Yeka werda 09 Communication/የካ ወረዳ 09 ኮሙኒኬሽን

Yeka werda 09 Communication/የካ ወረዳ 09 ኮሙኒኬሽን ይህ የየካክ/ከተማ ወረዳ 09 ኮሙኒኬሽን የፌስቡክ ገጽ ነው።

ፔጃችንን ፎሎው በማድረግ አዳዲስና ትኩስ መረጃዎችን ያግኙ!!

ህዝባችን ምንም ያህል ጫና፣ ሐሰተኛ ወሬ ቢናፈስም፥ ይሄን ሁሉ ሳይበግረው ምርጫው፥ ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሐዊ እና ሰላማዊ ኾኖ እንዲያልፍ ደማቅ የታሪክ ዕጥፋት እንዲፃፍ ላበረከተው አስተዋፅኦ ከ...
25/06/2026

ህዝባችን ምንም ያህል ጫና፣ ሐሰተኛ ወሬ ቢናፈስም፥ ይሄን ሁሉ ሳይበግረው ምርጫው፥ ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሐዊ እና ሰላማዊ ኾኖ እንዲያልፍ ደማቅ የታሪክ ዕጥፋት እንዲፃፍ ላበረከተው አስተዋፅኦ ከልብ እናመሰግናለን።

ህብረተሰቡ በምርጫው ዕለት በከፍተኛ የዲሲፕሊንና የሰላም ስሜት ወጥቶ ድምጹን በመስጠት ለፓርቲው የሰጠው አደራ እና አመኔታ፤ በቀጣይ የተጀመሩ የልማትና የብልጽግና ጉዞዎችን ይበልጥ ለማጠናከር ትልቅ አቅምና ስንቅ እንደሚሆን ይሆናል።ፓርቲው ህዝብ የጣለበትን ታላቅ ኃላፊነት መሰረት በማድረግ የመረጠውን ህዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሌሊትና ቀን እንደሚሰራ በድጋሚ ቃሉን አድሷል።

የከተማችን ኗሪዎች ከሌሊቱ 9:00 ሰዓት እስከ ቀጣዩ ሌሊት 9:00 ሰዓት ሳይታክት ይሆነኛል የሚለውን ፓርቲ መርጧል። የመረጠው ፓርቲም ብልፅግና ኾኗል። ስለኾነም፣ የሰጠንን አደራ ሳንሸራርፍ አልቀን እንደምንፈፅም እየገለፅን ፣ ህዝባችን በድምፁ ያሳየውን የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ አስቀጥለን፣ ሰላማችን አፅንተን ከህዝባችን ጋር ኾነን የጀመርነውን ሁለንተናዊ የልማት ጥረት እንደምናስቀጥል እያረጋገጥን፤ ህዝባችን ለሰጠን አደራ እና እምነት ከልብ እናመሰግናለን።

የካ ወረዳ 09 ኮሙኒኬሽን ሰኔ 18/2018

ኢትዮጵያ ታከናውናለች፡ የአዲስ አበባ የአዲሱ ትውልድ አሻራ ከእንጦጦ እስከ ፒኮክባለፉት አምስት ዓመታት በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወነው የወንዞች ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ከተማዋ...
25/06/2026

ኢትዮጵያ ታከናውናለች፡ የአዲስ አበባ የአዲሱ ትውልድ አሻራ ከእንጦጦ እስከ ፒኮክ

ባለፉት አምስት ዓመታት በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወነው የወንዞች ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ከተማዋን ውበት ከማልበስ ባለፈ የነዋሪዎቿን የደኅንነት፣ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ሕይወት ምሕዋር ሙሉ በሙሉ የቀየረ ሥር ነቀል የትራንስፎርሜሽን ማሳያ ሆኗል።

ይህ ግዙፍ መሠረተ ልማት ከእንጦጦ እስከ ፒኮክ ፓርክ እንዲሁም ከእንጦጦ እስከ ቀበና ከ22 ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያለውን መስመር በመሸፈን የከተማዋን መልክ በከፍተኛ ደረጃ ቀይሮታል።

