Ministry of Transport and Logistics - Ethiopia

Ministry of Transport and Logistics - Ethiopia Ministry of Transport and Logistics የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር

አረንጓዴ ትራንስፖርትን ለማስፋፋት ዓለም አቀፍ ትብብር ወሳኝ መሆኑ ተገለጸየኖርዲክ–አፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ በኢትዮጵያ ሳይንስ ሙዚየም እየተካሄደ ነው።መስከረም 5/2019 ዓ.ም (ትሎሚ...
15/09/2026

አረንጓዴ ትራንስፖርትን ለማስፋፋት ዓለም አቀፍ ትብብር ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ

የኖርዲክ–አፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ በኢትዮጵያ ሳይንስ ሙዚየም እየተካሄደ ነው።

መስከረም 5/2019 ዓ.ም (ትሎሚ) — የአየር ንብረት ተፅዕኖን ለመቋቋም፣ የአማቂ ጋዝ ልቀትን ለመቀነስና ዘላቂ የልማት አማራጮችን ለማስፋፋት አረንጓዴ ትራንስፖርትን ማሳደግ እንዲሁም ዓለም አቀፍ ትብብርን ማጠናከር ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ።

ጉባኤው በኖርዲክ ሀገራትና በአፍሪካ መካከል በአካባቢ ጥበቃ፣ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ፣ በታዳሽ ኃይልና በዘላቂ ትራንስፖርት ዘርፎች ያለውን ትብብር ለማጠናከርና ለአየር ንብረት ለውጥ ተግባራዊ መፍትሔዎችን ለማፍራት ያለመ ነው።

በጉባኤው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አለሙ ስሜ፣ የአየር ንብረት ተፅዕኖን ለመቋቋም አረንጓዴ ትራንስፖርትን ማስፋፋት የጋራ ጥረትን የሚጠይቅ በመሆኑ የዓለም አቀፍ ትብብር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የፋይናንስ ድጋፍ ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል።

ሚኒስትሩ አክለውም የአማቂ ጋዝ ልቀትን የሚቀንሱ ቴክኖሎጂዎችን ማስፋፋት፣ የታዳሽ ኃይል አጠቃቀምንና ዘላቂ የትራንስፖርት ሥርዓትን ማጠናከር እንዲሁም ከካርቦን ነፃ የኃይልና የትራንስፖርት አማራጮች ላይ የጋራ ኢንቨስትመንት ማድረግ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በተለይም ለአረንጓዴ ትራንስፖርት ሽግግር የሚያስፈልጉ የፋይናንስና የቴክኖሎጂ አቅሞችን ማሳደግ፣ የእውቀትና የተሞክሮ ልውውጥን ማጠናከር እንዲሁም የጋራ የኢንቨስትመንት ዕድሎችን ማስፋፋት የጋራ ተግባር ሊሆን እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የኖርዲክ–አፍሪካ ትብብር ከአካባቢ ጥበቃና ከአየር ንብረት ለውጥ ባሻገር በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በዲጂታላይዜሽንና በቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፎች ላይም ያተኮረ መሆኑ በመድረኩ ተገልጿል።

በዚህ መሠረት የግል ዘርፉን በማጠናከር የጋራ ኢንቨስትመንትን ማስፋፋት፣ የዲጂታል ቴክኖሎጂና የፈጠራ ሥራዎችን ማበረታታት እንዲሁም የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም አቅምን መገንባት በትብብሩ ውስጥ ትኩረት የሚሰጣቸው ዋና ጉዳዮች መሆናቸው ተጠቁሟል።

በጉባኤው በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ሽግግርና በአረንጓዴ ትራንስፖርት ዙሪያ የፓናል ውይይቶችም ተካሂደዋል።

ኢትዮጵያም የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ለማበረታታት የወሰደቻቸውን የፖሊሲ፣ የስትራቴጂና የስታንዳርድ እርምጃዎች እንዲሁም በኤሌክትሪክ ትራንስፖርት ሽግግር ያላትን ተሞክሮ ለተሳታፊዎች አጋርታለች።

