17/07/2026
እንኳን በሰላም ተገላገልሽ!
"ምንም እንኳን የመውለጃዬ ቀን ቢቃረብም “ሀገሬ ጠርታኝ አልቀርም” በማለት ከጋምቤላ ክልል ወደ አዲስ አበባ ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የመጣችው ወጣት ክርኑዶ ኡጁሉ፣ በጉባኤው ሂደት ላይ እያለች በዘውዲቱ ሆስፒታል ወንድ ልጅ በሰላም ተገላግላለች።
የሀገር ፍቅር እና የእኔነት ስሜት ሲኖር የማይቻል ነገር አለመኖሩን ማሳያ የሆነችውን ይህችን ጀግና እናት፤ ከጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ከክብርት ወ/ሮ አለሚቱ ኡመድ ጋር በመሆን ባረፈችበት ቤት በመገኘት እንኳን ደስ አለሽ ብለናታል።
ይህችው ጀግና እናት፤ የተለመደውን ስም የማውጣት ባህል በመተው፣ የልጇን ስም ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ እንዲያወጣላት በጠየቀችው መሰረት የህፃኑን ስም "ምክክር" ብላዋለች።
ዛሬም በሄድንበት ወቅት፣ ወጣቷ የመጣችበትን ታላቅ ሀገራዊ ዓላማ ለማሳካት ከጥቂት ቀናት እረፍት በኋላ ወደ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በልበ ሙሉነት እንደምትመለስ አረጋግጣልናለች። እኛም ጉባኤውን አጠናቃ ወደ መጣችበት እስክትመለስ ድረስ ለእሷና ለልጇ የሚያስፈልገውን ድጋፍ እናደርግላታለን።
እህታችን ወንድ ልጇን በሰላም ተገላግላ በደስታ እንደተሞላች ሁሉ፤ ኢትዮጵያ ሀገራችንም ከገጠማት አንዳንድ ችግሮች በምክክር እና በንግግር ተገላግላ፣ ትልቅ እና ወሳኝ የሽግግር ምዕራፍ እንደሚሆንላት ፅኑ እምነታችን ነው።
ህፃን ምክክርም፤ እደግ ተመንደግልን! አንተ እና መሰል የኢትዮጵያ ህፃናት ሁሉ ቦርቃችሁ እና ተደስታችሁ የምታድጉባት፣ እንዲሁም የምትረከባት ሀገር ሰላሟ ሙሉ የሆነች፣ የህዝቦች ፍቅር ያበበበት እና የበለፀገች ኢትዮጵያ እንድትሆን ከልብ እንመኛለን።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን አብዝቶ ይባርክ!
Baga nagaan deesse!
"Yeroon dahumsa koo dhiyaatullee, biyyi koo na waamtee hin hafu” jechuun naannoo Gaambeellaa irraa gara Finfinneetti yaa'ii Marii Biyyoolessaatiif kan dhufte dargaggeettiin Kirnuudoo Ujuluu, adeemsa marii kanarra osoo jirtuu Hospitaala Zawudituutti mucaa dhiiraa nagaan deessee jirti.
Jaalala biyyaa fi miirri kiyya jedhu yoo jiraate wanti hin danda'amne akka hin jirre argarsiistuu kan taate haati gootni kun, Pirezidaantii Naannoo Gaambeellaa Kabajamtuu Aadde Alamituu Umad waliin ta'uun mana isheen boqottee jirtutti argamuun baga gammadde jenneerraan.
Haati gootni kun, aadaa maqaa baasuu barame dhiisuun, maqaa mucaashee Koreen Marii Biyyaalessaa akka baasuuf gaafatte irratti hunda'uun maqaa daa'imichaa "Mikikkir" jettee moggaasteetti.
Har'as yeroo dhaqne, dargaggeettiin kun kaayyoo guddaa biyyaalessaa dhufteef galmaan gahuuf, boqonnaa guyyoota muraasaa booda gara yaa'ii Marii Biyyaalessaatti onnee guutuun akka deebitu nuuf mirkaneessiteetti. Nutis marii kana xumurtee gara iddoo dhufteetti hanga deebitutti