብርሀኔ የመድረኩን ዋና ዓላማ አስመልክተው ማብራሪያ ሰጥተዋል። እንደ ወይዘሮ ፈለጉሽ ገለጻ፤ መድረኩ የተዘጋጀው ከጥቅምት 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በየካቲት 12 ሆስፒታል የተጀመረውን የተኝቶ ህክምናን መሰረት ያደረገ የጤና አገልግሎት ክፍያ ስርዓት አፈጻጸም ለመገምገም ነው። በቀጣይም የታዩ ጉድለቶችን በመሙላት፣ የሚሻሻሉትን በማሻሻልና ጠንካራ አፈጻጸሞችን በመለየት የክፍያ ስርዓቱን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል።
ለግምገማው መነሻ የሚሆኑ ጽሁፎች በሶስት አቅራቢዎች የቀረቡ ሲሆን፣ ከዋናው መስሪያ ቤት ስራ አስፈጻሚዎችና ባለሙያዎች፣ ከጤና ሚኒስቴር እና ከየካቲት 12 ሆስፒታል የተወከሉ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች፣ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ11ዱም ክፍለ ከተማ የጤና ጽህፈት ቤት ሃላፊዎች፣ የጤና መድህን አስተባባሪዎችና የሚመለከታቸው አካላት በመድረኩ ተገኝተዋል፡፡"Youtube: https://www.youtube.com/-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram: https://t.me/buu

X (formerly Twitter) (https://twitter.com/service4E)
Ethiopia Health Insurance Service () / X

‹‹የጤና መድህን እናትም አባትም የማያደርግውን ነው እያደረገልኝ ያለው››አቶ አህመድ ኢብራሂም24/09/2018 ዓም ኢጤመአየጤና መድህን አገልግሎት በሀገራችን የጤና ሥርዓት ውስጥ ተደራሽነትን...
01/06/2026

‹‹የጤና መድህን እናትም አባትም የማያደርግውን ነው እያደረገልኝ ያለው››አቶ አህመድ ኢብራሂም
24/09/2018 ዓም ኢጤመአ
የጤና መድህን አገልግሎት በሀገራችን የጤና ሥርዓት ውስጥ ተደራሽነትን በማስፋትና የዜጎችን የኪስ ወጪ በመቀነስ ረገድ እያከናወነ ያለው ሚና እጅግ የላቀ ነው። በተለይም አቅመ ደካማና አርሶ አደሩን የኅብረተሰብ ክፍል በማገዝ ረገድ የጤና መድህኑ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ የህይወት ዋስትና ሆኖ እየታየ ነው። ይህንኑ እውነታ የሚያረጋግጥ የአንድ አርሶ አደር ምስክርነት እንደሚከተለው ቀርቧል።
በወረባቦ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት አቶ አህመድ ኢብራሂም የ50 ዓመት ዕድሜ ያላቸው፣ የአራት ልጆች አባት እና አርሶ አደር ናቸው። በአሁኑ ወቅት ባለቤታቸው በሃሞት ጠጠር ሕመም ምክንያት በደሴ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የጽኑ ሕሙማን ክፍል (ICU) ውስጥ ሕክምና እየተከታተሉ ይገኛሉ።
አቶ አህመድ ስለ ቆይታቸው እና ስለ ጤና መድህን አገልግሎት ያላቸውን አስተያየት ሲገልጹ እንዲህ ብለዋል፣
ለዚህ ሆስፒታል የመጣሁት ለሁለተኛ ጊዜ ነው። መጀመሪያ ለተጨማሪ ምርመራ ከጤና ጣቢያ ተልኬ ነበር፤ አሁን ደግሞ ለቀዶ ጥገና መጥቻለሁ። በአጠቃላይ ለ23 ቀናት ባለቤቴን በአልጋ ላይ እያሳከምኩ እገኛለሁ። በጤና መድህን አገልግሎት ዙሪያ ምንም አይነት ቅሬታ የለኝም፤ በጣም ድንቅ ነው። የጤና መድህን እናትም አባትም የማያደርግውን ነው እያደረገልኝ ያለው።
አቶ አህመድ፣ የጤና መድህን ጠቀሜታውን እንደ አርሶ አደር ጠንቅቀው ማወቃቸውን ይናገራሉ፡፡፤ የሚከፍሉት አመታዊ የአባልነት መዋጮ ከሚያገኙት ጥቅም አንጻር በጣም አነስተኛ ነው። የጤና መድህን በአሁኑ ጊዜ ማንም የማይተካው እና ወሳኝ የሆነ አገልግሎት ይዞላቸው መምጣቱን ያስረዳሉ፡፡"Youtube: https://www.youtube.com/-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram: https://t.me/buu

