14/12/2021
የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የቀድሞ ሰልጣኞች ለመከላከያና ህዝባዊ ሰራዊቱ ድጋፍ አደረጉ
ታህሳስ 05/2014ዓ.ም
የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የቀድሞ የአትሌቲክስ ሰልጣኞች ግምታቸው 40,000 ብር (አርባ ሺህ ብር ) የሚያወጣ ፓስታ፣ዘይትና የንፅህና መጠበቂያ የቁሳቁስ ለመከላከያ ሠራዊት ድጋፍ አድርገዋል ።
አካዳሚው ሰራተኞቹን አስተባብሮ ካዘጋጀው ስንቅና ቁሳቁስ ጋር በአንድ ላይ ለመከላከያ እና ህዝባዊ ሰራዊት ወደ ግንባር እንዲላክላቸው ለአካዳሚው አስረከቡ፡፡
ድጋፉ በአሰልጣኝ ተሾመ ከበደ አስተባባሪነት የተሰበሰበ ሲሆን እሳቸውን ጨምሮ ኢትዮጵያን በተለያዩ የአለም አትሌቲክስ መድረኮች ሀገራቸውን ያስጠሩ አትሌት ጌትነት ዋለ፣ አትሌት አብርሃም ስሜ ፣አትሌት ዘርፌ ወንድማገኝ እንዲሁም አትሌት መልኬነህ አዘዝ እና አትሌት መልካሙ ዘገየ ድጋፉን አድርገዋል፡፡
አትሌቶቹ በሰጡን አስተያየት የሃገራቸው ጉዳይ የሚመለከታቸው እና የሚያሳስባቸው በመሆኑ የበኩላቸውን ድጋፍ እንዳደረጉ በመግለፅ በቀጣይም ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል ፡፡