ፕሮጀክቱ ከመልክዓ-ምድር ውበት እና ከወንዝ ዳርቻ ማስዋብ ባለፈ፣ ልማት ከአካባቢ ጥበቃ ጋር በተናበበ መልኩ በጥናትና በጋራ ግብ እንዴት ሊከወን እንደሚችል በተግባር ያሳየ ዘመናዊና ውጤታማ የፈጠራ አውድ ነው።

የዚህ አምስት ዓመት የልማት ጉዞ እጅግ የጎላው ስኬት የተመዘገበው በአካባቢ ጥበቃ ሽግግር እና በሕዝብ ደኅንነት ረገድ ነው።

ቀደም ሲል መርዛማ ኬሚካሎችና ቆሻሻዎች ይጣሉባቸው የነበሩ እንዲሁም ለከፍተኛ የጎርፍ አደጋ ተጋላጭ የነበሩ የከተማዋ ክፍሎች ዛሬ ላይ ወደ ንጹሕ፣ ጤናማ እና እፎይታን ወደሚሰጡ አረንጓዴ ስፍራዎች ተለውጠዋል።

ይህ የተቀናጀ የልማት ሥራ የፍሳሽ ማስወገጃ ቱቦዎችን ችግር በመፍታት እና የጎርፍ ሥጋትን በከፍተኛ ደረጃ በመቀነስ የወንዝ ዳርቻዎችን ተገን አድርገው በአስጊ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ በርካታ ነዋሪዎችን ሕይወት ታድጓል።

የተፈጥሮ ወንዞችን ከቆሻሻ መጣያነት አላቅቆ ወደ ቀደመ ተፈጥሯቸው በመመለስ የተረጋገጠው የወንዞች ትንሣኤም የነዋሪዎችን አስተሳሰብ እና የቦታ አጠቃቀም ወደ ሀብት የቀየረ ታላቅ ድል ነው።

በሌላ በኩል የፕሮጀክቱ ሰውን ማዕከል ያደረገ ስትራቴጂ የከተማዋን ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር በአዲስ መልክ አዋቅሮታል።

ሰፊ የሕዝብ መሰብሰቢያዎችን፣ የእግር ጉዞ መንገዶችን፣ የመዝናኛ ማዕከላትን እና የንግድ ቦታዎችን በማቀናጀት አዲስ አበባን በሰው ልጅ እንቅስቃሴና ምቾት ላይ የተመሠረተች ንቁ የቱሪስት መዳረሻ ማድረግ ተችሏል።

ከዚህም ባሻገር በግንባታ፣ በምሕንድስና፣ በመልክዓ-ምድር ውበት እና በሎጂስቲክስ ዘርፎች ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል።

አብዛኛው የመሠረተ ልማት ሥራ በሀገር ውስጥ ተቋራጮች እና በኢትዮጵያውያን መሐንዲሶች መከናወኑ የሀገር ውስጥ ባለሙያዎችን አቅም ወደ ላቀ ደረጃ ያሳደገ ነው።

በስፍራው የቆሙት የተለያዩ ሐውልቶች እና ምልክቶችም ከውበት ባለፈ የኢትዮጵያን ታሪክ እና ምድረ ቀደምትነት የሚገልጹ መታሰቢያዎች ሆነው አገልግለዋል።

ከዚህ ስኬት በስተጀርባ ያለው ጥልቅ ትርጓሜ ሲፈተሽ፣ ፕሮጀክቱ በከተማዋ የሥነ-ልቦና እና የማኅበረሰብ ግንባታ ላይ ያመጣው ለውጥ እጅግ የጎላ ሆኖ እናገኘዋለን።

ቀደም ሲል የነበረውን "የለንም" የሚል የተስፋ መቁረጥ ስሜት እና ራስን የማሳነስ ልማድ በመስበር፣ የከተማዋን የተፈጥሮ ሀብቶች ወደ ታላቅ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ እሴት መቀየር እንደሚቻል በተግባር ተረጋግጧል።

በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል ዓለም አቀፍ አርዓያነትን ካስመዘገበው የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ ስትራቴጂ ጋር የተናበበው ይህ ልማት፣ አዲስ አበባን ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ የአፍሪካ መዲናዎች ተርታ እንድትሰለፍ አድርጓታል።

በአጠቃላይ ባለፉት አምስት ዓመታት የተመዘገቡት እነዚህ ሁለንተናዊ ድሎች ከተማዋን ሰውን ማዕከል ባደረገ፣ ዘመናዊ፣ አረንጓዴና በኢኮኖሚ በጠነከረ መሠረት ላይ የገነቡ የትውልድ ታላቅ አሻራ ሆነው በታሪክ ይዘከራሉ።

በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 በቤተሰብ ቢዝነስ ለተደራጁ ነዋሪዎች የዶሮና የኬጂ ድጋፍ ተደረገ።የየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 አስተዳደር በወረዳው በቤተሰብ ቢዝነስ (Family Business)...
25/06/2026

በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 በቤተሰብ ቢዝነስ ለተደራጁ ነዋሪዎች የዶሮና የኬጂ ድጋፍ ተደረገ።

የየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 አስተዳደር በወረዳው በቤተሰብ ቢዝነስ (Family Business) የተደራጁ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ያደረገ የዶሮና የዶሮ ማስቀመጫ ኬጂ ድጋፍ አደረገ።

በድጋፍ መርሀግብሩ ላይ የወረዳው ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ብርሀኑ ዳሪሎና የወረዳው ምክትል ስራ አስፈጻሚና ስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ጌራወርቅ ኃይሉ ተገኝተዋል።

ድጋፉ የተደረገው አነስተኛ ገቢ ያላቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች በቤተሰብ ደረጃ በማደራጀት፣ የውስጥ አቅማቸውን በማውጣትና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የሚረዳ ነው።

"ይህ የቤተሰብ ቢዝነስ ሞዴል አነስተኛ ቦታ ያላቸውን ነዋሪዎች ወደ አምራችነት ለመቀየር ትልቅ ድልድይ ነው።

የድጋፉ ተጠቃሚ የሆኑት የነዋሪዎች ተወካዮች በበኩላቸው፥ የተደረገላቸው ድጋፍ በገበያ ላይ ያለውን የኑሮ ውድነት ለመቋቋም ትልቅ አቅም እንደሚሆናቸው ገልጸው፣ የተሰጣቸውን ቁሳቁስና ዶሮዎች በአግባቡ በመንከባከብ ውጤታማ ለመሆን ቃል ገብተዋል።

የካ ወረዳ 09 ኮሙኒኬሽን ሰኔ 18/2018

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር “በጎነት ለአዲስ አበባ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ ፈቃድ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም.፣ የካ ኮሙኒኬሽንየየካ ክፍለ ከተ...
25/06/2026

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር “በጎነት ለአዲስ አበባ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ ፈቃድ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ

ሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም.፣ የካ ኮሙኒኬሽን

የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በክረምት ወራት የሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ ሥራዎችን በይፋ ለማስጀመር በወረዳ 08 የፅዳት ዘመቻ እና የአቅመ ደካማ ቤተሰቦች የቤት እድሳት ሥራ በማስጀመር መርሃ ግብሩን በይፋ አስጀምሯል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፍፁም ኃይሌ፣ ባለፉት ዓመታት በበጎ ፈቃድ ሥራዎች በርካታ ሰው ተኮር ተግባራት መከናወናቸውን ገልፀው፣ ለአቅመ ደካሞች እና ለሃገር ባለውለታዎች ደረጃቸውን የጠበቁ መኖሪያ ቤቶችን በመገንባትና በማስረከብ፣ እንዲሁም የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ በርካታ ማህበራዊ ችግሮችን ማቃለል ተችሏል ብለዋል።

