Federal First Instance Court Of Ethiopia

  • Home
  • Federal First Instance Court Of Ethiopia

Federal First Instance Court Of Ethiopia Justice Organization

በዲጂታል ፋይናንስ  ወንጀሎች ዙሪያ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ዎርክሾፕ በዛሬዉ እለት ተጀመረ።********** የፌደራል ፍርድ ቤቶች ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር “Combating Di...
05/06/2026

በዲጂታል ፋይናንስ ወንጀሎች ዙሪያ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ዎርክሾፕ በዛሬዉ እለት ተጀመረ።
**********

የፌደራል ፍርድ ቤቶች ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር “Combating Digital Banking Fraud: The Way Forward for Effective Prevention and Enforcement." በሚል ርዕስ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ዎርክሾፕ በዛሬዉ እለት ተጀመረ።

በ ዎርክሾፑ መክፈቻ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክብርት ወ/ሮ ሌሊሴ ደሳለኝ ፣ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ፋዓድ ኪያር ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮርፖሬት አጠቃላይ አገልግሎቶች ስራ አስፈፃሚ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ በመገኘት የመክፈቻ ንግግሮች ያደረጉ ሲሆን የፌደራል የከፍተኛ እና የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞች ፣ ዐቃቢያን ህጐች እና የባንኩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እየተሳተፋ ይገኛሉ ።

ለሁለት ቀናት በሚቆየዉ ዎርክሾፕ "Understanding Digital Banking Business, Combating Digital Banking Crimes - Legal and Regulatory Perspectives, Fraud Awareness and Cyber Security, Digital Banking Frauds in Financial Sector በሚሉ ርዕሶች ላይ ፁሁፎች ቀርበዉ ዉይይት የሚደረግባቸዉ ይሆናል።

የሀዘን መግለጫ------‎በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩት ክቡር ዳኛ ሽመክት አሰፋ ህልፈተ ህይወት የተሰማንን ሀዘን እየገለፅን ለቤተሰቦቹ÷ ለወዳጆቹ እና ለስራ ...
04/06/2026

የሀዘን መግለጫ
------
‎በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩት ክቡር ዳኛ ሽመክት አሰፋ ህልፈተ ህይወት የተሰማንን ሀዘን እየገለፅን ለቤተሰቦቹ÷ ለወዳጆቹ እና ለስራ ባልደረቦች መፅናናትን እንመኛለን::
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት !

የፍርድ ቤት መር አስማሚነትን ከባህል እና ሽምግልና ስርአት እንዲሁም ከሃይማኖት አባቶች ጋር  ለማቀናጀት የምክክር መድረክ በድሬደዋ ከተማ ተካሄደ።************የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ...
04/06/2026

የፍርድ ቤት መር አስማሚነትን ከባህል እና ሽምግልና ስርአት እንዲሁም ከሃይማኖት አባቶች ጋር ለማቀናጀት የምክክር መድረክ በድሬደዋ ከተማ ተካሄደ።
************
የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እያከናወነ ያለውን የፍርድ ቤት መር አስማሚነት የበለጠ ለማጠናከርና የህብረተሰቡን ተሳትፎ ለማሳደግ ይጠቅም ዘንድ ከድሬደዋ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በከተማ አስተዳደሩ ካሉ የባህል ሽማግሌዎች (አባ ገዳና ኡጋዝ) እንዲሁም ከሃይማኖት አባቶች ጋር የውይይት መድረክ በድሬዳዎ አስተዳደር ምክር ቤት አካሂዶል ።
በመድረኩም የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ወደ ፍርድ ቤቱ የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ትግበራ ሥርዓት በመግባት አገልግሎት የሚሰጡበትና የፍትህ ተደራሽነትን በሚያረጋግጡበት መንገድ ላይ ውይይት ተደርጓል።
በተለይም የድሬደዎ ከተማ የበርካታ ብሔር ብሔረሰቦች እና ሀይማኖቶች መገኛ እንደመሆኗ የፍርድ ቤት መር አስማሚነትን ከባህል እና ሽምግልና ስርአት እንዲሁም ከሃይማኖት አባቶች ጋር ማቀናጀት እንደሚገባ ተገልፃል።
በመድረኩ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ፉአድ ኪያር እና የድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ የተከበሩ አቶ ከድር ጁሀር የተገኙ ሲሆን
በቀጣይ ፍርድ ቤቱ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር የመግባቢያ ሰነድ በመፈረም: ወደ ስራው ለሚገቡም አስማሚዎች መሠረታዊ የህግና የአሰራር መመሪያ ስልጠና በመስጠት ወደ ትግበራ ስራው እንደሚገባ ተገልፃል።

