07/05/2026
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሠራተኞች የሥራ ኃላፊዎች የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖን ጎበኙ
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሠራተኞች የሥራ ኃላፊዎች “ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት” በሚል መሪ ሐሳብ እየተካሄደ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ጎብኝተዋል።
በኤክስፖው ላይ ለአካል ጉዳተኞች የአካል ድጋፍ ለማድረግ የሚያግዙ በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ዊልቸርሮች፣ ለህፃናት ቅድመ ልጅነት ዕድገትን የሚያግዙ አገር በቀል የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦቶችን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ አምራቾች ምርቶቻቸውን አቅርበዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሚያዝያ 25 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆየውን አራተኛውን የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ኤክስፖ መርቀው መክፈታቸው ይታወሳል።