አቶ ፍፁም አክለውም በ2018/19 የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር የተለያዩ በጎ ፈቃደኛ ባለሀብቶችና ግለሰቦችን በማስተባበር በየደረጃው ከ280 በላይ ለሚሆኑ አቅመ ደካማ ዜጎች መኖሪያ ቤቶች እንደሚገነቡ ገልጸው፣ ልበ ቀና ባለሀብቶች በተጀመረው የክረምት በጎ ፈቃድ ሥራ ላይ በመሳተፍ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

የየካ ክፍለ ከተማ ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለሙ ኢመሮ በበኩላቸው፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በራስ ተነሳሽነት የሚከናወን የመደጋገፍና የመረዳዳት ተግባር መሆኑን ገልጸው፣ በክረምት መርሃ ግብሩ ወቅት የሚከናወኑ ሥራዎችን በዝርዝር አቅርበዋል።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የየካ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መገርሳ ገላና፣ የየካ ክፍለ ከተማ ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ብስራት ማጆሬ፣ የየካ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚና የሥራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ እንዳልካቸው አስራት፣ የየካ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሆርዶፋ ሲማ እንዲሁም የክፍለ ከተማና የ12ቱም ወረዳ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት እና ከሁሉም ወረዳዎች የተወጣጡ በጎ ፈቃደኞችና ነዋሪዎች የተገኙ ሲሆን የክረምት ጎርፍ መከላከል ስራ የውሃ መውረጃ ቦዮችን አፅድተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ያለፉ ዓመታት የፋይናንስ ጉዞ፣ ከገቢ ማሳደግ እስከ ልማት ተኮር የበጀት ሽግግርየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከ2010 እስከ 2019 በጀት ዓመት ያሳየው የፋ...
25/06/2026

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ያለፉ ዓመታት የፋይናንስ ጉዞ፣ ከገቢ ማሳደግ እስከ ልማት ተኮር የበጀት ሽግግር

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከ2010 እስከ 2019 በጀት ዓመት ያሳየው የፋይናንስ መረጃ፣ ከተማዋ በታሪኳ አይታው የማታውቀውን የኢኮኖሚ ዕድገትና መዋቅራዊ ሽግግር እያደረገች መሆኑን በግልጽ ያሳያል። ይህ የ10 ዓመታት ጉዞ ጠንካራ የገቢ አሰባሰብ አቅምን ከመገንባት ባለፈ፣ በጀትን አስተዳደራዊ ወጪዎችን በመቀነስ ለዘላቂ ልማት (ካፒታል) የማዋል ጤናማ የፋይናንስ ፖሊሲን የተገበረበት ነው።

መረጃዎቹ እንደሚያሳዩት፣ በ2010 በጀት ዓመት 40.5 ቢሊዮን ብር የነበረው የከተማዋ አጠቃላይ በጀት፣ በ2019 ወደ 502.27 ቢሊዮን ብር አድጓል። ይህ የ461.77 ቢሊዮን ብር (የ1140 በመቶ) አስደናቂ ዕድገት ሊመዘገብ የቻለው ከተማ አስተዳደሩ የገቢ አሰባሰብ አቅሙን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደጉ ነው።

በ2010 30 ቢሊዮን ብር ብቻ የነበረው የገቢ አሰባሰብ አፈጻጸም፣ በ1574.23 በመቶ (በ472.27 ቢሊዮን ብር) በማደግ በ2019 በጀቱን በሙሉ በራስ አቅም መሸፈን ወደሚያስችልበት ደረጃ ደርሷል። ይህ የገቢ ዕድገት እና የአጠቃላይ በጀት ዕድገት መመጣጠን፣ ከተማዋ የፋይናንስ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጧን እና በውስጥ አቅም ፕሮጀክቶችን የማስፈጸም ብቃቷ መጎልበቱን ያመላክታል።

