የካ ወረዳ 1 ኮሙኒኬሽን _ Yeka woreda 1 communication

የካ ወረዳ 1 ኮሙኒኬሽን _ Yeka woreda 1 communication የመንግስት የህዝብ ግንኙነት

የመስቀል ደመራና ኢሬቻ በዓላትን ሀይማኖታዊና ባህላዊ እሴታቸውን በጠበቀ መልኩ በህብረትና በአንድነት ለማክበር ዝግጁ መሆናቸውን ሴቶች ገለጹመስከረም 10/2019 ዓ.ም (የካ ኮሙኒኬሽን)በየካ...
20/09/2026

የመስቀል ደመራና ኢሬቻ በዓላትን ሀይማኖታዊና ባህላዊ እሴታቸውን በጠበቀ መልኩ በህብረትና በአንድነት ለማክበር ዝግጁ መሆናቸውን ሴቶች ገለጹ

መስከረም 10/2019 ዓ.ም (የካ ኮሙኒኬሽን)

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የመስቀል ደመራና የኢሬቻ በዓላት አከባበር በተመለከተ በወረዳ ደረጃ ሲካሄድ የቆየው የሴቶች የምክክር መድረክ የማጠቃለያ ፕሮግራም ተካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር እሸቱ ለማ እንደገለጹት፣ ሴቶች በማኅበራዊ፣ በኢኮኖሚና በሌሎች ዘርፎች ያላቸው አስተዋጽኦ ጠቅሰው
የመስቀል ደመራና የኢሬቻ በዓላት በሰላም፣ በመቻቻልና በመከባበር እንዲከበሩ ሴቶች ያላቸውን ማኅበራዊ ሚና በመጠቀም በአከባበሩ ሂደት ላይ በንቃት እንዲሳተፉ አሳስበዋል።

የአዲስ አበባ አስተዳደር የሴቶች፣ ሕፃናትና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ገነት ቅጣው በበኩላቸው አዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ብሔረሰቦችና ባህሎች መገኛ ከተማ መሆኗን ጠቁመው የመስቀል ደመራና የኢሬቻ በዓላት ሃይማኖታዊና ባህላዊ እሴቶቻቸውን ጠብቀው በሰላም፣ በመቻቻልና በመከባበር እንዲከበሩ ሴቶች ከእንግዳ አቀባበል ጀምሮ ንቁ ተሳትፎ ማድረግና የሚጠበቅባቸውን ሚና መወጣት እንዳለባቸው ገልጸዋል።

የየካ ክፍለ ከተማ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ተራማጅ ተረፈ እንደገለጹት የመስቀል ደመራና የኢሬቻ በዓላት በሰላም፣ በአንድነትና በመቻቻል እንዲከበሩ ሴቶች በሰላም ግንባታና በማኅበራዊ ትስስር ያላቸውን ሚና በማጠናከር ንቁ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በመድረኩ በየካ ክፍለ ከተማ የሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በወይዘሮ እናቴነሽ አለማየሁ አዘጋጅነት የቀረበውና የመስቀል ደመራ በዓል አከባበርን የተመለከተው የውይይት ሰነድ ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

በበዓላቱ አከባበር ወቅት የሴቶችን ተሳትፎ ማሳደግ፣ የባህልና የሃይማኖት እሴቶችን ጠብቆ ለተተኪው ትውልድ ማስተላለፍ፣ እንዲሁም እንግዳ አቀባበልና ሰላማዊ አከባበርን ማረጋገጥ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር ተካሂዷል።

የመድረኩ ተሳታፊዎችም የመስቀል ደመራና የኢሬቻ በዓላትን በሰላም፣ በደማቅ ሁኔታና በህብረ ብሔራዊ አንድነት ለማክበር በቅንጅት ለመሥራት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 አስተዳደር ስር በሚገኙት የኬላ እና 41 እየሱስ  የሰንበት ገበያዎች መጪዎችን የመስቀል ደመራና ኢሬቻ በዓላትን ምክንያት በማድረግ እስስከ  ረቡዕ ክፍት ሆነው የ...
20/09/2026

በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 አስተዳደር ስር በሚገኙት የኬላ እና 41 እየሱስ የሰንበት ገበያዎች መጪዎችን የመስቀል ደመራና ኢሬቻ በዓላትን ምክንያት በማድረግ እስስከ ረቡዕ ክፍት ሆነው የሚቆዩት ገበያዎች በሰፊው
‎የኢንዱስትሪና የግብርና ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረባቸው አስታውቋል።
‎የካ ወረዳ 1ኮሙኒኬሽንመስከረም 10/2019 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ የሠራተኞች ምልመላና ቅጥር ሂደቱ ፍጹም ግልጽ፣ ፍትሐዊና በውጤት ላይ ብቻ የተመሠረተ እንዲሆን ጥብቅ አሰራር ዘርግቶ እየሰራ ይገኛል።በዚህ ሂደት ላይ...
20/09/2026

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ የሠራተኞች ምልመላና ቅጥር ሂደቱ ፍጹም ግልጽ፣ ፍትሐዊና በውጤት ላይ ብቻ የተመሠረተ እንዲሆን ጥብቅ አሰራር ዘርግቶ እየሰራ ይገኛል።
በዚህ ሂደት ላይ በማንኛውም መልኩ ሕገ-ወጥ አሰራር፣ አድሎ ወይም የሙስና ሙከራ ተፈጽሟል የሚል ተጨባጭ መረጃና ማስረጃ ያላችሁ ወገኖች ጥቆማችሁን እንድታቀርቡ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
መረጃችሁን ይዛችሁ መቅረባችሁ ለሥራችን እንደተደረገ ትልቅ እገዛና አጋርነት ይቆጠራል።

ከተማ አስተዳደሩ የሚቀርቡለትን ጥቆማዎች በጥልቀትና በገለልተኝነት መርምሮ ጥፋት በተገኘበት አካል ላይ የማያዳግም ሕጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ ለመውሰድ ሙሉ ዝግጁነቱን ያረጋግጣል።
ጥቆማና ማስረጃ ማቅረቢያ አድራሻዎች፦
• በነጻ የስልክ መስመር፦9977
• በቀጥታ የስልክ መስመሮች፦011 171 0281 / 011 171 0993 / 011 171 0477 / 011 171 0556
• በአካል፦ በከንቲባ ጽሕፈት ቤት የፀረ-ሙስና ግብረ-ኃይል
ከማህበራዊ ሚዲያ ይልቅ ችግሩን በተጨባጭና በሕጋዊ መንገድ መፍታት የሚችለው የከተማ አስተዳደሩ ነው!

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ የሠራተኞች ቅጥር ሂደትን በተመለከተ በማህበራዊ ሚዲያ ለሚሰራጩ ሐሰተኛና መሠረተ-ቢስ መረጃዎች የተሰጠ ማብራሪያ

እንደሚታወቀው የከተማ አስተዳደሩ ጤና ቢሮ በአዲስ ላስገነባቸው ሆስፒታሎች ሠራተኞችን ለመቅጠር መመሪያው በሚፈቅደው መሠረት ግልጽ ማስታወቂያ አውጥቶ በቅጥር ሂደት ላይ ይገኛል። ሆኖም አንዳንድ ኃላፊነት የማይሰማቸው የማህበራዊ ሚዲያ አካላት የቅጥር ሂደቱን ለማደናቀፍ በሚመስል መልኩ ሐሰተኛ መረጃዎችን እያሰራጩ ይገኛሉ።

በጉዳዩ ላይ እውነታውን ግልጽ ለማድረግ የሚከተሉትን ነጥቦች እናሳውቃለን፦
1ኛ. እስከ አሁን ድረስ ለተቋማቱ አዲስ ተቀጥሮ የተመደበ ምንም ዓይነት ሠራተኛ የሌለ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በሆስፒታሎቹ ውስጥ እየሰሩ የሚገኙትም ከከተማ አስተዳደሩ ነባር ሆስፒታሎችና ጤና ጣቢያዎች በውሰት የተመደቡ መሆናቸውን ማንኛውም አካል ማረጋገጥ ይችላል።

2ኛ. እየተሰራጨ ያለውን መሠረተ-ቢስ መረጃ ለማጀብ ሲባል በከተማ አስተዳደሩ በቀጥታ የማይተዳደሩና ቢሮው ቅጥር ፈጽሞላቸው የማያውቁ ተቋማት ስም ጭምር በዘገባው ተካቷል።

