Ministry of Transport and Logistics - Ethiopia

Ministry of Transport and Logistics - Ethiopia Ministry of Transport and Logistics የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር

11/06/2026
የህዝብ ትራንስፖርት ኤሌክትሮኒክስ ትኬት አገልግሎት አሰጣጥን በሙከራ ደረጃ ኦንላይን  ለማድረግ ከልዩ ባስ አገልግሎት ሰጭ ኦፕሬተሮች ጋር ውይይት ተደረገ ሰኔ 4/2018 ዓ.ም (ትሎሚ):- ...
11/06/2026

የህዝብ ትራንስፖርት ኤሌክትሮኒክስ ትኬት አገልግሎት አሰጣጥን በሙከራ ደረጃ ኦንላይን ለማድረግ ከልዩ ባስ አገልግሎት ሰጭ ኦፕሬተሮች ጋር ውይይት ተደረገ

ሰኔ 4/2018 ዓ.ም (ትሎሚ):- የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ደኤታ ክቡር አቶ በርኦ ሀሰን የህዝብ የትራንስፖርት ትኬት አገልግሎት አሰጣጥን በሙከራ ደረጃ ኦንላይን ለማድረግ ከልዩ ባስ አገልግሎት ሰጭ ኦፕሬተር ኃላፊዎች ጋር ውይይት አድርገዋል።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር የተዘጋጀው የህዝብ ትራንስፖርት ማኔጅመንት ሲስተም በሙከራ ደረጃ በልዩ ባስ አገልግሎት ሰጭዎች ተግባራዊ ሆኖ በቀጣይ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንደሚሆን ተገልጿል።

የተዘጋጀው ይህ የህዝብ ትራንስፖርት ማኔጅመንት ሲስተም ተሳታፊው ባለበት ቦታ ሆኖ ትኬት መቁረጥ የሚያስችል፣ ታሪፍ የማወቅ፣ የመስመሩን መነሻ እና መድረሻ የመለየት፣ የተሽከርካሪውን መነሻ ቦታ ቀን ስዓት መለየት የሚያስችል በመሆኑ በቅርቡ በሙከራ ደረጃ ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር መረጃዎችን ለማግኘት👇👇👇

በድረ ገጽ፡

www.motl.gov.et

በፌስቡክ
https://www.facebook.com/EthiopianTransport?mibextid=ZbWKwL

በቴሌግራም:
https://t.me/ministryoftransportethiopia

በዩቲዩብ

https://youtube.com/

በትዊተር

https://x.com/MoTLogestics

በቲክቶክ

https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZS-93fuvA1twuuy

የአዲሱ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ስርጭትን በትዕግሥት ስለጠበቃችሁ ከልብ እናመሰግናለን!ዛሬ የአዲሱ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ስርጭት በአዲስ አበባ በይፋ ተጀምሯል። አገልግሎቱ ቀልጣፋ፣ ግልጽ...
11/06/2026

የአዲሱ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ስርጭትን በትዕግሥት ስለጠበቃችሁ ከልብ እናመሰግናለን!

ዛሬ የአዲሱ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ስርጭት በአዲስ አበባ በይፋ ተጀምሯል።

አገልግሎቱ ቀልጣፋ፣ ግልጽ እና ተደራሽ እንዲሆን የሚያስፈልጉ ዝግጅቶች ተደርገዋል።

የአዲሱ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ስርጭትን በትዕግሥት ስለጠበቃችሁ ከልብ እናመሰግናለን!ዛሬ የአዲሱ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ስርጭት በአዲስ አበባ በይፋ ተጀምሯል። አገልግሎቱ ቀልጣፋ፣ ግልጽ...
11/06/2026

የአዲሱ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ስርጭትን በትዕግሥት ስለጠበቃችሁ ከልብ እናመሰግናለን!

ዛሬ የአዲሱ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ስርጭት በአዲስ አበባ በይፋ ተጀምሯል።

አገልግሎቱ ቀልጣፋ፣ ግልጽ እና ተደራሽ እንዲሆን የሚያስፈልጉ ዝግጅቶች ተደርገዋል።

11/06/2026

ውድ ኢትዮጵያውያን ለ5 ሚሊዮን ኮደሮች ምዕራፍ ስኬት እንኳን ደስ አላችሁ!

