የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን/Federal Tax Appeal Commission

የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን/Federal Tax Appeal Commission የታክስ ከፋዩን ማህበረሰብ ከግብር ሰብሳቢዉ ባለስልጣን በታክስ አከፋፈል የሚቀርቡ ቅሬታዎችን በመመርመር እና በማከራከር ነፃ፣ ገለልተኛና ፍትሐዊ ውሳኔ ይሰጣል

11/08/2026

በ2018 ዓ.ም የተከናወኑ አፎይታን የሰጡ የኮሚሽኑ ውሳኔዎች እና የሥራ አፈጻጸም

የግብር ከፋዩን እንግልት የቀነሱ፣ ፍትሐዊነትን ያረጋገጡ እና አፎይታን የሰጡ የኮሚሽኑ የ2018 ዓ.ም ውሳኔዎች እንዲሁም አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ዝግጅት በይፋዊ የዩቲዩብ ቻናላችን ተለቋል።

የቪዲዮውን ሙሉ ይዘት ለመከታተል ሊንኩን ይጫኑ https://www.youtube.com/watch?v=mlogxSimcR8&t=921s

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን
ነፃና ገለልተኛነት ለፍትሐዊ የታክስ ሥርዓት !

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የማህበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
Facebook
https://www.facebook.com/ftacofficial
Telegram
https://t.me/ftac_official
(x) Twitter
https://twitter.com/federal_appeal
YouTube channel
https://www.youtube.com/channel/UCzpuuuXybdHh7BlgWXMVI

የምንለቃቸው መረጃዎች ቀድመው እንዲደርስዎ Subscribe, Like, Comment እና Share ያድርጉ!

የኮሚሽኑ መደበኛ ችሎት ለ1 ወር ከ24 ቀን ዝግ ሆኖ ይቆያል፡፡********************ፌታይኮነሀሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ምየፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ነፃና ገለልተኛ በሆነ መልኩ የ...
07/08/2026

የኮሚሽኑ መደበኛ ችሎት ለ1 ወር ከ24 ቀን ዝግ ሆኖ ይቆያል፡፡
********************
ፌታይኮ
ነሀሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም
የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ነፃና ገለልተኛ በሆነ መልኩ የይግባኝ አቤቱታዎችን ተቀብሎ በማከራከር ፍትሐዊ ውሳኔ በመስጠት ላይ የሚገኝ ተቋም መሆኑ ይታወቃል። ኮሚሽኑ ከነሐሴ 4 ቀን 2018 ዓ.ም. እስከ መስከረም 24 ቀን 2019 ዓ.ም. ድረስ መደበኛ ችሎት ዝግ ሆኖ እንደሚቆይ የኮሚሽኑ ፕሬዚዳንት ክቡር ሙሉጌታ አያሌው ገልፀዋል፡፡

መደበኛ ችሎቱ በሚዘጋበት በእነዚህ ቀናት ውስጥ ወደ ተቋሙ የሚመጡ ባለጉዳዮች ከችሎት ውጭ ያሉትን አገልግሎቶች ሳያስተጓጉሉ ማግኘት የሚችሉ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ አረጋግጠዋል። ከእነዚህም አገልግሎቶች መካከል የይግባኝ አቤቱታ ማቅረብ፣ የውሳኔ ግልባጭ መውሰድ፣ የመልስ መልስ ማቅረብ፣ አስተያየትና ጥቆማ ማቅረብ፣ እንዲሁም የፍርድ ቤቶች ትዕዛዝና የተለያዩ አቤቱታዎችን ማቅረብ እንደሚገኙበት ተናግረዋል።

በተጨማሪም የመደበኛ ችሎት ሥራዎች ቢቋረጡም የአፈፃፀም ችሎትን በተመለከተ ቀደም ሲል በነሐሴ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. እና በነሐሴ 12 ቀን 2018 ዓ.ም. በተያዘላቸው የቀጠሮ ቀን መሠረት አስተናግዶ ጉዳያቸውን የሚያይ ይሆናል ብለዋል።

