18/03/2023
መግለጫውን በአጭሩ ለመግለጽ ያህል
ኢትዮጵያ ሀገራችን ወደ ታላቅ ምእራፍ በምትሻገርበት ድልድይ ላይ ትገኛለች፡፡
1. ከድልድዩ ወደኋላ ሊመልሷት ይታገላሉ፡፡
2, ሌሎቹ ድልድዩን ሰብረው ገደል ሊከቷት
ይለፋሉ፡፡
3, ታጋይ ልጆቿ ደግሞ በድልድዩ ላይ ብዙ
ሳትቆይ ወደፊት እንድትራመድ ለማድረግ
ይታገላሉ፡፡
ብልጽግና ደግሞ ይህን መርጧል፡፡
👉ድልድይ ያለፈውን መንገድ ያህል ጠንካራ አይሆንም፡፡
👉ገደሉን ለመሻገር ግን የግድ ነው፡፡ ረዥም ጊዜ በድልድዩ ላይ መቆየትም አደጋ አለው፡፡
👉በቶሎ መሻገርና ወደጸናው መሬት መድረስ አስፈላጊ ነው፡፡
👉ያለንበት የሽግግር ጊዜም የሚነግረን ይሄንን ነው፡፡
👉የሽግግሩ ወቅት ዓላማው በዚያው መቆየት ሳይሆን ወደ በለጸገች ኢትዮጵያ መሸጋገሪያ ነው፡፡
👆እየገጠሙን ያሉትም የሽግግር ጊዜ ፈተናዎች ናቸው፡፡
የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ባደረገው ስብሰባ
👉ኢትዮጵያ ካለፈው መንገድ የመጣችበትን፣ ወደ ብልጽግና ለመሻገር በድልድዩ ላይ የቆየችበትን፣ በድልድዩ ላይ በቆየችባቸው ወቅቶች የገጠሟትን ፈተናዎች፤ ከድልድዩ ወደኋላ ለመመለስ የሚታገሏትን ኃይሎች፣ ድልድዩን ተሻግራ ወደ ብልጽግና እንዳትሸጋገር ያጋጠሟትን አምስት ተግዳሮቶች በዝርዝር መርምሯል፡፡
1ኛ, ታሪክ ካሸከመን ዕዳችን ነው።
መፍትሄው፦ ለዕድሉም ለዕዳውም ተገቢውን ዕውቅና መስጠት ነው ብሏል።
2ኛ, ነፃነትን ለማስተዳደር አለመቻል ነው።
መፍትሄው ፦ ነፃነት ከኃላፊነት ጋር ሚዛናዊነቱን ጠብቆ እንዲሄድ ሂሉም ተቋማት የሚጠበቅበትን መስራት ነው።
3ኛ, ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን የሚፈታትኑ ሁኔታዎች እየገነገኑ መምጣታቸው ነው።
መፍትሄው ፦ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ያለፉ ቁስሎችን ከሚቀሰቅሱ ጥላቻ ከሚያነገሱ እና መሰሎችን ከድርጊታቸውና ንግግሮች መቆጠብ አለባቸው።
4ኛ, የኑሮ ውድነት ነው።
መፍትሄው ፦ ምርትን በተገቢ መጠን ማምረትና ወደ ገበያ ማድረስ ችግሮችን ማረም ስራ ዕድል መፍጠር የቤት ስራችን ነው።
5ኛ, ሌብነት ነው።
የሌብነት እንደ መግለጫው መሠረት ዓይነቶች በ4 አከባቢዎች ይከፈላሉ!
1, በመንግስት ውስጥ ያሉ ሌቦች
2, በባለሀብቱ አከባቢ ያሉ ሌቦች
3, በብሔሮ አከባቢ ያሉ ሌቦች
5, በሚዲያ አከባቢ ያሉ ሌቦች ናቸው።
መፍትሄው፦ የጀመርነውን ዘመቻ አጠናክሮ መቀጠል። ከራሳችን ጀምረን እጃችን ንጹህ በማድረግ ትግሉን መምራት ነው።
👉እኛም እንደ አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወጣቶች ሊግ ያሉን ችግሮችን ተረድተን በሙሉ አቅም ለመስራት ቁርጠኛ መሆናችን እናረጋግጣለን።
መጋቢት 8/2015ዓ.ም
አቃቂ ቃሊቲ