‎በሦስት ዓመታት ውስጥ ለማሳካት የታቀደውን ግብ ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማሳካት ተችሏል። የ«5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች» ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ፣ በመረጃ ትንተና፣ በአንድሮይድ ሶፍትዌር ልማት እና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ ትምህርቶች 5,005,146 ሰልጣኞች ተመዝግበው ከ3 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ስልጠናውን አጠናቀዋል። ይህ ስኬት የሕዝባችንን ቁርጠኝነት እና ወሰን የሌለው አቅም ማረጋገጫ ነው።

‎በዲጂታሉ ዓለም በልኩ ለመዘጋጀት የጀመርነው ታሪካዊ ምዕራፍ፤ የጉዟችን ማብቂያ ሳይሆን፥ ብሔራዊ ርዕያችንን ይበልጥ የምናፋጥንበት መነሻ ነው። እስከ ነሐሴ 2018 ዓ.ም. ድረስ የሰልጣኞችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ የተሰነቀውን ግብ ለማሳካት፥ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የዚህ ብሔራዊ ተልዕኮ አካል እንዲሆን ጥሪዬን አቀርባለሁ።

‎ለወጣት ተማሪዎቻችን፤ መጭው የክረምት ወቅት ትልቅ ዕድላችሁ ነው። ጊዜያችሁን በዋዛ ከማሳለፍ ተቆጥባችሁ፤ በመመዝገብና በመማር ወደ ትምህርት ገበታችሁ ስትመለሱ ተማሪዎች ብቻ ሳትሆኑ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላችሁ የዲጂታል መሪዎች እንድትሆኑ አሳስባለሁ። ሥልጠናዎቹ ሙሉ በሙሉ በነጻ የሚሰጡ ሲሆን፥ የምስክር ወረቀቱም በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለው ነው።

‎የምትገነቡት ነገ የሚጀምረው ዛሬ ነው!

‎ለመመዝገብ እዚህ ይጫኑ:
‎ethiocoders.et/

Itoophiyaanota jaallatamtoota, boqonnaa milkaa’inaa kooderoota miliyoona 5 tiif baga gammaddani!

Galma waggoota sadii keessatti milkeessuuf karoorfame waggoota lamaa gaditti milkeessuun danda’ameera. Sagantaan “Kooderoota Itoophiyaa Miliyoona Shan” Adoolessa 16 bara 2016 edda eegalamee barnoota bu’uraa piroograamiingii kompiiwuteraa, odeeffannoo qaaccessuu, misooma sooftiweerii Andirooyidiifi Artifiishaal intelejensiitiin leenjitoota 5,005,146 galmaa’an keessaa miliyoona sadii ol kan ta’an leenjicha xumuraniiru. Milkaa’inni kun kutannoofi human uummata keenyaa hin daangeffamneef ragaadha.

Boqonnaan seena qabeessi addunyaa dijitaalaatiif haalaan qophaa’uuf eegalle kun dhuma imala keenyaa utuu hin ta’iin, ka’umsa mul’ata keenya biyyaalessaa caalatti ittiin saffisiifnudha. Galama hanga Hagayya 2018 tti lakkoofsa leenjitootaa miliyoona torbaan gahuuf qabame milkeessuuf, lammiin Itoophiyaa hundi qaama ergama biyyaalessaa kanaa akka ta’un waamichakoo dhiyeessa.

‎Barattoonni dargaggoonni keenya waktii gannaa dhufu kanatti kanaaf carraa guddaa qabdu. Yeroo keessan waan hin mallerratti dabarsuu dhiiftanii galmooftanii barachuudhaan wayita gara barnoota keessaniitti deebitan barattoota qofaa utuu hin ta’iin hooggantoota dijitaalaa sadarkaa addunyaatti beekamtii qabdan akka taatanin isin hubachiisa. Leenjiiwwan kunneen guutummaadhaan tolaan kan kennaman yoo ta’an, waraqaan ragaasaas sadarkaa addunyaatti beekamtii kan qabudha.

Egereen ijaartan har’a jalqaba!‎
Galmaa’uuf hidha kana cuqaasaa: ethiocoders.et/


𝐂𝐎𝐍𝐆𝐑𝐀𝐓𝐔𝐋𝐀𝐓𝐈𝐎𝐍𝐒, 𝐅𝐄𝐋𝐋𝐎𝐖 𝐄𝐓𝐇𝐈𝐎𝐏𝐈𝐀𝐍𝐒 𝐎𝐍 𝐓𝐇𝐄 𝟓 𝐌𝐈𝐋𝐋𝐈𝐎𝐍 𝐂𝐎𝐃𝐄𝐑𝐒 𝐌𝐈𝐋𝐄𝐒𝐓𝐎𝐍𝐄!

What we set out to achieve in three years, we have accomplished in less than two. Since the launch of the 5 Million Ethiopian Coders Initiative on July 23, 2024, Ethiopia has reached 5,005,146 enrollments across Programming, Data Analysis, Android Development, and Artificial Intelligence fundamentals. This is our testament to our people's determination and limitless potential.