X (formerly Twitter) (https://twitter.com/service4E)
Ethiopia Health Insurance Service () / X

ጤና መድኅን፡ የሕይወት ቀጣይና ጋሻ መከታ24/09/2018 ዓም ኢጤመአወይዘሮ ፋጡማ ማሞ የ37 ዓመት ጎልማሳና  አርአያነት ያለው የ5 አባላት ያሉት ቤተሰብ አስተዳዳሪ ናቸው፡፡ መኖሪያቸው በ...
01/06/2026

ጤና መድኅን፡ የሕይወት ቀጣይና ጋሻ መከታ
24/09/2018 ዓም ኢጤመአ
ወይዘሮ ፋጡማ ማሞ የ37 ዓመት ጎልማሳና አርአያነት ያለው የ5 አባላት ያሉት ቤተሰብ አስተዳዳሪ ናቸው፡፡ መኖሪያቸው በአማራ ክልላዊ መንግሥት፣ በደሴ ከተማ አስተዳደር፣ በአራዳ ክፍለ ከተማ 03 ቀበሌ ነው፡፡ ወይዘሮ ፋጡማ የረጅም ጊዜ የወገብ ሕመምና የአስም በሽተኛ በመሆናቸው ምክንያት የማያቋርጥና የቅርብ የሕክምና ክትትል ያስፈልጋቸዋል፡፡
የቤተሰባቸው የኢኮኖሚ መሠረት ሙሉ በሙሉ የተደገፈው በባለቤታቸው ላይ ነው፡፡ የረዥም ጊዜና ቋሚ ገቢ የሌላቸው ፣ በየቀኑ በግላቸው ተሯሩጠው በሚያገኙት የቀን ሥራ ገቢ የ5 ሰዎችን ሕይወትና የዕለት ኑሮ ለመግፋት ሌት ተቀን ይደክማሉ፡፡ በዚህ አስቸጋሪ የኑሮ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ የሁለት ከባድና ሥር የሰደዱ ሕመሞች የሕክምና ወጪን መሸፈን የማይታሰብ ከባድ ሸክም ነበር፡፡
ወይዘሮ ፋጡማን በደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አግኝተናቸው የሕክምና አገልግሎት በደስታና በእርካታ እየተከታተሉ መሆኑን ገልጸውልናል፡፡ ለዚህ ስኬታማ ሕክምናቸውና ዕፎይታቸው በምክንያትነት የጠቀሱት የማኅበረሰብ አቀፍ ጤና መድኅን (CBHI) አባል መሆናቸውን ነው፡፡
ወይዘሮ ፋጡማ የጤና መድኅንን ጥቅም ሲያስረዱ እንዲህ ይላሉ፡- “የጤና መድኅን አባል ባልሆን ኖሮ በአግባቡ ተከታትዬ የሕክምና አገልግሎት ማግኘት በፍጹም አልችልም ነበር፡፡ ምክንያቱም የሕክምና ምርመራውና የመድኃኒቱ ዋጋ አሁን ባለው ገበያ እጅግ የተጋነነ ነው፡፡ ይህንን ወጪ ደግሞ በቤተሰባችን ባለው ዝቅተኛ ገቢ መሸፈን አይቻልም ነበር፡፡ ዛሬ በደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የምናገኘውን ጥራት ያለው ሕክምና፣ አስተማማኝ ምርመራና በቂ መድኃኒት ማግኘት የቻልነው በዚህ ሥርዓት ውስጥ በመታቀፋችን ነው፡፡”
የማኅበረሰብ አቀፍ ጤና መድኅን ዋናው ፍልስፍና “ጤናማው የታመመውን፣ ይደግፋል” የሚል ነው፡፡ ሁሉም ሰው አቅሙ የፈቀደውን አነስተኛ ዓመታዊ መዋጮ ወደ አንድ የጋራ ፈንድ ያደርጋል፡፡ ከዚያም አባል የሆነ ሰው ሁሉ በታመመ ጊዜ ካለምንም ተጨማሪ የገንዘብ ክፍያ መታከም ይችላል፡፡ ይህ አሠራር ድንገተኛ ሕመም ሲመጣ ንብረትን ከመሸጥ፣ ከመበደርና ለከፋ ድህነት ከመጋለጥ ይታደጋል፡፡
በመጨረሻም ፋጡማ ማሞ “እስካሁን የጤና መድኅን አባል ያልሆናችሁ ወገኖች በአስቸኳይ አባል በመሆን ራሳችሁንና ቤተሰባችሁን ከድንገተኛ የኢኮኖሚ ቀውስ ጠብቁ፤ በመደጋገፍና ወጪን በመጋራት ለራስም ለሌላውም ወገን መድረስ እንደሚቻል እመኑ፤ ጤና የሁሉም ነገር መሠረት በመሆኑ፣ ሳይታመሙ በፊት አስቀድሞ መዘጋጀት ብልህነት ነው፡፡” በማለት መክረዋል፡፡
"Youtube: https://www.youtube.com/-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram: https://t.me/buu