3ኛ. ቢሮው በጭራሽ የቅጥር ማስታወቂያ ያላወጣባቸው የሙያ ዘርፎች (ለምሳሌ፦ የድንገተኛ ቀዶ-ሕክምና ባለሙያ የመሳሰሉ በሆስፒታሎቹ የሙያ መደባቸው የሌለና በአሁኑ ሰዓት በውሰት እንኳ የማይገኙ ሙያዎች) እንደተቀጠሩ ተደርጎ ፍጹም ሐሰተኛ መረጃ ተሰራጭቷል።

በተጨማሪም ገና ለፈተና ያልተጠሩና ፈተና በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ እንደ ሰመመን ሰጪ (አንስቴዥያ) ባለሙያዎች ፈተና ወስደው እንደተቀጠሩ ተደርጎ ከመዘገቡ ባሻገር፣ የጨቅላ ሕጻናት ነርስ ባለሙያዎችን ጨምሮ በማንኛውም ሙያ ቅጥር ባልተፈጸመበት ሁኔታ ቅጥር እንደተከናወነ ተደርጎ መዘገቡ መረጃው ከእውነት የራቀ ፈጠራና ውንጀላ መሆኑን ያረጋግጣል።

ስለሆነም እየተሰራጨ ያለው መረጃ ተራ አሉባልታ መሆኑን እየገለጽን፣ ቢሮው አጠቃላይ የቅጥር ሂደቱን ግልጽነት በተሞላበት መልኩ ለመምራት የሚከተሉትን አሰራሮች ተግባራዊ አድርጓል፦

1. ለአገልግሎት አሰጣጡ ጥራትና ለሥራው ተገቢው እውቀት፣ ብቃትና ክህሎት ያላቸው መሆኑን ለማረጋገጥ፣ ፈቃድ ሰጪ ተቋማት የሰጡትና የመጠቀሚያ ጊዜው ያላለፈ ወይም የታደሰ ሕጋዊ የሙያ ፈቃድ ያላቸው መሆን ግዴታ እንዲሆን ተደርጓል።
2. የምዝገባ ሂደቱ ከሰው ንክኪ ነጻ በሆነ መልኩ ሙሉ በሙሉ በበይነ-መረብ (ኦንላይን) እንዲከናወን ተደርጓል።

3. ከምዝገባ በኋላ መስፈርቱን አሟልተው ለፈተና የሚቀርቡ ተወዳዳሪዎች ስም ዝርዝር ማንኛውም ሰው ሊመለከተው በሚችልበት የቢሮው ይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ይፋ ይደረጋል።

ጥሪ በሚደረግበት ወቅትም መስፈርቱን አሟልተው ስማቸው ያልተካተተ ቢኖር እንኳ ቅሬታ የሚያቀርቡበት ሥርዓት ተዘርግቷል። በዚህም በተፈቀደው የምዝገባ ጊዜ ውስጥ በበይነ-መረብ ተመዝግበው የተጠየቀውን መስፈርት እስካሟሉ ድረስ ታይቶ ለፈተና የሚቀመጡበት ሁኔታ ተመቻችቷል፤ ከተቀመጠው አቅጣጫ ውጪ በምንም ዓይነት ሁኔታ ለፈተና የተቀመጠ ተፈታኝ የሌለ መሆኑን እናረጋግጣለን።

4. የፈተና ሂደቱ ጥንቃቄ የተሞላበት እንዲሆን በከተማ አስተዳደሩ ሥር በሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ባለሙያዎች አማካኝነት እንዲሰጥ ተወስኖ፣ በየተቋማቱ የፈተና አሰጣጥ መመሪያው በሚፈቅደው መሠረት በጥንቃቄ እየተተገበረ ይገኛል።

በመሆኑም በቅጥር ሂደቱ ላይ እየተሳተፋችሁ ያላችሁ ክቡራን ተወዳዳሪዎች ፣ የምልመላና የቅጥር ሂደቱ በተወዳዳሪዎች የውጤት ብልጫ ላይ ብቻ የተመሠረተ መሆኑን ተገንዝባችሁ በተረጋጋ መንፈስ እንድትወዳደሩ እናሳውቃለን።