በመጨረሻም የኮሚሽኑ መደበኛ ችሎት ከመስከረም 25 ቀን 2019 ዓ.ም. ጀምሮ አገልግሎቱን አጠናክሮ ሙሉ በሙሉ ወደ መደበኛ ሥራው እንደሚመለስ ተገልጿል፡፡

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን
ነፃና ገለልተኛነት ለፍትሐዊ የታክስ ሥርዓት !
የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የማህበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
Facebook
https://www.facebook.com/ftacofficial
Telegram
https://t.me/ftac_official
(x) Twitter
https://twitter.com/federal_appeal
YouTube channel
https://www.youtube.com/channel/UCzpuuuXybdHh7BlgWXMVI

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ከሰላም ሚኒስቴር፣ ከፍትህ ሚኒስቴርና ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን የደም ልገሳ አከናወነ፡፡********************ፌታይኮሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ምየ...
06/08/2026

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ከሰላም ሚኒስቴር፣ ከፍትህ ሚኒስቴርና ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን የደም ልገሳ አከናወነ፡፡
********************
ፌታይኮ
ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም
የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ከተሰጠው ተቋማዊ ተግባርና ኃላፊነት ባሻገር ማህበራዊ ግዴታውን በመወጣት ረገድ አርአያነታቸውን የሚያስመሰክሩ የበጎ አድራጎት ስራዎች ላይ በንቃት በመሳተፍ ላይ ይገኛል።

ኮሚሽኑ ከሰላም ሚኒስቴር፣ ከፍትህ ሚኒስቴርና ከተጠሪ ተቋማት ጋር በጋራ በመተባበር በመከላከያ ሚኒስቴር ጦር-ሃይሎች ሆስፒታል በመገኘት የደም ልገሳ መርሃ ግብር አካሂዷል። ይህ የደም ልገሳ መርሃ ግብር ኮሚሽኑ በክረምት ወቅት ለማከናወን ካቀዳቸው የበጎ አድራጎት ተግባራት መካከል አንዱ ነው።

በዕለቱ የኮሚሽኑ አመራሮችና ሰራተኞች በቦታው በመገኘት "ደም በመለገስ ሕይወትን እናድን" ‹‹ደማችን ለሀገር መከላከያ ሠራዊታችን›› የሚለውን መሪ ቃል ጥሪ በተግባር ምላሽ ሰጥተዋል።ወገንን ለመርዳትና የሰዎችን ሕይወት ለመታደግ በሚደረገው በዚህ ቅዱስ ተግባር ላይ በመሳተፍ የተለገሰው ደም አስቸኳይ የህክምና እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው የሕይወት አለኝታ እንደሚሆን ታምኖበታል።

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ወደፊትም የታክስ ፍትሕን የማረጋገጥ ዋና ተግባሩን እየተወጣ መሰል ህዝባዊና ማህበራዊ ኃላፊነቶችን በስፋት በማከናወን አዎንታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን
ነፃና ገለልተኛነት ለፍትሐዊ የታክስ ሥርዓት !
የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የማህበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
Facebook
https://www.facebook.com/ftacofficial
Telegram
https://t.me/ftac_official
(x) Twitter
https://twitter.com/federal_appeal
YouTube channel
https://www.youtube.com/channel/UCzpuuuXybdHh7BlgWXMVI

«ዛሬ የምንተክለው፤ ነገ የምንመገበውን፣ የምናርፍበትን ጥላና የነገውን የተፈጥሮ አደጋ መከላከያ ከለላችንን ነው!››ክቡር ሙሉጌታ አያሌው*******************ፌታይኮሐምሌ 27 ቀን 2...
03/08/2026