የኖርዲክ–አፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤው ዴንማርክ፣ ፊንላንድ፣ ስዊድን፣ ኖርዌይና አይስላንድን ጨምሮ የኖርዲክ ሀገራትና የአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በአየር ንብረት፣ በአረንጓዴ ኢኮኖሚና በዘላቂ ትራንስፖርት ዘርፎች የጋራ መፍትሔዎችን ለማምጣት የሚያግዝ መድረክ መሆኑ ተገልጿል።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር መረጃዎችን ለማግኘት👇👇👇

በድረ ገጽ፡

www.motl.gov.et

በፌስቡክ
https://www.facebook.com/EthiopianTransport?mibextid=ZbWKwL

በቴሌግራም:
https://t.me/ministryoftransportethiopia

በዩቲዩብ

https://youtube.com/

በትዊተር

https://x.com/MoTLogestics

በቲክቶክ

https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZS-93fuvA1twuuy

የBRICS የኒው ዴልሂ መግለጫ የኢትዮጵያን የICAO ካውንስል ዕጩነት ደገፈ“We welcome the candidatures of Ethiopia, endorsed by the African Union ...
14/09/2026

የBRICS የኒው ዴልሂ መግለጫ የኢትዮጵያን የICAO ካውንስል ዕጩነት ደገፈ

“We welcome the candidatures of Ethiopia, endorsed by the African Union as the sole African candidate…”

የBRICS የኒው ዴልሂ መግለጫ፣ ሴፕቴምበር 12፣ 2026

በ18ኛው የBRICS የመሪዎች ጉባኤ የፀደቀው የኒው ዴልሂ መግለጫ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ኅብረት የተደገፈች የአፍሪካ ብቸኛ ዕጩ በመሆን በመጪው የICAO 43ኛ ልዩ ጠቅላላ ጉባኤ ለሚደረገው የካውንስል ተጨማሪ መቀመጫ ምርጫ ያቀረበችውን ዕጩነት በግልጽ ደግፏል።
ይህ ድጋፍ የመጣው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባኤው ኢትዮጵያ በBRICS መድረክ የበለጠ ትብብር፣ የአፍሪካ ተሳትፎ እና የአባል ሀገራትን ካፒታል፣ ቴክኖሎጂና ገበያ በማስተሳሰር የጋራ እሴት እንዲፈጠር ያቀረቡትን ጥሪ ተከትሎ ነው።

✈️ ይህ ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ አቪዬሽን ምን ማለት ነው?

የBRICS ድጋፍ የኢትዮጵያ የአቪዬሽን ዲፕሎማሲ ከአፍሪካ አህጉር ባሻገር በGlobal South የትብብር መድረኮች እውቅና እያገኘ መሆኑን ያሳያል።

የአፍሪካን ድምፅ ማጠናከር
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት (ICAO) ካውንስል ውስጥ የምትወክለው የራሷን ጥቅም ብቻ ሳይሆን የአፍሪካን የአቪዬሽን ደህንነት፣ ትስስር፣ ልማት እና ክልላዊ ትብብር አጀንዳ ነው። በተጨማሪም የዓለም አቀፍ ሲቪል አቪዬሽንን እድገት የመምራት፣ የአየር ትራንስፖርትን ደህንነት፣ ሴኩሪቲ፣ ቅልጥፍና እና ዘላቂ ዕድገት የመደገፍ፣ እንዲሁም የICAO ፖሊሲዎችና ደረጃዎች አፈጻጸምን የመቆጣጠር ኃላፊነት የሚሰጥ ነው።

