25/06/2026
ባለስልጣኑ የግል ጤና ተቋማት የብቃት ማረጋገጫ እድሳት ሙሉ በሙሉ ኦን ላይን ማከናወን የሚያስችል ተግባራትን እያከናወነ ነው፡፡
--------------------------------
ሰኔ 18/2018ዓ.ም
የአዲስ አበባ ምግብ መድሃኒት ባለስልጣን የጤና ተቋማትና ባለሙያዎች ብቃት ማረጋገጥ ዳይሬክቶሬት አገልግሎቱን ተደራሽና ፈጣን ለማድረግ በ2019 በጀት ዓመት የግል ጤና ተቋማት ሙሉ በሙሉ በኦን ላይን ብቃት ማረጋገጥ አገልግሎት ማከናወን የሚያስችል ሰፊ ቅድመ ዝግጅት ስራ እያከናወነ ይገኛል፡፡
ባለስልጣኑ በከተማዋ የሚገኙ የግል ጤና ተቋማት መረጃ ዲጂታላይዝድ በማድረግ በ 2019 በጀት ዓመት በኦንላይን ሙሉ በሙሉ ብቃት ማረጋገጥ እድሳት አገልግሎት ማከናወን እንዲችሉ ለተቋማቱ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ተግባራትን እያከናወነ ነው፡፡
ባለስልጣኑ አገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻልና ተደራሽነቱን በማስፋት የተቋማትን መረጃ ዲጂታላይዝድ በማድረግ ጤና ተቋማት ኦን ላይን ብቃት ማረጋገጫ እድሳት እንዲያከናወኑ ከተቋማት ባለቤቶች ጋር የአሰራር ሲስተም የስልጠና የመስጠት እና የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