ተጫራቾች ተጋብዛችኋል !!*******የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለዋና መስሪያ ቤት እና በኢፌ.ዴ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ ዘርፍ ለልደታ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት በአዲስ ...
02/06/2026

ተጫራቾች ተጋብዛችኋል !!
*******
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለዋና መስሪያ ቤት እና በኢፌ.ዴ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ ዘርፍ ለልደታ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት በአዲስ የሚገነቡ ህንፃዎች (2B+G+11 እና 2B+G+6) በተመለከተ የዲዛይን የአፈር ምርምራ እናየማማከር ስራውን በማጠናቀቅ የግንባታ ሂደቱን በግልጽ ጨረታ አውጥቷል፡፡
ስለሆነው በዚህ አለም አቀፍ ግልፅ ጨረታ ላይ መሳተፍ የሚፈልጉ ተቋራጮች በሙሉ የጨረታ ሰነዱን ከመንግስት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ (Egp) ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እየገለጽን ተጫራቾች ከዚህ በታች በተያያዘው ሊንክ ወይም በመንግስትየኤሌክትሮኒክስ ግዥ (Egp) ድህረ ገጽ በመግባት በጨረታእንድትሳተፉ ተጋብዛችኋል፡፡

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት!

https://production.egp.gov.et/__--

‎ዘመናዊ የህጻናት ማስመስከሪያ ክፍል የስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ ።*********‎በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት የተሰራ ዘመናዊ የህጻናት ማስመ...
26/05/2026

‎ዘመናዊ የህጻናት ማስመስከሪያ ክፍል የስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ ።
*********
‎በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት የተሰራ ዘመናዊ የህጻናት ማስመስከሪያ ክፍል (One way mirror) በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አዲስ ከተማ ምድብ ችሎት በይፋ ስራ ጀምሯል።

‎የህጻናት ፍትህ አስተዳደርን ለማዘመን እንደሚያግዝ የተገለጸው ይህ ክፍል የስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ክብርት ወ/ሮ አበባ እምቢአለ በተገኙበት ተከናውኗል።

‎ትኩረት የሚሹ የማህበረሰብ ክፍሎችን በዳኝነት አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ በትኩረት የሚሰራበት መሆኑ እና ለህጻናት ምቹ ችሎትን ከመፍጠር አንጻር የሚሰሩ ስራዎች የዚሁ ግብ አካል መሆናቸው በመርሃ ግብሩ ላይ ተገልጿል።

‎ምንጭ:- ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት

ኢድ-ሙባረከ ! ********የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ፣ እንኳን ለ1447ኛው ዓመተ ሂጅራ የአረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ በማለት መልካም ...
26/05/2026

ኢድ-ሙባረከ !
********
የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ፣ እንኳን ለ1447ኛው ዓመተ ሂጅራ የአረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ በማለት መልካም ምኞቱን ይገልፃል።

ድህረ-ውሣኔ ኦዲት*********የዳኝነት አገልግሎት ጥራትን ከሚያረጋግጡ ቁልፍ መሳሪያዎች አንዱ ተከታታይነት ያለው የድህረ-ውሣኔ ኦዲት ስራ መስራት ነው፡፡ በተለይም ጥራትን ለማረጋገጥ፣ወጥነ...
25/05/2026