X (formerly Twitter) (https://twitter.com/service4E)
Ethiopia Health Insurance Service () / X

የጤና መድህን የሕይወት መዳኛዬ ነው፡ የአቶ ሰይድ ይማም ምስክርነት22/09/2018 ዓም ኢጤመአበደሴ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ሰይድ ይማም፣ የ38 ዓመት ዕድሜ ያላቸው የሶስት ልጆች አባት እ...
30/05/2026

የጤና መድህን የሕይወት መዳኛዬ ነው፡ የአቶ ሰይድ ይማም ምስክርነት
22/09/2018 ዓም ኢጤመአ
በደሴ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ሰይድ ይማም፣ የ38 ዓመት ዕድሜ ያላቸው የሶስት ልጆች አባት እና በሙያቸው ሹፌር ናቸው። ባጋጠማቸው የጤና ችግር (የፊንጢጣ ፊስቱላ) ምክንያት አቶ ሰይድ በደሴ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የጽኑ ሕሙማን ክፍል ውስጥ ሕክምናቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ።
በሆስፒታሉ ቆይታቸው ስላገኙት ድጋፍ ሲናገሩ፣ "እዚህ ስመጣ ሕመሜ በጣም ከፍ ብሎ ነበር፤ ሆኖም አስፈላጊው ሕክምና ተደርጎልኝ አሁን ፈጣሪ ይመስገን ደህና ነኝ" በማለት ደስታቸውን ይገልጻሉ። ለሕመማቸውም እስከ አሁን ባለው ጊዜ ውስጥ ሶስት ጊዜ የቀዶ ጥገና ሕክምና ማድረጋቸውን ይናገራሉ።
አቶ ሰይድ የጤና መድህን አገልግሎት ለቤተሰባቸው የፈጠረውን እፎይታ ሲገልጹ እንዲህ ብለዋል፦"በእኔ የኑሮ ደረጃ ከፍሎ ለመታከም ቀርቶ፣ የዕለት ጉርስ ለማሟላትም የሚከብደኝ ሰው ነኝ። የጤና መድህን ደብተሬ ባይኖር ኖሮ፣ ሕክምና ለማግኘት ንብረቴን መሸጥ ወይም ለከባድ ብድር መዳረግ የመጀመሪያ አማራጮቼ ሊሆኑ ይችሉ ነበር። ጤና መድህን እኔን ከዚህ ሁሉ ምስቅልቅል ታድጎኛል።"
ከ2014 ዓ.ም. ጀምሮ የጤና መድህን ተጠቃሚ የሆኑት አቶ ሰይድ፣ ከጤና ጣቢያ እስከ ሆስፒታል ድረስ ያለ ተጨማሪ የኪስ ክፍያ ቤተሰባቸውን ማሳከም መቻላቸውን ይናገራሉ። በሆስፒታሉ ሁሉንም ዓይነት የላቦራቶሪ ምርመራዎች ያገኙ ሲሆን፣ አስፈላጊ ከሆነም ወደ አዲስ አበባ ሪፈር ተብለው መሄድ እንደሚችሉ ተገልጾላቸዋል።
አቶ ሰይድ፣ "ጤና መድህን ከመጀመሩ በፊት ብዙ ሰዎች ሕክምና ለማግኘት አቅም በማጣታቸው ብቻ ቤታቸው ውስጥ ሞታቸውን ይጠባበቁ የነበረበት ወቅት የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው። እኔም ቢሆን ጤና መድህን ባይኖር ምን ዓይነት ሁኔታ ሊገጥመኝ እንደሚችል ሳስበው ይከብደኛል፤ ስለዚህ 'ጤና መድህን ይቀጥልልን' ከማለት ውጭ ሌላ የምለው የለኝም" በማለት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
አቶ ሰይድ በሆስፒታሉ አገልግሎት እጅግ ደስተኛ ቢሆኑም፣ አልፎ አልፎ መድሃኒት የሚያልቅበት አጋጣሚ መኖሩን እንደ ክፍተት አንስተዋል። ቢሆንም፣ የጤና መድህን ለራሳቸው እና ለቤተሰባቸው የነፍስ አድን ስራ መሆኑን በጽኑ ያምናሉ።