«ዛሬ የምንተክለው፤ ነገ የምንመገበውን፣ የምናርፍበትን ጥላና የነገውን የተፈጥሮ አደጋ መከላከያ ከለላችንን ነው!››
ክቡር ሙሉጌታ አያሌው
*******************
ፌታይኮ
ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም
የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ዳኞች አመራሮችና ሰራተኞች በአንድ ጀንበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ላይ ተሳተፉ፡፡

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ዳኞች፣ አመራሮች እና ሰራተኞች በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ በተካሄደው በአንድ ጀንበር 800 ሚሊዮን ችግኞች የመትከል ሀገራዊ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ላይ ንቁ ተሳትፎ አደረጉ።

ለአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ከተለዩት 176 የመትከያ ቦታዎች መካከል የኮሚሽኑ ሰራተኞች በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 (ቦሌ ቪ.አይ.ፒ ፓርክ) በመገኘት «ተስፋን እንትከል» በሚል መሪ ቃል ችግኞችን ተክለዋል።

በስፍራው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኮሚሽኑ ፕሬዚዳንት ክቡር ሙሉጌታ አያሌው እንደገለጹት፤ተስፋችንን በምድር ላይ እያነጽን፣ የበለጸገችና ለምለም ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ በጋራ ራዕይ አልመን፣ በሀሳብ ተጣጥመንና በተግባር ተጋግዘን መስራት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።

ፕሬዚዳንቱ አክለውም ዛሬ የምንተክለው፤ ነገ የምንመገበውን፣ የምናርፍበትን ጥላና የነገውን የተፈጥሮ አደጋ መከላከያ ከለላችንን ነው በማለት ገልጸው፣ ዛሬ በእጆቻችን አፈር በመንካት የሚተከሉት ችግኞች የነገውን የአየር መበከል፣ የጤና ጠንቅና ድንገተኛ የጎርፍ አደጋን ለመከላከል የሚያስችሉ መሆናቸውን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን
ነፃና ገለልተኛነት ለፍትሐዊ የታክስ ሥርዓት !

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የማህበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
Facebook
https://www.facebook.com/ftacofficial
Telegram
https://t.me/ftac_official
(x) Twitter
https://twitter.com/federal_appeal
YouTube channel
https://www.youtube.com/channel/UCzpuuuXybdHh7BlgWXMVI

የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ባለው ክፍት የሥራ ቦታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡መስፈርቱን የምታሟሉ በኦንላይን አመልክቱ https://forms....
01/08/2026

የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ባለው ክፍት የሥራ ቦታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
መስፈርቱን የምታሟሉ በኦንላይን አመልክቱ https://forms.gle/mXg8SxMxbVCBN41X8

የአረንጓዴው ዘመቻ ሀገራዊ ጥሪ********************በአንድ ልብ ለጸናች ኢትዮጵያ 800 ሚሊዮን ችግኖች በአንድ ጀምበርከእናት ሀገራችን ኢትዮጵያ ከአራቱም ማዕዘናት የተውጣጣን ውድ ...
29/07/2026

የአረንጓዴው ዘመቻ ሀገራዊ ጥሪ
********************
በአንድ ልብ ለጸናች ኢትዮጵያ 800 ሚሊዮን ችግኖች በአንድ ጀምበር

ከእናት ሀገራችን ኢትዮጵያ ከአራቱም ማዕዘናት የተውጣጣን ውድ ልጆቿ ጠንካራ አንድነታችንንና ለነገዋ ሀገራችን ያለንን የጋራ ኃላፊነት በሥራ ለመግለፅ በታላቁ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ሥር በአንድነት ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም እንነሳለን

በዚህ ታሪካዊ ዘመቻ በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ለትውልድ የሚሻገር አረንጓዴ ታሪክና የጸናች ሀገር መሠረት እንጥላለን።

እርሶም የዚህ ድንቅና ታሪካዊ ሀገራዊ ንቅናቄ ባለቤትና አካል ይሁኑ

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን
ነፃና ገለልተኛነት ለፍትሐዊ የታክስ ሥርዓት !