የኢትዮጵያን የትስስር ሚና ማጠናከር

ኢትዮጵያ አፍሪካን ከዓለም ጋር በአየር ትራንስፖርት ለማገናኘት ልዩ ስትራቴጂካዊ ሚና አላት። ይህም አቪዬሽንን ከመጓጓዣ ዘርፍ ባሻገር የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲና የአፍሪካ ትስስር መሣሪያ ያደርገዋል።
ለኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን (ECAA) የበለጠ ኃላፊነት
ይህ ዓለም አቀፍ ድጋፍ በተመሳሳይ ጊዜ የECAAን የቁጥጥር፣ የአቪዬሽን ደህንነት፣ የICAO ስታንዳረዶቸንን እና ተመራጭነት ያላቸውን አሰራሮች (SARPs) ተግባራዊነትና ተቋማዊ አቅም በተጨባጭ የማጠናከር ኃላፊነትን ያሳድጋል።

🌍 የዛሬው ድጋፍ፣ የነገ ኃላፊነት

የBRICS ድጋፍ ጠቃሚ የዲፕሎማሲ ስኬት ቢሆንም፣ የICAO ካውንስል መቀመጫ ገና የተረጋገጠ የምርጫ ውጤት አይደለም። የመጨረሻው ውጤት በመጪው ህዳር 2019 የICAO 43ኛ ልዩ ጠቅላላ ጉባኤ በሚካሄደው ምርጫ ይወሰናል። (Prime Minister of India⁠)

ኢትዮጵያ የአፍሪካን ድምፅ በብቃት፣ በታማኝነት እና በሙያዊ አመራር ለማጠናከር ዝግጁ ናት።

ኢትዮጵያ - የአፍሪካ ድምፅ፣ የዓለም አቪዬሽን አገናኝ!

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን

ከናይሮቢ እስከ አዲስ አበባ፡ የኤሌክትሪክ ትራንስፖርት በተግባር 🚌⚡️🇪🇹🇰🇪የምሥራቅ አፍሪካ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ እንቅስቃሴ የወደፊት ራዕይ ብቻ ሳይሆን በተግባር እየተመዘገበ ያለ እውነታ...
11/09/2026

ከናይሮቢ እስከ አዲስ አበባ፡ የኤሌክትሪክ ትራንስፖርት በተግባር 🚌⚡️🇪🇹🇰🇪

የምሥራቅ አፍሪካ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ እንቅስቃሴ የወደፊት ራዕይ ብቻ ሳይሆን በተግባር እየተመዘገበ ያለ እውነታ ሆኗል።

ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሪክ የሚሠሩት የግሪን አዲስ አውቶቡሶች ከአዲስ አበባ ሞያሌ ተጉዘው በNordic-Africa EV Summit ለመሳተፍ ከኬንያ ናይሮቢ ተነስተው ሞያሌ የደረሱ ተሳታፊዎችን ወደ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ለማድረስ እና በተመሳሳይም ጨርሰው ሲመለሱ ከአዲስ አበባ ሞያሌ ለመመለስ ታሪካዊ ድንበር ተሻጋሪ ጉዞ ላይ ይገኛሉ።

አውቶቡሶቹ ከአዲስ አበባ 560 ኪሎ ሜትር ርቀት በምትገኘው ያቤሎ ከተማ በኤሌክትሪክ ቻርጅ ሀይል እየሞሉ ሲሆን፣ ይህም በምሥራቅ አፍሪካ የኤሌክትሪክ ቻርጅንግ መሠረተ ልማት ፈጣን እድገት የተመዘገበ ሌላው አበረታች ምልክት ነው።

ይህ ድንበር ተሻጋሪ ጉዞ በኢትዮጵያና በኬንያ መካከል የአረንጓዴና ዘላቂ የትራንስፖርት ትስስርን ከማጠናከር ባሻገር፣ የክልላዊ ውህደትን እና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ አጠቃቀምን ለማስፋፋት ያለውን አቅም ያሳያል።

በተጨማሪም ይህ ተግባራዊ ልምድ ኢትዮጵያ ከመስከረም 4 እስከ 6 ቀን 2026 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ለምታስተናግደው የNordic-Africa EV Summit ዝግጅት ጠንካራ መሠረት ይፈጥራል።