ከቁጥራዊ ዕድገት ባሻገር፣ የከተማዋን የልማት ራዕይ ይበልጥ የሚያጎላው የበጀት ድልድል ስብጥር (Capital vs. Regular Budget) ለውጥ ነው። በ2010 የነበረው የካፒታል በጀት ድርሻ 53.18 በመቶ (21.53 ቢሊዮን ብር) የነበረ ሲሆን፣ ለመደበኛ ወይም ለሥራ ማስኬጃ 46.82 በመቶ (18.96 ቢሊዮን ብር) ይውል ነበር።

ነገር ግን በ2019 ይህ ምጣኔ መሠረታዊ ለውጥ አሳይቶ፣ የካፒታል በጀቱ ድርሻ ወደ 71 በመቶ (355.52 ቢሊዮን ብር) ሲያድግ፣ የመደበኛ በጀቱ ድርሻ ወደ 29 በመቶ (146.74 ቢሊዮን ብር) ዝቅ ብሏል። የአስተዳደራዊ ወጪዎችን (መደበኛ በጀት) በከፍተኛ ሁኔታ በመቀነስ የገንዘቡን አብዛኛውን እጅ ለመሠረተ ልማት እና ለትልልቅ ፕሮጀክቶች (ካፒታል በጀት) መዋሉ፣ ከተማዋ ፊቷን ሙሉ በሙሉ ወደ እድገትና ብልፅግና ላይ ለሚታይ ትክክለኛ ልማት ማዞሯን የሚያረጋግጥ የፖሊሲ ስኬት ነው።

በአጠቃላይ፣ እነዚህ መረጃዎች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሀብት አሰባሰብ አቅሙን እጅግ በላቀ ሁኔታ ከማስፋቱም በላይ፣ የተሰበሰበውን ሀብት በአግባቡ ቆጥቦ የነዋሪዎችን ኑሮ ለሚቀይሩ እና ከተማዋን ለሚያዘምኑ የካፒታል ፕሮጀክቶች ቅድሚያ በመስጠት ከፍተኛ የአመራር ብቃት እያሳየ መሆኑን በተጨባጭ የሚያስረዱ ናቸው።

የጎርፍ ተጋላጭነትን ለመቀነስ በየካ ክፍለ ከተማ የክረምት ጎርፍ አደጋ መከላከል ንቅናቄ በይፋ ተጀመረ​ ሰኔ 17 / 2018 ዓ.ም (የካ ኮሙኒኬሽን)​የክረምት ወቅት የጎርፍ አደጋን በመከላከ...
24/06/2026

የጎርፍ ተጋላጭነትን ለመቀነስ በየካ ክፍለ ከተማ የክረምት ጎርፍ አደጋ መከላከል ንቅናቄ በይፋ ተጀመረ

​ ሰኔ 17 / 2018 ዓ.ም (የካ ኮሙኒኬሽን)

​የክረምት ወቅት የጎርፍ አደጋን በመከላከል በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ፤ "ቦዮቻችን የንጹህ ውሃ መውረጃ እንጂ የቆሻሻ ማከማቻ ሊሆኑ አይገባም" በሚል መሪ ቃል በየካ ክፍለ ከተማ የክረምት ጎርፍ አደጋ ስጋት መከላከል ንቅናቄ በይፋ ተጀምሯል።

​በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ተፈራ ሞላ እንደገለጹት ውብ፣ ጽዱና ማራኪ ከተማ ለመገንባት የሁሉም የጋራ ተሳትፎ አስፈላጊ በመሆኑ ቆሻሻን በአግባቡ በመለየት ወደ ሀብትነት መቀየር፣ እንዲሁም የጎርፍና የፈሳሽ መውረጃ ቦዮችን በወቅቱ በማጽዳት የጎርፍ አደጋን በእጅጉ መቀነስ እንደሚቻል አስገንዝበዋል።