"Youtube: https://www.youtube.com/-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram: https://t.me/buu

X (formerly Twitter) (https://twitter.com/service4E)
Ethiopia Health Insurance Service () / X

የተስፋው ጭላንጭል፡ የኢብራሂም ይመር የሽንፈትና የድል ታሪክ2109/2018 ዓም ኢጤመአየገራዶ መንደር አየር ንብረት ሁሌም ቢሆን ሰላማዊ ነው። ነገር ግን ለኢብራሂም ይመር ያ ሰላማዊ መንደር...
29/05/2026

የተስፋው ጭላንጭል፡ የኢብራሂም ይመር የሽንፈትና የድል ታሪክ
2109/2018 ዓም ኢጤመአ

የገራዶ መንደር አየር ንብረት ሁሌም ቢሆን ሰላማዊ ነው። ነገር ግን ለኢብራሂም ይመር ያ ሰላማዊ መንደር በበሽታና በጭንቀት የተሞላች ሆናበት ሰንብታለች። በሰውነቱ ላይ የሚሰቃይበት፣ ከአቅሙ በላይ የሆነና መፍትሄ ያጣለት የጤና ችግር በአንድ ጊዜ ተደራረገበት። ለአመታት የኖረበትና የደከመበት አቅሙ በአንዴ ከዳው፣ አልጋ ላይ ሲውል የገራዶ አካባቢ የጤና ጣቢያ ባለሙያዎችም ሁኔታው ከአቅማቸው በላይ መሆኑን ተረዱ።

በመጨረሻም፣ ወደ ደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሚያሻግረውን የሪፈር ደብዳቤ በእጁ ላይ አስጨበጡት። ያቺ የታጠፈች ወረቀት ለኢብራሂም የህይወትና የሞት ድልድይ ነበረች።
"ይህን ሁሉ ህክምና በግሌ ቢሆን ኖሮ ፈጽሞ አልችለውም ነበር..."
ይላል ኢብራሂም፣ በደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ግቢ ውስጥ ቆሞ የነበረውን አስቸጋሪ የህክምና ጉዞ ወደኋላ እያሰበ።