በተመሳሳይ መልኩ ቢሮው በሚያከናውነው የሰው ኃይል ቅጥርም ሆነ ስምሪት ላይ ከሕግና ከመመሪያ ውጪ ስለመሰራቱ ትክክለኛ ማስረጃ ማቅረብም ሆነ ጥቆማ መስጠት የሚችል ማንኛውም አካል ለከተማ አስተዳደሩም ሆነ ለጤና ቢሮው በማንኛውም ሰዓት ማቅረብ እንደሚችል እንገልጻለን። እስከ አሁን ድረስ ከማንኛውም ሚዲያም ሆነ ግለሰብ ከጉዳዩ ጋር ተያያዥነት ያለው ምንም ዓይነት ጥያቄም ሆነ ጥቆማ ያልቀረበልን ቢሆንም፣ ከየትኛውም ወገን የሚመጣን ጥቆማ ተቀብለን አስፈላጊውን ማጣራት ለማድረግ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ዝግጁ መሆናችንን እናረጋግጣለን።

በየካ  ክ/ከተማ ወረዳ 1 ለሚገኙ የሰላም ሰራዊት አባላት የአንድ ማዕከል የፀጥታ ስምሪት ዛሬም ተጠናክሮ ቀጥሏል::‎‎የካ ወረዳ 1 ኮሙዩኒኬሽን መስከረም 9/2019ዓም‎‎በመርሐ ግብሩ ተገኝ...
19/09/2026

በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 1 ለሚገኙ የሰላም ሰራዊት አባላት የአንድ ማዕከል የፀጥታ ስምሪት ዛሬም ተጠናክሮ ቀጥሏል::

‎የካ ወረዳ 1 ኮሙዩኒኬሽን መስከረም 9/2019ዓም

‎በመርሐ ግብሩ ተገኝተው ለሰላም ሰራዊቱ አባላት መልክት ያስተላለፉት የየካ ክ/ከተማ የብልፅግና የኢንስፔክሽን ና ስነ ምግባር ኮሚሽን ጽ/ቤት ኃላፊ
‎አቶ ተፈራ ማመሞ የከተማችን ሰላም በማስጠበቅ ረገድ እንዲሁም ከፊታችን የሚከበሩት የመስቀልና ኢሬቻ በዓል ሃይማኖታዊና ባህላዊ እሴታቸውን ጠብቀውበሰላም እንዲከበሩ የሰላም ሰራዊቱ ሚና ልዩ ምስጋና የሚቸረው ብለዋል ። ሰላም የአንድ ግዜ ብቻ ሳይሆን ቀጣይነት ያለው ተግባር በመሆኑ የሰላም ሰራዊቱ ይህንን ተግባር አጠናክ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል ።

በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 አስተዳደር የ2019 ዓ.ም የመስቀል እና የኢሬቻ  በዓላት አከባበርን በተመለከተ በተዘጋጀው ሰነድ ላይ  የማጠቃለያ ውይይት ተካሄደ። ‎የካ ወረዳ 01 ኮሙኒኬሽን...
19/09/2026

በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 አስተዳደር የ2019 ዓ.ም የመስቀል እና የኢሬቻ በዓላት አከባበርን በተመለከተ በተዘጋጀው ሰነድ ላይ የማጠቃለያ ውይይት ተካሄደ።
‎የካ ወረዳ 01 ኮሙኒኬሽን መስከረም 9/2019አ.ም

‎በማጠቃለያ መድረኩ ላይ በቀረበው ሰነድ የመስቀልና ኢሬቻ በዓላት ላይ በቂ ግንዛቤ በመያዝ ሀይማኖታዊና ባህላዊ ትውፊታቸውን ጠብቀው እንዲከበሩ በማድረግ ለከተማችን ኢኮኖሚ መነቃቃትን የበኩላችንን መወጣት እንደሚገባና የመስቀል ደመራና ኢሬቻ በዓላት በዩኔስኮ በዓለም ቅርስነት የተመዘገቡ ታላላቅ በዓላቶች በመሆናቸው ስለ በዓላቱ ግንዛቤ ኖሮት እንዲያከብር አዎንታዊ ድርሻቸውን ሊወጣ እንደሚተጋ ተገልጿል።