ድህረ-ውሣኔ ኦዲት
*********
የዳኝነት አገልግሎት ጥራትን ከሚያረጋግጡ ቁልፍ መሳሪያዎች አንዱ ተከታታይነት ያለው የድህረ-ውሣኔ ኦዲት ስራ መስራት ነው፡፡ በተለይም ጥራትን ለማረጋገጥ፣ወጥነት ያለው አሠራርን ለማስፈን፣የስልጠና ፍላጎትን ለመለየት፣ተጠያቂነት እና ግልፅነት ለማስፈን: ክፍተቶችን ለይቶ ለማስተካከል እና የሕዝብ አመኔታ ለማግኘት የድህረ-ኦዲት ውሣኔ አስፈላጊ ነው፡፡
ከዚህ አንፃር የፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት የዳኝነት ጥራትን ለማረጋገጥ በተለይም የመዛግብት ሙሉ ሂደታቸዉን መሠረታዊ እና ስነ-ስርዓታዊ ህጐችን የተከተለ ስለመሆኑ ለማረጋገጥ በዳኝነት ኢንስፔክሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሰብሳቢነት የሚመራ የዳኞች ኮሚቴ በማዋቀር የድህረ-ውሣኔ ኦዲት ስራ አከናውኗል፡፡
ኮሚቴው የድህረ-ውሣኔ ኦዲት ግኝት የመጀመሪያ ረቂቁን በዛሬው እለት የፍ/ቤቱ ኘሬዝዳንት ክቡር አቶ ፉአድ ኪያር፣የፍ/ቤቱ ማኔጅመንት አባላት፣የሁሉም ምድብ ችሎት ተጠሪዳኞች እና የዳኞች ፎረም ሰብሳቢዎች በተገኙበት አቅርበዋል፡፡
የመጀመሪያ ረቂቅ ሰነድ ገለፃ በኮሚቴው ሰብሳቢ ዳኛ ዳንኤል አበበ እና ዳኛ ዳንኤል ዱጋሳ የቀረበ ሲሆን ሠነዱ ከቀረበ ቡኋላ ከተሳታፊዎች በርካታ አስተያየት እና ጥያቄዎች ተነስተው ሰነዱ እንዲዳብር ተደርጓል፡፡
በቀጣይም ሠነዱ የመጨረሻ ይዘቱን ከያዘ ቡሃላ ለባለድርሻ አካላት እና ለሁሉም ዳኞች ለውይይት የሚቀርብ ይሆናል፡፡

ቅን ኢትዮጵያ  ማህበር  ለህፃናት ማቆያ አገልግሎት  የሚውሉ ቁሳቁሶችን  ለፌደራል መጀመሪያ  ደረጃ ፍርድ ቤት ድጋፍ አደረገ። ማህበሩ በፍርድ ቤት ለሚገኙ ሰራተኛ እናቶች በስራ ቦታቸው ላይ...
21/05/2026

ቅን ኢትዮጵያ ማህበር ለህፃናት ማቆያ አገልግሎት የሚውሉ ቁሳቁሶችን ለፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ድጋፍ አደረገ።

ማህበሩ በፍርድ ቤት ለሚገኙ ሰራተኛ እናቶች በስራ ቦታቸው ላይ ሆነው በልጆቻቸው ሁኔታ እንዳይጨናነቁ በቅርበት ልጆቻቸውን እንዲገናኙ በፍርድ ቤቱ ውስጥ የህፃናት ማቆያ መቋቋሙን በማድነቅ የበኩሉን ይህንን ቀና ተግባር ለመደገፍ ለዚህ የህፃናት ማቆያ ድጋፍ ማድረጉን ገልፃል።