ወደ ሆስፒታሉ ሲመጣ በበሽታው መያዙ ብቻ ሳይሆን፣ “ህክምናውን እንዴት እችለዋለሁ?” የሚለው የገንዘብ ጭንቀት ህመሙን እጥፍ ድርብ አድርጎት ነበር። ነገር ግን በሆስፒታሉ ያገኘው እንክብካቤ፣ የባለሙያዎቹ ርህራሄና የተደረገለት ድጋፍ ያንን ከባድ የጭንቀት ማዕበል አሻገረው።

ዛሬ ኢብራሂም ይመር ከገራዶ ተነስቶ የመጣበትን ያንን ከባድ የህመም መንገድ በድል ተሻግሮታል። የደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልም ለእሱ ህይወትን አዲስ መልክ የሰጠ፣ ከአቅም በላይ የሆነውን የህክምና ሸክም ያቀለለለትና የነገ ተስፋውን የመለሰለት የጤና ተቋም ሆኖ በታሪኩ ውስጥ በደመቀ ቀለም ተመዝግቧል።
"Youtube: https://www.youtube.com/-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram: https://t.me/buu

X (formerly Twitter) (https://twitter.com/service4E)
Ethiopia Health Insurance Service () / X

የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድኅን፤ የወጣቶችም ዋስትና21/09/2018 ዓም ኢጤመአወጣት ሳዳም ይመር የ26 ዓመት ወጣት ሲሆን፣ ከሶስት ቤተሰብ አባላት ጋር በአማራ ክልላዊ መንግሥት ደሴ ከተማ ...
29/05/2026

የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድኅን፤ የወጣቶችም ዋስትና
21/09/2018 ዓም ኢጤመአ
ወጣት ሳዳም ይመር የ26 ዓመት ወጣት ሲሆን፣ ከሶስት ቤተሰብ አባላት ጋር በአማራ ክልላዊ መንግሥት ደሴ ከተማ አስተዳደር ቦሩ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 013 በተለምዶ “ቦሩ” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነዋሪ ነው። ወጣቱን በደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ያገኘነው የስኳር በሽታ ታማሚ ሆኖ የህክምና ክትትልና አገልግሎት ለማግኘት በመጣበት ወቅት ነው።
ሳዳም ስለ ማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድኅን ያለውን እምነት ሲገልጽ፣ “የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድኅን አባል የሆንኩት ወላጆቼን በማየት ነው። እነሱ በአግባቡ ሲገለገሉ አይቻለሁ። እኔን ግን በወጣትነቴ ዕድሜ ህመም ይገጥመኛል ብዬ ፈጽሞ አላሰብኩም ነበር” ብሏል።