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የማህበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስ ቡክ፡- https://www.facebook.com/ftacofficial
ቴሌግራም፡- https://t.me/ftac_official
ትዊተር፡- https://twitter.com/federal_appeal
ዩ ቱብ፡- https://www.youtube.com/channel/UCzpuuuXybdHh7BlgWXMVIGw

27/07/2026

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የአፈፃፀም ችሎት መጀመሩን ያውቃሉ ?
*******************
ፌታይኮ
የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የተጣለበትን አገራዊ አደራ እና ህዝባዊ ኃላፊነት ይበልጥ ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመወጣት ግልፅነትና ተጠያቂነት ያለው ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ አዳዲስ አሰራሮችን በመዘርጋት ላይ ይገኛል።

በዚሁ መሰረት ኮሚሽኑ የግብር ከፋዮችን እና የህዝብን እንግልት ለመቀነስ እንዲሁም ጉዳዮች በወቅቱና በቅልጥፍና ውሳኔ እንዲያገኙ ለማድረግ ሲባል ከዋናው ችሎት በተጨማሪ የአፈጻጸም ችሎት በመሰየም በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡

በመሆኑም ሰኞ፣ ረቡዕ እና አርብ ጠዋት እና ከሰዓት መደበኛ ችሎት የሚሰየም ሲሆን የአፈፃፀም ችሎት በየሁለት ሳምንቱ ማክሰኞ ጠዋት የሚቻል መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን፡፡

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን
ነፃና ገለልተኛነት ለፍትሐዊ የታክስ ሥርዓት !

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የማህበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስ ቡክ፡- https://www.facebook.com/ftacofficial
ቴሌግራም፡- https://t.me/ftac_official
ትዊተር፡- https://twitter.com/federal_appeal
ዩ ቱብ፡- https://www.youtube.com/channel/UCzpuuuXybdHh7BlgWXMVIGw

22/07/2026

የታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ከመቼ እስከ መቼ

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን በ2018 በጀት ዓመት ከ9.8 ቢሊዮን ብር በላይ በያዙ መዛግብት ላይ ውሳኔ አሳረፈ፡፡********************ፌታይኮ ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም አዲ...
21/07/2026

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን በ2018 በጀት ዓመት ከ9.8 ቢሊዮን ብር በላይ በያዙ መዛግብት ላይ ውሳኔ አሳረፈ፡፡
********************
ፌታይኮ
ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ
የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የኮሚሽኑ ፕሬዚዳንት፣ ዳኞች፣ የማኔጅመንት አባላት፣ መላው ሠራተኞች እንዲሁም የገቢዎች ሚኒስቴርና የጉምሩክ ኮሚሽን የሥራ ክፍል አመራሮች በተገኙበት የ2018 በጀት ዓመት የይግባኝ አቤቱታዎች፣ የውሳኔ አሰጣጥ ፍጥነትና ጥራት ዝርዝር የአፈጻጸም ሪፖርት ገመገመ።

በበጀት ዓመቱ ለውሳኔ የቀረቡት አጠቃላይ መዛግብት 1,224 ሲሆኑ የያዙት የገንዘብ መጠን 17,676,952,272.95 ብር ሲሆን ከእነዚህም መካከል ከአምናው የዞሩ 469 መዛግብት የያዙት የገንዘብ መጠን 5,229,097,472.14 ብር፣ አዲስ የተከፈቱ 755 መዛግብት የያዙት የገንዘብ መጠን 12,447,854,800.81 ብር ሲሆኑ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የመዛግብት ብዛት በ177 ያነሰ ቢሆንም በገንዘብ መጠን የ5,839,641,152.06 ብር ብልጫ አሳይቷል።