‎በውይይት መድረኩ የአዲስ አበባ ምክር ቤት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ መንግስቱ ላማሮ እንደተናገሩት የዘንድሮው የመስቀል እና የኢሬቻ በዓላትን ስናከብር የኢትዮጵያን የማሰራራት ማሳያ የሆኑ በርካታ ተግባራት የተከናወኑበት በተለይም እነዚህ በዓላት የኢትዮጵያውያን የአንድነት መንፈስን የሚያጎለብቱ ናቸው፤ በበዓላቱ ላይ በተለያየ አከባቢ የሚኖሩ ሰዎች ተሰብስበው በመደጋገፍና በመተሳሰብ ፍቅርን ያሳያሉ። ይህም ኢትዮጵያ የብዙሃን ሀገር እንደሆነች የሚያሳይ እና የኢሬቻ እና የመስቀል በአላት የኢትዮጵያ የአብሮነት መገለጫዎች ናቸው በመሆኑ የእኛ የኢትዮጵያን የአደባባይ ህዝባዊ በዓላት የአብሮነትና የፍቅር መገለጫነታቸውን በጠበቀ ሁኔታ በሰላምና በጋራ ማክበር አለብን ብለዋል።

‎የየካ ክፍለ ከተማ ሴቶች ፣ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ እናቴነሽ አለማየሁ በበኩላቸው የመስቀልና ኢሬቻ በዓላት በኢትዮጵያውያን ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጣቸው ከመሆኑም በላይ በዓላቱ ሲከበሩ በተለያየ የሀገሪቱ ክፍል የሚኖሩ ዜጎች በደስታና በሰላም በአደባባዮች ወጥተው አብረው እንዲያከብሩ ዕድል ይሰጣሉ። ኢሬቻ ሲከበር የኦሮሞ ማህበረሰብ በአንድ ቦታ ተሰብስበው ፈጣሪን ስለተፈጥሮ ጸጋ አመስግነው ምሕረትን ሲለምኑ፤ መስቀል ሲከበር ደግሞ ክርስቲያኖች ደመራ ለኩሰው በደስታ ይዘምራሉ እነዚህ ሁሉ መገለጫ ህብረ ብሔራዊነታችንን የሚያሳዩ ነው ብለዋል።

‎የየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለሙ ኢሞሮ በበኩላቸው የመስቀል ደመራ እና የኢሬቻ በዓላት የኢትዮጵያ ሕዝቦች መንፈሳዊ ፣ ባህላዊ እና ማህበራዊ እሴቶች ጎልተው የሚታዩባቸው አብሮነትን ዕርቅን የሚያጠናክሩ ታላላቅ የመኸር ወቅት በዓላት መሆናቸውን የገለፁ ሲሆን።

‎በተዘጋጀው የመወያያ ሰነድ ላይ በተሳታፊዎች ሀሳብና አስተያየት የተነሳ ሲሆን ሁሉም በዓላት ሃይማኖትና ባህላዊ እሴቶች ተጠብቆ በሰላምና በአብሮነት ለማክበር የየድርሻቸውን በጋራ ልንወጣ ይገባናል ተብለዋል።

በየካ ክፍለ ከተማ የቀበና ካፕ የስፖርት ውድድር ተጀመረ መስከረም 09/2019 ዓ.ም:  የካ ኮሙኒኬሽን የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት  ከቤላ ኢቨንት ጋር በመተባበር...
19/09/2026

በየካ ክፍለ ከተማ የቀበና ካፕ የስፖርት ውድድር ተጀመረ

መስከረም 09/2019 ዓ.ም: የካ ኮሙኒኬሽን

የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ከቤላ ኢቨንት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው “ቀበና ካፕ” የስፖርት ውድድር ተጀምሯል።

የውድድሩ ዋና ዓላማ በቀበና ወንዝ ዙሪያ የታየውን ተጨባጭ የልማት ለውጥ ለወጣቶች ማስተዋወቅ፣ ወጣቶች ከትርፍ ጊዜ አጠቃቀም አንፃር በስፖርት እንዲሳተፉ ማበረታታት እና ጤናማ የአኗኗር ልምድን ማጎልበት ሲሆን ወጣቶች በስፖርት ያላቸውን ተሳትፎ በማሳደግ የወደፊት ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት የሚያግዝ መድረክ ለመፍጠር ያለመ ነው።

በውድድሩ መክፈቻ መርሃ ግብር የየካ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ብስራት ማጆሬ፣ የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ መስከረም በቀለ፣ የቤላ ኢቨንት አስተባባሪዎች እና የስፖርት ማህበረሰቡ ተገኝተዋል።