ይህ ታሪካዊ ሥራ ስኬታማና እውን መሆን የቻለው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት (EEU)፣ BKG፣ AATB፣ በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት፣ በፌዴራልና በክልል ፖሊስ ተቋማት እንዲሁም በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አመራር ባለሙያዎች በተደረገ የተቀናጀ ትብብር ነው።

ኢትዮጵያና ኬንያን በአረንጓዴ፣ ዘላቂ እና ንፁህ የትራንስፖርት መስመር የሚያገናኘው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ጉዞ በተግባር መጀመሩን አሳይቷል።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር መረጃዎችን ለማግኘት👇👇👇

በድረ ገጽ፡

www.motl.gov.et

በፌስቡክ
https://www.facebook.com/EthiopianTransport?mibextid=ZbWKwL

በቴሌግራም:
https://t.me/ministryoftransportethiopia

በዩቲዩብ

https://youtube.com/

በትዊተር

https://x.com/MoTLogestics

በቲክቶክ

https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZS-93fuvA1twuuy

11/09/2026
10/09/2026

#ፋና #ኢትዮጵያ

10/09/2026
ክቡር ሚኒስትሩ ለሚኒስቴር መስሪያቤቱ  ሠራተኞች አመት በዓልን ምክንያት ማዕድ አጋርተዋል።አዲስ አበባ፣ ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም (ትሎሚ) – የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ...
09/09/2026

ክቡር ሚኒስትሩ ለሚኒስቴር መስሪያቤቱ ሠራተኞች አመት በዓልን ምክንያት ማዕድ አጋርተዋል።

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም (ትሎሚ) – የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አለሙ ስሜ መጪውን የ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት በዓል አስመልክተው ለሚኒስቴሩ ሠራተኞች የበዓል ማዕድ አጋርተዋል።

የበዓል ማዕዱ የሚኒስቴሩን ሠራተኞች በአንድነት ለማሰባሰብና በጋራ የበዓሉን ደስታ ለመጋራት ያለመ ሲሆን፣ በዚሁ ወቅት ሚኒስትሩ ለሠራተኞቹ የአዲስ ዓመት መልዕክት አስተላልፈዋል።

ክቡር ሚኒስትሩ አዲሱ ዓመት የሰላምና የደስታ፣ ሠራተኞች ያቀዷቸውን ዕቅዶች የሚያሳኩበትና የሀገራችንን ብልጽግና እውን ሆኖ የሚመለከቱበት ዓመት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

በተጨማሪም ሠራተኞች በአዲሱ ዓመት በተሰማሩባቸው የሥራ መስኮች በትጋትና በተባበረ መንፈስ በመሥራት ለሀገራዊ ልማትና ብልጽግና የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር መረጃዎችን ለማግኘት👇👇👇

በድረ ገጽ፡

www.motl.gov.et

በፌስቡክ
https://www.facebook.com/EthiopianTransport?mibextid=ZbWKwL

በቴሌግራም:
https://t.me/ministryoftransportethiopia

በዩቲዩብ

https://youtube.com/

በትዊተር

https://x.com/MoTLogestics

በቲክቶክ

https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZS-93fuvA1twuuy

ብዝሃ ማንነትን በእኩልነት ማስተናገድ ለጠንካራና ለበለፀገች ኢትዮጵያ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸየትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አመራሮችና ሠራተኞች የጳጉሜን 4 “የህብር ቀን”ን አከበሩአዲስ አ...
09/09/2026

ብዝሃ ማንነትን በእኩልነት ማስተናገድ ለጠንካራና ለበለፀገች ኢትዮጵያ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አመራሮችና ሠራተኞች የጳጉሜን 4 “የህብር ቀን”ን አከበሩ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4/2018 ዓ.ም. (ትሎሚ) – የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አመራሮችና ሠራተኞች “ለኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ሃሳብ የጳጉሜን 4 “የህብር ቀን”ን በድምቀት አክብረዋል።