ከቀረቡት 1,224 መዛግብት ውስጥ 960 የሚሆኑትን ክርክር በማድረግ በ958 መዛግብት የያዙት የገንዘብ መጠን 9,864,684,674.39 ብር ላይ ውሳኔ አሳርፏል። በዚህም የውሳኔ አሰጣጥ አፈጻጸም 99.79% ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ ይህ አፈጻጸም ከታቀደው ግብ በ0.21% ዝቅ ያለ ቢሆንም ከባለፈው በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ0.33%፣ የ26 መዛግብት እና የ 3,056,471,025.64 ብር ብልጫ አሳይቷል። ቀሪዎቹ 266 መዛግብት መካከል 21 ለመልስ፣ 3 ለብይን ፣ 240 ለቃል ክርክር እና 2 ለውሳኔ ለቀጣይ የተቀጠሩ ናቸው።

እንደ ሕጉ አሰራር ማመልከቻ በደረሰ 120 ቀናት ውስጥ ውሳኔ የሚሰጥ ቢሆንም ውስብስብ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ በፕሬዝደንቱ ፈቃድ እስከ 60 ቀናት ሊራዘም ይችላል። በዚህ መሠረት ውሳኔ ካገኙት 958 መዛግብት ውስጥ 881 መዛግብት (91.96%) በሕጋዊ ገደብ ማለትም በ120 ቀናት እና ከዚያ ባነሰ ጊዜ ውስጥ ውሳኔ አግኝተዋል። ከእነዚህም ውስጥ 140 መዛግብት (15%) ከ120 ቀን ባነሰ ጊዜ፣ 741 መዛግብት (77%) ደግሞ በ120 ቀናት ውስጥ የተወሰኑ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ 77 መዛግብት (8%) ከ120 ቀናት በላይ ጊዜ የወሰዱ ናቸው።

ውሳኔዎች ከ120 ቀናት በላይ የወሰዱበት ዋና ዋና ምክንያቶች ከሦስተኛ ወገን የሚፈለጉ ማስረጃዎች በወቅቱ አለመቅረብ፣ ከመዝገብ ውስብስብነት የተነሳ ለኮሚሽኑ ፕሬዝደንት ቀርበው የጊዜ ማራዘሚያ በመፈቀዱ እና በተከራካሪ ወገኖች ቀጠሮዎች በተደጋጋሚ በመቀየራቸው ምክንያት መሆኑ ተገምግሟል። በአጠቃላይ የሕግ ተገዢነት ምጣኔ 92% መድረሱ ተረጋገጧል።

ውሳኔ ከተሰጠባቸው መካከል 757 መዛግብት ላይ ለከ/ፍ/ቤት ይግባኝ የተጠየቀ ሲሆን 37 (4.88%) የሚሆኑት በነጥብ ተመልሰዋል። በዚህም መሠረት የጥራት ምጣኔው 95.12% ሆኗል።

ለድጋሚ ምርመራ ከተመለሱት 37 መዛግብት ውስጥ 14 መዛግብት ውሳኔ የሚያስለውጥ አዲስ መረጃ ባለመገኘቱ ሲፀኑ 4 መዛግብት የቀረቡበት አግባብ ታይቶ ሲሻሻል 11 መዛግብት ደግሞ ተሽረዋል (4 በከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ 7 በኮሚሽኑ)። ቀሪዎቹ 8 መዛግብት በአሁኑ ወቅት በመታየት ላይ ይገኛሉ። በዚህ ሂደት የውሳኔዎች የጥራት ምጣኔ ወደ 98.01% ከፍ ለማለት ችሏል።

በበጀት ዓመቱ 342 የአፈጻጸም መዛግብት የቀረቡ ሲሆን 144 መዛግብት ዕግድ፣ 94 መዛግብት ግራ ቀኝ (ሁለቱም ወገኖች) ባለመቅረባቸው ሲዘጉ 31 መዛግብት በውሳኔው መሠረት ሙሉ በሙሉ ሲፈፀሙ 73 መዛግብት በአሁኑ ወቅት በአፈጻጸም ሂደት ላይ ይገኛሉ። ኮሚሽኑ ውሳኔዎችን የማስፈጸም አቅሙን ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን በመረዳት የአፈጻጸም መዛግብትን ብቻ ለይቶ የሚያይ የችሎት ቀን መሰየሙ አፈፃፀሙ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰሩ መሆኑ ተገምግሟል፡፡

