15/10/2022
የስልጤ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መመሪያ የ2014 ዓ.ም የተግባር አፈፃፀም መነሻ በማድረግ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የምሳ ፕሮግራምና አቅም ለሌላቸው የህብረተሰብ ክፍል የዱቄት ድጋፍ ማድረጉን ገለፀ፡፡
የመማሪያ ኃላፊ የሆኑት አቶ ሸምሴ ኑሪ እንደገለፁት በ2014 ዓ ም በነበረው ሃገራዊ ነበራዊ ሁኔታ መነሻ በማድረግ በዞኑ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች መደረጉን ገልፀው በተለይ በወራቤ ከተማ አስተዳደር የተጀመረውን የቅዳሜ ገበያ በማስፋፋት ረገድ ጥሩ የሚባሉ ስራዎች ተሰርቷል ብለዋል ፡፡ አያይዘውም የንግድ እንቅስቃሴ ለማዘመን የተለያዩ ስራዎች በመስራት ሁሉም መዋቅራችን ከነ ጉድለቱም ቢሆን የonlione አገልግሎት ማደረስ ተችሏል ብለዋል ፡፡
ይህንን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ በመገምገም በክልል በቢሮ ደረጃ የሶስተኛ ደረጃ እውቅና በተመሳሳይ በዞን ምክር ቤት በኢኮኖሚ ዘርፍ የሁለተኛ ደረጃ እውቅና ማግኘት ተችሏል በመሆኑ ይህ እውቅና የሚያኩራራ ሳይሆን ተጨማሪ የህዝብ አደራን ስለሚጥል በቀጣይ ተጠናክሮ ጉድለትን በማረም መስራት ይጠበቅብናል በማለት አሳስበዋል ፡፡
ይህንን በማስመልከት መምሪያው በዛሬ ዕለት ከአቅመ ደካሞችና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የምሳ ግብዣ ያደረገ ሲሆን ለ16 አቅመ ደካሞች የምሳ ግብዣና በአራት ዱቄት ፋብሪካዎች እስፖንሰር ፈድሉ ፣ ሲሃም ፣ አዳዘርና ሀጂ ወርቄ ዱቄት ፋብሪካዎች የሰጡንን ዱቄት ለየ አንዳንዳቸው 25 ኪ.ግ ዱቄት ስጦታ ማድረግ ተችሏል በማለት የገለፁት ኃ
ኃላፊው ከፕሮግራሙ በማያያዝ ከወረዳና ከተማ አስተዳደር የፅ/ቤት ኃላፊዎች ጋር በመሆን የወራቤ ከተማ አስተዳደር የቅዳሜ ገበያና በመምሪያ ጊቢ ላይ እለማ ያለ የከተማ ግብር /ምግቤን ከጓሮዬ/ከስራ ገበታዬ/ የጉብኝቱ አካል እንደነበረ ገልፀዋል ፡፡
አያይዘውም በፕሮግራሙ በመገኘት የምሳ ግብዣና ድጋፍ የተደረገላቸው አካላት በሰጡት አስተያየት ያለነበትን የኑሮ ደረጃ በመረዳት በክብርና በእንክብካቤ የምሳና የዱቄት ድጋፍ ስላደረጋቹልን አላህ ኸይር ጀዛ ይክፈላችሁ በማለት ዱኣ አድርጓል ፡፡
በመጨረሻምፕሮግራም እንዲሳካ ላደረጉ አካላት በሙሉ በመምሪያው ስም ከልብ አመስግነዋል ፡፡
# #መረጃውም ከስልጤ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