እንደ ሳዳም ገለጻ፣ ህመም ልጅና አዋቂ፣ ሀብታምና ደሃ፣ ሴትና ወንድ፣ የተማረና ያልተማረ ሳይል በድንገት የሚከሰት ነው። በተለይም ድንገተኛ ህመም ሲከሰት ያልተጠበቀ ከፍተኛ የህክምና ወጪ ያስከትላል። ስለዚህ ከእንደዚህ ያለ ችግር ራስን ለመጠበቅ አስቀድሞ በጤና መድኅን አባልነት መዘጋጀት ተገቢ መሆኑን ይናገራል።
“ብንታመም የምንታከምበት፣ ባንታመም ደግሞ ወላጆቻችንና ሌሎች ዜጎች በአግባቡ እንዲታከሙ ድጋፍ ማድረግ እና ወጪን መጋራት ትልቅ ብልህነት ነው” ሲል ወጣቱ ያስረዳል። አባላት ጥራት ያለው ህክምና ያገኛሉ፤ በተጨማሪም ህብረተሰቡ በመደጋገፍና ወጪን በመጋራት በአንድ ሰው ላይ የሚወድቀውን የህክምና ጫና ይቀንሳል። በዚህም ወላጆቹ ከፍተኛ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጿል።
ወጣቱ በተለይ ለወጣቶች መልዕክት ሲያስተላልፍ፣ “ወጣት ስለሆንን ከህመም ነጻ እንደሆን ማሰብ የለብንም። ዛሬ ጤናማ ብንሆንም ነገ ምን እንደሚፈጠር አናውቅም። ስለዚህ ባንታመም ሌሎችን ለመደገፍ፣ ብንታመም ደግሞ ለመታከም የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድኅን አባል መሆን አስፈላጊ ነው” ብሏል።
በአሁኑ ወቅት የመድኃኒት ዋጋም በእጅጉ በጨመረበት ሁኔታ የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድኅን የሚሰጠው ጥቅም ከፍተኛ መሆኑን ሳዳም ያስረዳል። ሆኖም የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት በቂ የመድኃኒት አቅርቦት እንዲኖራቸው መደረግ እንዳለበት ጠይቋል።
የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድኅን የህብረተሰብ መተጋገዝን የሚያጠናክር፣ የህክምና ወጪን የሚያቀል እና በተለይም ድንገተኛ ህመም ሲከሰት ለዜጎች ትልቅ ዋስትና የሚሰጥ ስርዓት መሆኑን የወጣት ሳዳም ታሪክ በግልጽ ያሳያል። በመሆኑም ወጣቶችን ጨምሮ ሁሉም ዜጎች የጤና መድኅን አባል በመሆን ራሳቸውንና ህብረተሰባቸውን ከድንገተኛ የጤና ችግሮች ሊጠብቁ ይገባል።
"Youtube: https://www.youtube.com/-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram: https://t.me/buu