የምርት ገበያ፣ የንግድ ውድድርና የሸማቾች ጥበቃ አስተዳደራዊ ችሎት እና የፌደራል የንግድ ውድድርና የሸማቾች ጥበቃ አስተዳደራዊ ይግባኝ ሰሚ ከፍትህ ሚኒስቴር በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት በተገቢው ነፃነት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ በፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን አስተዳደራዊ ድጋፍ የሚደረግላቸው ሲሆን በ2018 በጀት ዓመት የምርት ገበያ ህጎች እንዲከበሩ የማድረግ ሚና ቢኖርም በበጀት ዓመቱ የቀረበ አቤቱታ አለመኖሩ የተገመገመ ሲሀን ይሄንንም ለሚመለከተው አካል ሪፖርት ተደርጓል።

በሌላ በኩል የንግድ ውድድርና የሸማቾች ጥበቃ አስተዳደራዊ ችሎት በበጀት ዓመቱ 4 አዲስ የፀረ ውድድር መዝገቦች የተከፈቱ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 3ቱ ውሳኔ ሲያገኙ የቀረው 1 መዝገብ በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ላይ ብይን ለመስጠት በቀጠሮ ላይ ይገኛል። በተጨማሪም አንድ ነጋዴ በሌላ ነጋዴ ላይ ባቀረበው አቤቱታ ከባለፈው በጀት ዓመት የዞረ 1 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ግምት ያለው 1 መዝገብ እና 9 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ግምት ያለው 1 አዲስ መዝገብ በድምሩ 10 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ 2 መዝገቦች ቀርበው ሁለቱም እልባት አግኝተዋል። ተገቢ ባልሆነ የንግድ ውድድር ተግባር ምክንያት ለደረሰ ጉዳት ካሳ ይከፈለኝ በሚል የቀረቡ 2 መዝገቦችን ጨምሮ 371 ሺህ 500 ብር በፍትህ ሚኒስቴር አካውንት ገቢ ተደርጓል። ከቀረቡት 5 የአፈፃፀም መዝገቦች ውስጥ 3ቱ ሲፈፀሙ 2ቱ በሂደት ላይ የሚገኙ ሲሆን 8 የብርበራ ትዕዛዝ ይሰጥልኝ አቤቱታዎችም አስተናግዷል። በአጠቃላይ ለችሎቱ የቀረቡ 19 መዛግብት ሲሆኑ ከነዚህ ውስጥ 16ቱ ውሳኔ ሲያገኙ ቀሪዎቹ 3 መዛግብት ወደ ቀጣዩ በጀት ዓመት ተሸጋግረዋል።

የፌደራል የንግድ ውድድርና የሸማቾች ጥበቃ አስተዳደራዊ ይግባኝ ሰሚ በበኩሉ በስር ዳኝነት ችሎት የተሰጠው ውሳኔ ይሻርልኝ በሚል የቀረቡ 5፣ ተገቢ ያልሆነ የንግድ ውድድር ተፈፅሞብናል በሚል የቀረቡ 3 እንዲሁም የጉዳት ካሳ ይከፈለን በሚል የቀረቡ 2 አቤቱታዎችን ተቀብሎ ያስተናገደ ሲሆን በድምሩ የቀረቡት 5ቱም መዝገቦች ውሳኔ አግኝተዋል። በዚህም ሂደት በ4 መዝገቦች 168 ሺህ 750 ብር የዳኝነት ክፍያ ተሰብስቦ በፍትህ ሚኒስቴር አካውንት ገቢ ሆኗል።