This milestone is not where our ambition ends, it is where it accelerates further. With 7 million enrollments by August 2026 firmly within our vision, I call upon every Ethiopian to be part of this national mission.

To our young students, this summer is your opportunity. Do not let it pass idly. Register, learn, and return to your classrooms not just as students, but as certified digital leaders. The courses are free, the certification is internationally recognized.

The future you build starts today!

ENROLL NOW:
ethiocoders.et/

11/06/2026
ኢትዮጵያ እና አርሜንያ በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍ ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለፀ ሰኔ 1/2018 ዓ.ም (ትሎሚ)፦የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አለሙ ...
08/06/2026

ኢትዮጵያ እና አርሜንያ በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍ ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለፀ

ሰኔ 1/2018 ዓ.ም (ትሎሚ)፦የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አለሙ ስሜ ከአርሜንያ አምባሳደር ሻሀክ ሳርጌሳን ጋር በፅ/ቤታቸው ባደረጉት ውይይት ኢትዮጵያ እና አርሜንያ በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍ ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተወያይተዋል።

ሁለቱም ሀገራት ረጅም የሆነ ጠንካራ እና ታሪካዊ ግንኙነት ያላቸው መሆኑን የተገለፀ ሲሆን በሎጂስቲክስ፣ በአየር ትራንስፖርት፣ በአቪዬሽን እና በደረቅ ወደብ በትብብር እና በመደጋጋፍ መስራት እንደሚፈልጉ ውይይት አድርገዋል።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር መረጃዎችን ለማግኘት👇👇👇

በድረ ገጽ፡

www.motl.gov.et

በፌስቡክ
https://www.facebook.com/EthiopianTransport?mibextid=ZbWKwL

በቴሌግራም:
https://t.me/ministryoftransportethiopia

በዩቲዩብ

https://youtube.com/

በትዊተር

https://x.com/MoTLogestics

በቲክቶክ

https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZS-93fuvA1twuuy

ማስታወቂያ የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር ከሰኞ ሰኔ 1/2018  ዓም ጀምሮ ወረቀት አልባ የአገልግሎት አሠጣጥ ይጀምራል ።በዚህም መሠረት ማንኛውንም አገልግሎት ፈላጊ ወደ ተቋሙ በአ...
08/06/2026

ማስታወቂያ

የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር ከሰኞ ሰኔ 1/2018 ዓም ጀምሮ ወረቀት አልባ የአገልግሎት አሠጣጥ ይጀምራል ።

በዚህም መሠረት ማንኛውንም አገልግሎት ፈላጊ ወደ ተቋሙ በአካል ከመምጣቱ በፊት ከዚህ በታች በተቀመጠው URL ወይም QR code እስካን በማድረግ ኦን ላይን ቀጠሮ ማሲያዝና የሚመለከተው ኃላፊ ምላሽ መስጠቱን ማረጋገጥ እንዲሁም ወደ ተቋሙ የሚላኩ ደብዳቤዎችም በዚሁ መልክ መላክ ይጠበቅበታል ።

በመሆኑም ምላሽ ሲሰጥ እንዲደርሳችሁ ትክክለኛ ኢሜይል እና ስልክ ቁጥር ማስገባት ይጠበቅባችኋል::

ማሳሰቢያ፦ ለሎጀስቲክስ ፣ ለአሽከርካሪ እና ተሽከርካሪ ፣ ማሽነሪ አገልግሎት የምትመጡ ለጊዜው መስተናገድ ትችላላችሁ::

https://visit.gdop.gov.et/MOTL

05/06/2026
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትሩ ክቡር  ዶ/ር አለሙ ስሜ በኢትዮጵያ  የኬንያ አምባሳደር ጋልማ ሙኪሂንን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው በሁለቱ ሀገራት የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍ...
05/06/2026

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትሩ ክቡር ዶ/ር አለሙ ስሜ በኢትዮጵያ የኬንያ አምባሳደር ጋልማ ሙኪሂንን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው በሁለቱ ሀገራት የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍ ትብብር ላይ ተወያይተዋል፡፡

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር መረጃዎችን ለማግኘት👇👇👇

በድረ ገጽ፡

www.motl.gov.et

በፌስቡክ
https://www.facebook.com/EthiopianTransport?mibextid=ZbWKwL

በቴሌግራም:
https://t.me/ministryoftransportethiopia

በዩቲዩብ

https://youtube.com/

በትዊተር

https://x.com/MoTLogestics

በቲክቶክ

https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZS-93fuvA1twuuy

Address

Addis Ababa
1238

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ministry of Transport and Logistics - Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ministry of Transport and Logistics - Ethiopia:

Share