በርክክብ ስነ ስርዓቱ ላይ የማህበሩ አመራሮች የተገኙ ሲሆን ቅን ኢትዮጵያ ማህበር የኢትዮጵያ ሕዝቦች የመከባበርን፣ በጎ አስተሳሰብን እና የመደናነቅን ባህል የኑሮ ዘይቤያቸው ሆኖ ማየትን ራዕይ አድርጎ በበጎ ፈቃደኞች በ2002 ዓ.ም የተመሰረተ መንግስታዊ ያልሆነ ሀገር በቀል ማህበር ነው። በውጤቱም መልካም ሥነ ምግባር፣ ቅንነትና ታማኝነት እንዲጎለብቱ የበኩሉን ለመወጣት የሚንቀሳቀስ ሀገር ድርጅት ነው፡፡ ማህበሩ በባለ ራዕዮ እና የሃሳቡ አመንጪ በሆኑት ዶክተር ቶሎሳ ጉዲና የተመሰረተ ሲሆን ማህበሩ ወጣቶች እና ታዳጊዎችን በቅንነት ላይ የሚያስተምር ፣ ልምድ የሚያለዋውጥ እና ስልጠና የሚሰጥ መሆኑን በመግለፅ ረዕዮን በማጋራት የፍርድ ቤቱ አመራሮች፣ ዳኞች እና ሰራተኞች ስለ ሃገራችን ቅንነት የትም ቦታ ስለሚያስፈልግ በጋራ ለቅንነት እንስራ ብለዋል።
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት የተከበሩ አቶ ፋዓድ ኪያር በበኩላቸዉ ሁላችንም በቅንነት መንገድ ብንሰራ ሃገራችንን ለዜጎቿ የተሻለች እንድትሆን እናደርጋለን በመሆኑም ጅማሯችሁን ስላየን ለፍርድ ቤታችንም ስለሚጠቅም ከቅን ኢትዮጵያ ጋር በተለይ የፍትህ ስርዓቱን ነፃነት እና ገለልተኝነት በጠበቀ መልኩ ከስልጠና ጋር በተያያዙ ጉዳዮች አብረን እንሰራለን ብለዋል።
በርክክብ ስነ ስርአቱ ላይ የፍርድ ቤቱ የማኔጅመንት አባላት እንዲሁም የቀድሞዋ ምክትል ፕሬዝዳንት ክብርት ወይዘሮ አሸነፈች አበበ እና ጉዳዩ የሚመለከታቸው ዳይሬክተሮች እንዲሁም በቅን ኢትዮጵያ ማህበር በኩል ወይዘሮ መሰረት ስዪም የማህበሩ የቦርድ ሊቀ መንበር ፣ አቶ መላኩ ስብሃቱ ምክትል ሊቀ መንበር፣ ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማሪያም የማህበሩ አባል እና ወይዘሪት ቅድስት ከተማ የማህበሩ ፕሮግራም ኦፊሰር ተገኝተዋል።

“ከሙግት ወደ መስማማት፦ የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ለተፋጠነ እና ጥራት ላለዉ  ፍትህ “ በሚል በፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት እና አባይ ቲቪ በጋራ የተዘጋጀዉን ኘሮግራም ይከታተሉ!
14/05/2026

“ከሙግት ወደ መስማማት፦ የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ለተፋጠነ እና ጥራት ላለዉ ፍትህ “ በሚል በፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት እና አባይ ቲቪ በጋራ የተዘጋጀዉን ኘሮግራም ይከታተሉ!

በዚህ የፍትሕ ለሃገሬ ልዩ ፕሮግራማችን የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የፍርድ ቤት መር አስማሚ አገልግሎት ምን እንደሚመስል እናሳያችኋለን። ፕሮግራሙ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረ...

በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ተክኖሎጂ /ICT/ አገልግሎት መገልገያ መሳሪያዎች አያያዝ፣ አስተዳደር እና ጥገና ላይ ያተኮረ የግንዛቤ መሰጨበጫ ሰልጠና እየተሰጠ ነው፡፡****** የፌዴራል መጀመረ...
12/05/2026

በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ተክኖሎጂ /ICT/ አገልግሎት መገልገያ መሳሪያዎች አያያዝ፣ አስተዳደር እና ጥገና ላይ ያተኮረ የግንዛቤ መሰጨበጫ ሰልጠና እየተሰጠ ነው፡፡
******
የፌዴራል መጀመረያ ደረጃ ፍርድ ቤት የኢንፎርሜሸን እና ኮሙዩኒኬሸን ዳይሬክቶሬት በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ተክኖሎጂ /ICT/ አገልግሎት መገልገያ መሳሪያዎች አያያዝ፣ አስተዳደር እና ጥገና ላይ ያተኮረ የግንዛቤ መሰጨበጫ ሰልጠና ልደታ በሚገኘው የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈፃፀም ህንፃ ላይ በመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለሚገኙ የሁሉም ምድብ ችሎት እና የዋናው መስሪያ ቤት የአይሲቲ ቡድን መሪዎች እና የጥገና ባለሙያዎች ከግንቦት 4 እስከ 7 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ የአራት ቀናት ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡
ስልጠናውን አስመልክቶ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የፌዴራል መጀመረያ ደረጀ ፍርድ ቤት የአስተዳደር እና ሰው ሃብት ስራ አመራር ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ክቡር ዳኛ የምሰራች ከተማ የሰልጠናው ዋና አላማ በየምድብ ችሎቱ እና በዋና መሰረያ ቤት የሚገኙ ባለሙያዎች በንድፈ ሃሳብ የቀሰማችሁትን በልምድ ልውውጥ እና በተግባር ሙከራ ከሚገኝ ስልጠና በመመስረት ችግር ፈቺ የሆነ እውቀት በመጨበጥ በየስራ ቦታችሁ ለሚገጥሙ ችግሮች መፍትሄ አፍላቂ እና ችግር ፈቺ እንድትሆኑ ለማስቻል በዚህም የለሙ መተግበሪያዎች በአግባቡ አገልግሎቱን ለሚሰጡ ስራ ክፍሎች በማስረዳት በተገቢው ጥቅም ላይ እንዲያውሉት እና በአጠቃቀም የሚታዩ ክፍተቶችን በቀላሉ መፍትሄ ለመስጠት እንድትችሉ እንዲሁም በሶፍት እና ሃርድ ዌር አስተዳደር ላይ የሚታዩ ችግሮችን እንድትቀርፉ ስልጠናው በተደጋጋሚ እየተሰጠ መሆኑን በመግለፅ ተሳታፊዎች በአግባቡ እና በትጋት ስልጠናውን እንዲከታተሉ በአፅንኦት አሳስበዋል፡፡
የፌዴራል መጀመረያ ደረጀ ፍረድ ቤት የኢንፎርሜሸን ኮምዩንኬሸን ቴክኖሎጂ ዳይሬክቶትሬት የሰራተኛን አቅም እና ክህሎት ለማሳደግ በርካታ ሰልጣናዎችን እየሰጠ እንደሚገኝ አቶ ሃጎስ ግርማይ የስራ ክፍሉ ዳይሬክተር የገለፁ ሲሆን ስልጠናውን የኮምፒውተር ጥገና ቡድን መሪዋ ወይዘሪት ሳምራዊት ቱራ እና የኮምፒውተር ኤሌክትሮኒክሰ ጥገና ቴክኒሻን አቶ አያሌው አለሙ በኮምፒውተር፣ ፕሪንተር፣ ላፕቶፕ፣ ፎቶ ኮፒ ማሽን እና ዩፒኤሰ ባትሪ ጥገና ላይ በተግባር በተመሰረተ መንገድ እና አሳታፊ በሆነ ዘዴ እንደሚሰጡ ገልፀዋል፡፡

Address


LIDETASUBCITY

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Federal First Instance Court Of Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Federal First Instance Court Of Ethiopia:

  • Want your organization to be the top-listed Government Service?

Share