በመጨረሻም መሪ ቃሉን፣ ርዕይ፣ ተልዕኮ እና እሴቶችን በሚገባ ተረድቶ ከራስ ጋር በማዋሃድ እያንዳንዱ የተቋሙ ሠራተኛ ከመንግሥት የተጣለበትን ኃላፊነትና የገባውን ቃል በማክበር ለ2019 በጀት ዓመት የተያዘውን ዕቅድ በስኬት እንዲጠናቀቅ ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ፕሬዚዳንት አሳስበዋል፡፡

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2019 በጀት አመት የዕቅድ ትውውቅ መድረክ አካሄደ፡፡********************ፌታይኮሐምሌ 13 ቀን ...
21/07/2026

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2019 በጀት አመት የዕቅድ ትውውቅ መድረክ አካሄደ፡፡
********************
ፌታይኮ
ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ
የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማና ትውውቅ መድረኩን ያስጀመሩት የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ክቡር ሙሉጌታ አያሌው እንዳሉት፤ በበጀት ዓመቱ አገራችን ያለችበትን የለውጥ ጎዳና በመገንዘብ ተቋማዊ ትራንስፎርሜሽንን በማፋጠንና የታክስ ፍትሕን በማረጋገጥ ረገድ በርካታ ስራዎች የተከናወኑበት ዓመት እንደነበር ገልጸዋል።

በ2018 በጀት ዓመት በርካታ የይግባኝ መዛግብትን በማስተናገድ አመርቂ ሥራዎች የተሰሩበት ዓመት እንደነበር ያወሱት ፕሬዚዳንቱ፤ ተቋሙን ከነበሩበት የመዝገብ መዘግየት ክፍተቶች ለማውጣትና ውሳኔዎችን በጥራትና በጊዜ ገደብ ውስጥ ለማውጣት የተካሄዱት ተቋማዊ ማሻሻያዎችና የግምገማ መድረኮች በርካታ ችግሮችን መቅረፍ መቻላቸውን ተናግረዋል።

በቀጣይ 2019 በጀት ዓመት የይግባኝ አቀራረብ በኦንላይን አገልግሎት በቴክኖሎጂ መደገፍ ፣ የህግ ተገዢነትና ተፈፃሚነት፣ የውሳኔዎችን ጥራት እና የአስፈጻሚ አካላትን አቅም ከማጎልበት ጋር ተያይዞ በትኩረት እንደሚሰራ ፕሬዚዳንቱ ገልፀዋል።

የዓመቱን የተጠቃለለ የአፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት የኮሚሽኑ የእቅድ ዝግጅት ግምገማና ለውጥ ስራ አመራር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ሙሉነህ ታምሩ፤ በበጀት ዓመቱ በየዘርፉ በርካታ ስኬታማ ስራዎች መከናወናቸውን ገልፀው የይግባኝ አቤቱታዎችን ፍትሐዊ ፣ ፈጣንና ጥራት ባለው መልኩ ምላሽ የመስጠት አቅም ማደጉን ፣ የችሎት አሰራርን እና የመዝገብ አስተዳደርን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ (ዲጂታል ሲስተም) ለማስደገፍ የተከናወኑ ተግባራትን ፣ ከባለድርሻ አካላት እና ከተከራካሪ ወገኖች ጋር የተሰሩ የትብብርና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች አበረታች እንደነበሩ ተናግረዋል።

በመጨረሻም የስራ ክፍል መሪዎች ከኮሚሽኑ ፕሬዚዳንት ጋር የ2019 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ውል ስምምነት ተፈራርመዋል።

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የማህበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስ ቡክ፡- https://www.facebook.com/ftacofficial
ቴሌግራም፡- https://t.me/ftac_official
ትዊተር፡- https://twitter.com/federal_appeal
ዩ ቱብ፡- https://www.youtube.com/channel/UCzpuuuXybdHh7BlgWXMVIGw

Address

Piazza, Giyorgis, Belay Zeleke Road, In Front Of Soramba Hotel, Ministry Of Justice Arada Court Building 9-10 Floor
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን/Federal Tax Appeal Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share