መርሃ ግብሩ በሠራተኞች መካከል ያለውን አንድነትና መተሳሰብ በማጠናከር፣ የህብረ ብሔራዊነትን እሴት በሚያጎለብት መልኩ ተካሂዷል።

በመርሃ ግብሩ የ“የህብር ቀን”ን ዓላማና አስፈላጊነት የሚመለከት የውይይት መነሻ ሰነድ በሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ተወካይ አቶ ሰይፉ ክንፉ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።

በውይይቱ የብዝሃነት ምንነት፣ የህብር ገመዶችና አፈጣጠር፣ የህብረ ብሔራዊነት አያያዝና ውጤቶች፣ ብዝሃነት በኢትዮጵያ ያለው ገጽታ እንዲሁም ብዝሃነትን በመደመር መርህ የማስተናገድ አቅጣጫዎች ላይ ማብራሪያ ተሰጥቷል።

በተጨማሪም ብዝሃነትን በአግባቡ ከማስተናገድ አንፃር የተለያዩ አገራት ተሞክሮ ቀርቧል።

ብዝሃነትን አለመቀበልና በእኩልነት አለማስተናገድ ለማንነት ግጭቶችና ለማህበራዊ መከፋፈል መንስኤ መሆኑም በተሞክሮዎቹ ተመላክቷል።

ኢትዮጵያ የተለያዩ ማንነቶች፣ ባህሎች፣ ቋንቋዎችና ሃይማኖቶች የሚገኙባት ብዝሃነት የተሞላባት አገር መሆኗን በመጠቆም፣ በቀደሙት ሥርዓቶች ብዝሃነትን በእኩልነት አለማስተናገድ ለተለያዩ ግጭቶች መፈጠር አስተዋፅኦ ማድረጉ ተነስቷል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች ጠንካራና የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የተለያዩ ማንነቶችን መቀበል፣ ማክበርና በእኩልነት ማስተናገድ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም ብዝሃ ማንነትንና ብሔራዊነትን በተመጣጣኝ ሁኔታ በማስተናገድ፣ የጋራ እሴቶችንና የጋራ ትርክትን መገንባት ለሀገራዊ አንድነትና ለዘላቂ ልማት ወሳኝ መሆኑን ተሳታፊዎቹ አመልክተዋል።

ከማንነት ግጭት ተላቀው ወደ ብልፅግና የተሸጋገሩ አገራት ብዝሃነትን በመቀበልና በእኩልነት በማስተናገድ ላይ የተመሠረቱ ልምዶችን መከተላቸው ተጠቁሟል። በዚህም ኢትዮጵያ በብዝሃ ማንነትና በብሔራዊነት መካከል ሚዛን በመጠበቅ፣ የጋራ ትርክትን መገንባት ከቻለች ወደ ሰላም፣ አንድነትና ብልፅግና ለመሻገር የሚያግዛት መሆኑ ተገልጿል።

በተጨማሪም ባለፉት የለውጥ ዓመታት መንግሥት በተለይ በጳጉሜን ቀናት የጋራ ትርክትን፣ አንድነትንና የብዝሃነት አያያዝን የሚያጎለብቱ የተለያዩ መሪ ሃሳቦችን በመቅረፅ የሚያከናውነው ሥራ በትኩረትና በቀጣይነት መጠናከር እንዳለበት ተሳታፊዎቹ አስገንዝበዋል።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር መረጃዎችን ለማግኘት👇👇👇

በድረ ገጽ፡

www.motl.gov.et

በፌስቡክ
https://www.facebook.com/EthiopianTransport?mibextid=ZbWKwL

በቴሌግራም:
https://t.me/ministryoftransportethiopia

በዩቲዩብ

https://youtube.com/

በትዊተር

https://x.com/MoTLogestics

በቲክቶክ

https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZS-93fuvA1twuuy

Address

Addis Ababa
1238

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ministry of Transport and Logistics - Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ministry of Transport and Logistics - Ethiopia:

Shortcuts

Share