​የከተማዋን ንጽህና እና የነዋሪዎችን ደህንነት ለማስጠበቅ ቦዮችን ከቆሻሻ ነጻ ማድረግ የሁሉም ዜጎች የጋራ ኃላፊነት መሆኑን የገለጹት ዶ/ር ተፈራ ቆሻሻን በቦዮች ውስጥ መጣል የውሃ ፍሰትን በማስተጓጎል የጎርፍ አደጋን እንደሚያባብስና ለበሽታ መስፋፋትም ምቹ ሁኔታ ስለሚፈጥር በቅንጅት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

​የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ፍፁም ሀይሌ በበኩላቸው ደረቅ ቆሻሻን በአግባቡ በመሰብሰብና ወደ ሀብትነት በመቀየር፣ እንዲሁም የጎርፍና የፈሳሽ መውረጃ ቦዮችን በመደበኛነት በማጽዳት የጎርፍ ተጋላጭነትን በከፍተኛ ደረጃ መቀነስ እንደሚቻል አስገንዝበዋል።

​ይህ የንቅናቄ ስራ ለሚቀጥሉት ሦስት ወራት የሚቆይ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ፍፁም ነዋሪዎች ቆሻሻን በተዘጋጁ ቦታዎች ብቻ በመጣል እና ቦዮችን በንጽህና በመጠበቅ ለውብ፣ ጤናማ እና ከጎርፍ አደጋ ነፃ ከተማ እንድትሆን የበኩላቸውን ሁሉም ማህበረሰብ የበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል።

​በዚሁ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የአዲስ አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሞላት ተገኝን ጨምሮ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች፣ የወረዳ 12 ነዋሪዎች እና የፀጥታ አካላት ተሳትፈዋል።

ነዋሪዎቻችንን ከአደጋ መከላከል ቀዳሚ ስራችን ነው - ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይዛሬ ከተማ አቀፍ የጎርፍ መከላከልና የአደጋ ዝግጁነት ንቅናቄ በአቃቂ ክፍለ ከተማ ተጀምሯል። በቦታው ተገኝ...
23/06/2026

ነዋሪዎቻችንን ከአደጋ መከላከል ቀዳሚ ስራችን ነው - ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይ

ዛሬ ከተማ አቀፍ የጎርፍ መከላከልና የአደጋ ዝግጁነት ንቅናቄ በአቃቂ ክፍለ ከተማ ተጀምሯል። በቦታው ተገኝተው ንቅናቄውን ያስጀመሩት የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ ንቅናቄውን በአቃቂ ቃሊቲ ጀምረን በሁሉም ለጎርፍ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ዘላቂ ልማት እንዲኖር በማድረግ ነዋሪዎቻችንን ከአደጋ መከላከል የከተማ አስተዳደሩ ቀዳሚ ስራ ነው ብለዋል።

ከጥቂት ዓመታት በፊት በጎርፍ ምክንያት ይከሰት የነበረው አደጋ አሳዛኝ እንደነበር እና እንደዚህ ዓይነቱን አደጋ ቀድሞ መከላከል ተገቢ መሆኑን የገለፁት ምክትል ከንቲባው አዲስ አበባ የልማት አብዮት ውስጥ የገባች እንዲሁም ብዙ ስራዎችን እያሳካች የምትገኝ ከተማ መሆኗን ገልፀዋል። በመሆኑም ከዚህ ቀደም ያጋጥሙ ለነበሩ ችግሮች መፍትሔ በመስጠት ከችግር ነፃ የሆነ አከባቢ መፍጠር የአስተዳደሩ አጀንዳ መሆኑን ገልጸዋል።

መንግስት ከሚያደርገው ጥረት በተጨማሪ ነዋሪዎች ከተማቸውን የማልማት፣ ወንዞችን የመንከባከብና በአከባቢያቸው ያሉ የወንዝ መፍሰሻ ቦይዎችን በማጽዳት በቆሻሻ እንዳይዘጉ የማድረግ ሃላፊነት እንዳለባቸው ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አሳስበዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ የከተማ አስተዳደሩ የአደጋ ተጋላጭነት ሁኔታን በአግባቡ አጥንቶ ዘላቂ ምላሽ መስጠት የሚያስችል ስራዎችን በመስራት ላይ እንደሚገኝ ገልጸው የወንዝ ዳርቻ አከባቢዎቻችን ውበት ሆነው ሰዎች የሚዝናኑባቸው እንጂ የአደጋ ስፍራዎች መሆን የለባቸውም በሚል የተጀመረው ስራ ውጤት እያመጣ ነው ብለዋል።