ከ90 በመቶ በላይ  ተገልጋዮች የጤና መድኅን ተጠቃሚዎች መሆናቸውን የደሴ ሆስፒታል አስታወቀ20/09/2018 ዓም ኢጤመአበአማራ ክልላዊ መንግስት በደሴ ከተማ የሚገኘው እና ታሪካዊው የደሴ አ...
28/05/2026

ከ90 በመቶ በላይ ተገልጋዮች የጤና መድኅን ተጠቃሚዎች መሆናቸውን የደሴ ሆስፒታል አስታወቀ
20/09/2018 ዓም ኢጤመአ
በአማራ ክልላዊ መንግስት በደሴ ከተማ የሚገኘው እና ታሪካዊው የደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል፣ በአሁኑ ወቅት እየሰጠ ካለው አጠቃላይ የህክምና አገልግሎት ውስጥ ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑት ተገልጋዮች የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድኅን ተጠቃሚዎች መሆናቸውን አስታወቀ።
የሆስፒታሉ ዋና ስራ አስኪያጅ ዶክተር ኃይማኖት አየለ ስለ ሆስፒታሉ ሰፊ የአገልግሎት ተደራሽነት ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፣ እድሜ ጠገቡ የደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በአማራ ክልል ለሚገኙ 5 ዞኖች፣ ለ2 የከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም ከአጎራባች ክልሎች ለሚመጡ በርካታ ዜጎች ተመራጭ የህክምና ማዕከል በመሆን እያገለገለ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በነዚህ አካባቢዎች የሚኖሩና ከ10 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎች የሆስፒታሉ ቀጥተኛ ተጠቃሚዎች መሆናቸውን የጠቆሙት ዋና ስራ አስኪያጇ፣ ከነዚህ ተገልጋዮች መካከል እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ወይም ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑት የጤና መድኅን አባል መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
ዶክተር ኃይማኖት ሆስፒታሉ ከ1,300 በላይ የተለያዩ የህክምና እና የአስተዳደር ባለሙያዎች አሉት፣ እንዲሁም በአካባቢው ብቸኛ የማስተማሪያ ማዕከል ከመሆኑም በላይ በርካታ የምርምር ስራዎች የሚካሄዱበት ግዙፍ የህክምና ተቋም መሆኑን አስገንዝበዋል።
ይህ የጤና መድኅን ስርአት መዘርጋቱ ለተገልጋዮች ከፍተኛ የህክምና አገልግሎትና ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እየሰጠ እንደሚገኝ ያብራሩት ዋና ስራ አስኪያጇ ፤ ቀደም ባሉት ጊዜያት ህመምተኞች ለአገልግሎት ወደ ሆስፒታሉ መጥተው፣ ነገር ግን ለህክምና የሚሆን የገንዘብ አቅም በማጣታቸው ምክንያት ብቻ ህክምናቸውን አቋርጠው ለከፋ ስቃይና ሞት ይዳረጉ እንደነበር አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅት ግን ይህ የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድኅን የተጠቃሚነት ዕድል በመፈጠሩ፣ ዜጎች ያለምንም የገንዘብ ስጋት አስፈላጊውን ህክምና በሙሉ አግኝተው በጤና ወደ መኖሪያቸው መመለስ መቻላቸውን በደስታ ገልጸዋል።
በዚህ ጊዜ በአለም አቀፍና በሀገር አቀፍ ደረጃ የህክምና መገልገያ ግብዓቶችና የመድኃኒት ዋጋ በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መምጣቱን ዶክተር ኃይማኖት አልሸሸጉም።ለምሳሌ ለአንድ ግለሰብ የሚደረግ ከፍተኛ ህክምና ወጪ ከ180 ሺህ እስከ 200 ሺህ ብር ሊደርስ እንደሚችል ጠቁመው፣ ይህንን መሰል ያልታሰበ ከፍተኛ ወጪ ማህበረሰቡ እንደሚከብዳቸው እና የህክምና ወጪን በጋራ መሸፈን አማራጭ እንደሆነ አብራርተዋል።
በመጨረሻም የደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከተለያዩ አገልግሎቶች ከሚያገኘው የውስጥ ገቢ አቅሙን በየጊዜው እያሳደገ፣ የህክምና መገልገያዎችን እያሟላ፣ የመድኃኒት አቅርቦት እና የላብራቶሪ ምርመራዎችን በአግባቡ ተደራሽ እያደረገ እንደሚገኝ ተገልጿል። ተቋሙ ተጠቃሚዎችን በማርካት የተጣለበትን ታሪካዊ ተልዕኮ እየተወጣ መሆኑን የገለጹት ዶክተር ኃይማኖት፤ ሆስፒታሉ ከበሽታ የጸዳ አምራች ማህበረሰብ በመፍጠር በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የራሱን አዎንታዊ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝና የአለም የጤና ድርጅት (WHO) ያስቀመጠውን ሁለንተናዊ የጤና ሽፋን በሀገራችን በስፋት እንዲዳረስ በትጋት እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
"Youtube: https://www.youtube.com/-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram: https://t.me/buu

የደሴ ከተማ አስተዳደር በጤና መድህን ዘርፍ ውጤታማ ስራዎችን እያከናወነ  እንደሚገኝ አስታወቀ20/09/2018 ዓም ኢጤመአየደሴ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ለህብረተሰቡ ጥራት ያለው የጤና ...
28/05/2026