የ“ቀበና ካፕ” ውድድር ወጣቶችን በስፖርት እንዲተባበሩ፣ ተሰጥኦአቸውን እንዲያሳዩ እና ጤናማና ንቁ የሆነ የህይወት ዘይቤን እንዲከተሉ ለማበረታታት ያለመ መርሃ ግብር መሆኑ ተገልጿል።

የመስቀል ደመራና ኢሬቻ በዓላት ሀይማኖታዊ እና ባህላዊ እሴታቸውን ጠብቀው በሰላም እንዲከበሩ ዝግጁ መሆናቸው የሰላም ሰራዊት አባላት ገለፁ መስከረም 9/2019 ዓ•ም የካ ኮሙኒኬሽን“ሰላማችን...
19/09/2026

የመስቀል ደመራና ኢሬቻ በዓላት ሀይማኖታዊ እና ባህላዊ እሴታቸውን ጠብቀው በሰላም እንዲከበሩ ዝግጁ መሆናቸው የሰላም ሰራዊት አባላት ገለፁ

መስከረም 9/2019 ዓ•ም የካ ኮሙኒኬሽን

“ሰላማችንን እንጠብቅ፣ ባህላችንን እናክብር!” በሚል መሪ ሀሳብ የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የ2019 ዓ.ም. የመስቀል ደመራና የኢሬቻ በዓላት በሰላምና በፀጥታ እንዲከበሩ ከ12ቱም ወረዳዎች ከተውጣጡ የሰላም ሰራዊት አባላት ጋር የማጠቃለያ ውይይት አካሂዷል።

በመድረኩ የበዓላቱን ሃይማኖታዊ ይዘትና ባህላዊ እሴት በመጠበቅ፣ ሰላማዊ አከባበራቸውን ለማረጋገጥ በሰላም ሰራዊቱ፣ በፀጥታ አካላትና በህብረተሰቡ መካከል የተቀናጀ ሥራ እንዲጠናከር አቅጣጫ ተቀምጧል።

የየካ ክፍለ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ደረጀ የሰላም ሰራዊቱ ከፀጥታ አካላትና ከአጎራባች ክፍለ ከተሞች ጋር በቅንጅት በመስራት ለበዓላቱ ሰላማዊ አከባበር የሚጠበቅበትን ሚና እንዲወጣ አሳስበዋል።

የየካ ክፍለ ከተማ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ ሀላፊ ዋና ኢንስፔክተር አለማየሁ አርጋውም የፀጥታ አካላት በበዓላቱ ወቅት ዝግጁ እንዲሆኑና የሰላም ሰራዊቱ ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር ሰላማዊ አከባበሩን እንዲያግዝ ገልጸዋል።

የመስቀል ደመራና ኢሬቻ በዓላት ሀይማኖታዊ እና ባህላዊ እሴታቸውን ጠብቀው ድፁም ሰላማዊ በሆነ መልኩ እንዲከበሩ ዝግጁ መሆናቸው በክፍለ ከተማው የሚገኙ የሰላም ሰራዊት አባላት ገልለዋል።

የ2019 መስቀል ደመራና ኢሬቻ በዓላት ሀይማኖታዊ እና ባህላዊ ትውፊታቸውን ጠብቀው በሰላም እንዲከበሩ ውይይት ተካሄደ።‎‎የካ ወረዳ 1 ኮሙኒኬሽን  መስከረም 9/2019 ዓ/ም‎‎የየካ ክ/ከተ...
19/09/2026

የ2019 መስቀል ደመራና ኢሬቻ በዓላት ሀይማኖታዊ እና ባህላዊ ትውፊታቸውን ጠብቀው በሰላም እንዲከበሩ ውይይት ተካሄደ።

‎የካ ወረዳ 1 ኮሙኒኬሽን መስከረም 9/2019 ዓ/ም

‎የየካ ክ/ከተማ ወረዳ 1 አስተዳደር የ2019 መስቀል ደመራና ኢሬቻ በዓላት ሀይማኖታዊ እና ባህላዊ ትውፊታቸውን ጠብቀው በሰላም እንዲከበሩ
‎ከተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት አካሄደ።