ሥራ አስኪያጁ በዚህ ክረምት በሚሰሩ ስራዎችም የአደጋ ተጋላጭነትን በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስ መታቀዱን ተናግረዋል።
አደጋ ቢያጋጥምም እንኳን በራስ አቅም ተጎጂዎችን ማቋቋምና ሰብዓዊ ድጋፍ ማድረግ የሚያስችል ስራ በሁሉም ክፍለ ከተሞች የአደጋ ስጋት የክምችት መጋዘኖችን የመገንባት ስራ መጠናቀቁን ኢንጂነር ወንድሙ ገልጸዋል።

‎“ኢትዮጵያ ታከናውናለች” በተሰኘው ብሔራዊ ጉባኤ ላይ በመገኘቴ ታላቅ ክብር ይሰማኛል።‎‎ “ከለውጥ ወደ ዘላቂ ሽግግር” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ባለው ጉባኤ ላይ፣ በየደረጃው የተጓዝንበት...
23/06/2026

‎“ኢትዮጵያ ታከናውናለች” በተሰኘው ብሔራዊ ጉባኤ ላይ በመገኘቴ ታላቅ ክብር ይሰማኛል።

‎ “ከለውጥ ወደ ዘላቂ ሽግግር” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ባለው ጉባኤ ላይ፣ በየደረጃው የተጓዝንበትንና አሁን የደረስንበትን መንገድ መለስ ብዬ እንድቃኘው አድርጎኛል። ሀገራችን በራሷ አቅም ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በመገንባት፣ ያልተሞከሩ ግዙፍ ልማቶችን በማከናወን በየጊዜው ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገረች ትገኛለች። እነዚህ ሁሉ በአጋጣሚ የተገኙ ድሎች ሳይሆኑ በመደመር መንፈስ ላይ ተመስርተው፣ ዘላቂ ለውጥ የሚመጣው በጋራ በመቆም ነው፤ በሚል ጽኑ እምነት የተወሰዱ፣ በቆራጥ ውሳኔዎች የተገኙ ውጤቶች ናቸው።

‎የጀመርናቸው ለውጦች በራሳቸው የመጨረሻ ግብ አይደሉም፤ ይልቁንም ከእኛ በኋላ ለሚመጡት ተከታታይ ትውልዶች የምንጥለው ጠንካራ መሠረት ነው።
‎ሀገርን መገንባት በአንድ ትውልድ ብቻ የሚያበቃ ሳይሆን የሁላችንም የጋራና ቀጣይነት ያለው ሥራ በመሆኑ፤ በዚህ ጽኑ እምነት እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ይህንን መንፈስ ይዞ ወደፊት እንዲጓዝ፣ የተቀበለውን ወረት አግዝፎ ይበልጥ ወደ ላቀ ከፍታ እንዲያመራ ጥሪዬን አቀርባለሁ!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ

ከአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ የተላለፈ የምስጋና መልዕክትየህዝብ ድምጽ አሸንፏል፤ ኢትዮጵያ በልጆቿ ጸንታለች!መላው  የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ዴሞክራሲን በማፅናታች...
22/06/2026

ከአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ የተላለፈ የምስጋና መልዕክት

የህዝብ ድምጽ አሸንፏል፤ ኢትዮጵያ በልጆቿ ጸንታለች!

መላው የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ዴሞክራሲን በማፅናታችሁ እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን!