የደሴ ከተማ አስተዳደር በጤና መድህን ዘርፍ ውጤታማ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አስታወቀ
20/09/2018 ዓም ኢጤመአ
የደሴ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ለህብረተሰቡ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ በተለይም በማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ዘርፍ ተጨባጭ ለውጦችን እያስመዘገበ መሆኑ ተገለጸ።
የከተማው ጤና መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ፍስሃ ዳውድ እንደገለጹት፤ መምሪያው ማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህንን እንደ ዋና የትኩረት አቅጣጫ በመያዝ እየሰራ ይገኛል። በያዝነው በጀት ዓመት 50ሺ 4 መቶ 39 ዜጎችን የጤና መድህን አባል ለማድረግ ታቅዶ፣ 52ሺ 8 መቶ 77 አባላትን ማፍራት በመቻሉ ከዕቅድ በላይ አፈጻጸም መመዝገቡን አስታውቀዋል። ከዚህም ውስጥ የመክፈል አቅም የሌላቸው 17ሺ 4 መቶ 25 ነዋሪዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል።
ይህንን ስኬት ለማምጣትም መምሪያው ባለሙያዎችንና አመራሮችን በየደረጃው ባሉ መዋቅሮች በመመደብ በትኩረት እንዲሰሩ ማድረጉን የጠቀሱት አቶ ፍስሃ፣ በተለይም አቅመ ደካሞችን በዘርፉ ለማካተት "የቤተሰብ ትስስር" በሚል ጽንሰ-ሀሳብ፣ አቅም ያላቸውን ባለሀብቶች ከነዚህ ዜጎች ጋር በማስተሳሰር የክፍያ አቅማቸውን የመደገፍ ስራ መሰራቱ በምሳሌነት አንስተዋል።
የጤና መድህን ተጠቃሚዎች ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግም የጤና ተቋማት አቅም እየተገነባ ነው። በዚህም መሰረት አዳዲስ የህክምና መሳሪያዎችን ማሟላት፣ የህክምና ባለሙያዎችን መቅጠር መቻሉ ተመላክቷል።
በጤና ተቋማት ያለውን የመድሃኒት አቅርቦት ለማሻሻል ለጤና ተቋማቱ የገንዘብ እገዛ በማድረግና በከተማዋ አምስት የማህበረሰብ አቀፍ መድሃኒት ቤቶች ተከፍተው አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን ያስታወሱት አቶ ፍስሃ ፣የደሴ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለከተማዋና ለአካባቢው ህዝብ የሚሰጠውን ሰፊ አገልግሎት ታሳቢ በማድረግም መምሪያው ልዩ ድጋፍ እያደረገለት ይገኛል።
በሌላ በኩል፣ የጤናው ዘርፍ ሰራተኞችና ቤተሰቦቻቸው የሚታከሙበት "የማህበራዊ ጤና መድህን" መጀመሩ፣ ቀደም ሲል ለብዙ ቅሬታዎች መንስኤ የነበረውን ህጋዊነት የጎደለው አሰራርና በሪፈር ሂደት ያጋጥሙ የነበሩ ችግሮችን መቅረፉን ያስረዱት ምክትል ኃላፊው ይህም ለሰራተኞች የስራ ተነሳሽነት ከመፍጠሩም በላይ መልካም አስተዳደርን በማስፈን ረገድ ትልቅ ሚና ተጫውቷል ብለዋል።
"ዜጎች አምራች የሚሆኑት ጤናማ ሲሆኑ ነው" ያሉት አቶ ፍስሃ፣ ጤና መድህን በድንገተኛ የህክምና ወጪዎች ምክንያት የዜጎችን ንብረት መውደም የሚከላከል፣ በህክምና ተቋማት ፍትሃዊና ተደራሽ አገልግሎትን የሚያረጋግጥ ወሳኝ አገልግሎት መሆኑን ጠቁመዋል።
በከተማው የሚደረጉ ህዝባዊ ውይይቶችም የሚገልጹልን የጠቃሚዎች በጤና መድህን ደብተር እስከ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ድረስ ያለ ተጨማሪ ወጪ ህክምና ማግኘት መቻላቸውን እንደሚያረጋግጡላቸው ተናግረዋል።
በመጨረሻም አቶ ፍስሃ ዳውድ፣ ከተማዋ በርካታ የግል የጤና ተቋማት ያሉባት በመሆኑ፣አባል በማፍራትና በእድሳት ወቅት ከሚሰራጩ መሰረተ ቢስ ከሆኑ መረጃዎች እራሱን በማራቅ፣መላው የከተማዋ ነዋሪ የጤና መድህን ተጠቃሚ በመሆን እራሱንና ቤተሰቡን ድንገተኛ የህክምና ወጭ ይዞት ከሚመጣው ማህበራው ቀውስ እንድጠብቅ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
"Youtube: https://www.youtube.com/-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram: https://t.me/buu

Address

Nifase Silke Lafto Around Gotera Pepsi , GUAVA Building
Addis Ababa
21254/1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Health Insurance Service posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share