‎የመስቀል ደመራ እና የኢሬቻ በዓላት በአለም ቅርስነት የተመዘገቡ የኢትዮጵያውያን የባህል ሀብትና የእርስ በርስ ትስስር ትልቅ ማሳያ ናቸው። በአላቱ ሃይማኖታዊና ባህላዊ እሴታቸውን ጠብቀው በሰላም እንዲከበሩ ሁሉም ማህበረሰብ በወንድማማችነትና በእህትማማችነት መንፈስ እንዲያከብራቸው ማድረግ ይገባል ።
‎በውይይቱ ሁለቱም በዓላት ስናከብር የኢትዮጵያን መልካም ገጽታ የሚያሳዩ በመሆኑ የእንግዳ ተቀባይነትና የአንድነት ባህል በሚያጠናክር መልኩ ሊከበር ይገባል።

በየካ  ክ/ከተማ ወረዳ 01 አስተዳደር የሚገኙት የ41 እየሱስ ና ኬላ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች የተለያዩ የግብርና ና ኢንደስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ የማቅረብ ስራ ተጠናክሮ ...
19/09/2026

በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 01 አስተዳደር የሚገኙት የ41 እየሱስ ና ኬላ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች የተለያዩ የግብርና ና ኢንደስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ የማቅረብ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

‎የካ ክ/ከተማ ወረዳ 01 ኮሙኒኬሽን መስከረም 9/2019ዓ.ም

‎በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 በሚገኙ የ41 እየሱስ ና ኬላ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች የተለያዩ የግብርና ና ኢንደስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ የማቅረብ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

‎በእነዚህ የገበያ ማዕከላት አምራች ኢንዱስትሪዎች፣ አርሶ አደሮች፣ ነጋዴዎች እና የሸማቾች ህብረት ሥራ ማህበራት ምርቶቻቸውን በቀጥታ ለህብረተሰቡ እንዲያቀርቡ ተደርጓል።

የአለም የፅዳት ቀን ምክንያት በማድረግ በአንድ ማዕከል የፅዳት ዘመቻ ንቅናቄ ተደረገ ።‎የካ ወረዳ 01 ኮሙኒኬሽን መስከረም 9/2019አ.ም‎የየካ ክ/ከተማ ወረዳ 1 አስተዳደር የአለም የፅዳ...
19/09/2026

የአለም የፅዳት ቀን ምክንያት በማድረግ በአንድ ማዕከል የፅዳት ዘመቻ ንቅናቄ ተደረገ ።
‎የካ ወረዳ 01 ኮሙኒኬሽን መስከረም 9/2019አ.ም
‎የየካ ክ/ከተማ ወረዳ 1 አስተዳደር የአለም የፅዳት ቀን ምክንያት በማድረግ '' ከንፁህ ሳህንኖች ወደ ንፁህ ከተሞች '' በሚል መሪ ቃል በአንድ ማዕከል የፅዳት ዘመቻ ንቅናቄ ተደረገ ።

‎በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፅዳት አስተዳደር ኢጀንሲ ምክትል ዳሬክተር አቶ ሙላት ተገኝ የከተማችን ፅዳት ባለፍው የለውጥ አመታት የለውጥ አመራሩ ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት እና ህብረተሰቡን ፅዳት ባህሉ እንዲያደርግ በመሰራቱ ከተማችን ንፁና ፅዱ ማድረግ ተችሏል ።
‎የየካ ወረዳ 1 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አዲስ አጎናፍር በበኩላቸው ዛሬ በወረዳችን የአለም የፅዳት ቀን ምክንያት በማድረግ '' ከንፁህ ሳህንኖች ወደ ንፁህ ከተሞች '' በሚል መሪ ቃል የሚደረገው የፅዳት ዘመቻ እንደ ወረዳችን ውብና ፅዱ ብሎክ ለመፍጠር አንዱ አካል ሲሆን ባለፉት ግዜያት በሁሉም ብሎክ መደበኛ የፅዳት ስራዎችን በመስራታችን ሞዴል ብሎኮችን መፍጠር ተችሏል ብለዋል ።
‎በፅዳት ዘመቻው የካ ክ/ከተማ ፅዳት አስተዳደር ፅ/ቤት ኃላፈ አቶ ቢሻው ግርማ ጨምሮ የፅዳት አምባሳደሮች ና ሃይማኖት አባቶች እንዲሁም ብሎክ ነዋሪዎች ተገኝተዋል ።

Address

Addis Ababa
1000

Telephone

+251913583624

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የካ ወረዳ 1 ኮሙኒኬሽን _ Yeka woreda 1 communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share