የተከበራችሁ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ለፓርቲያችን ብልፅግና የሰጣችሁት ድምፅ የቃል ኪዳናችን ማሰሪያ በማድረግ የጣላችሁብን አደራ በላቀ ስኬት ለመመለስ እንተጋለን።

ይህ ምርጫ ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት የሀገራችን የዴሞክራሲ ጉዞ ወደ አዲስ ምዕራፍ የተሻገረበት ደማቅ የታሪካችን አካል ሆኖ ተመዝግቧል ።

በመዲናችን አዲስ አበባ በተደረገው የከተማ ምክር ቤት ምርጫ፣ ፓርቲያችን ብልፅግና ከጠቅላላው 158 መቀመጫዎች ውስጥ 134፤ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከ23ቱ የምክር ቤት መቀመጫዎች ውስጥ 20 መቀመጫዎችን በማግኘት የህዝብን ሙሉ አመኔታና አብላጫ ድምፅ በማግኘት አሸንፏል።

በሌላ በኩል ከ158 የከተማ ምክርቤት መቀመጫዎች ውስጥ 11 የተፎካካሪ ፓለቲካ ፒርቲዎች 23 የግል ተወዳዳሪ 1 ወንበሮች ያገኙ ሲሆን አዲስ አበባ ከምትወከልበት ከ23ቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎች ውስጥ
የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች 2 እንዲሁም የግል ተወዳዳሪ 1 ወንበሮችን ማሸነፍ ችለዋል።

ይህ እጅግ አስደናቂ ዉጤት እያደገ የመጣዉን የሰለጠነ የፖለቲካ ባህል እና የህዝብን ፍትሐዊ ዳኝነት ያሳያል። በጥቅሉ ፓርቲያችን በአብላጫ ድምፅ ቢያሸንፍም በዋናነት ያሸነፈዉ መላው የመዲናችን ነዋሪ ፣ ሰላም እንዲሁም ልማት እና እያደገ የመጣዉ የዴሞክራሲ ባህል ነው።

የተከበራችሁ መራጮቻችን ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከለሊት እስከ ለ‍ሊት በምርጫ ጣቢያዎች በመሰለፍ ምርጫው ነጻ፣ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ አግባብ እንዲጠናቀቅና ለብልፅግና ፓርቲ አብላጫ ድምፅ በመስጠት እምነት ለጣላችሁብን ለቀጣዩ ጉዟችንም የህዝብ አደራን በአግባቡ እንድንወጣ አቅማችን ለሆናችሁ በሙሉ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

በቀጣዩ የ5 ዓመቱ ጉዟችን ህዝባችን የሰጠንን ታላቅ አደራ በገባነው ቃል መሠረት ሌት ተቀን በመሥራት፣ የከተማችንን ብሎም የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግናን እውን ለማድረግ ተግባራዊ ምላሽ እንሰጣለን።

በተለመደው መልኩ ከህዝባችን ጋር በመተባበር በከተማችን የተጀመረውን የለውጥ ጉዞን በማሳለጥ የህዝባችን ኑሮ እና አኗኗር ለመለወጥ ያለንን ቁርጠኝነት ዳግም እናረጋግጣለን!

ይህ ድል የብልፅግና ፓርቲ ብቻ ሳይሆን የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ድል ነው!

ዲሞክራሲን እያፀናን ልዩነቶቻችንን በሰለጠነ መንገድ እያስተናገድን፣ በአንድነትና በፓርቲያችን መሪነት ወደ ላቀ ከፍታ እንጓዛለን።

ምርጫውን በማስፈጸም፣ በመታዘብ ፣ ሰላምን በማስጠበቅ ዉጤታማ ስራ የሰራችሁ እንዲሁም የኢትዮጵያን እውነት ለዓለም በማሳየት ረገድ የሀገሪቱን ህግና ስርዓት ተከትላችሁ የዘገባችሁ የሚዲያ ተቋማት ከሁሉ በላይ የሀገራችሁ ዴሞክራሲ አንድ እርምጃ ወደፊት እንዲራመድ የበኩላችሁን የተወጣችሁ በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ!

በመጨረሻ በሀገር አቀፍም ሆነ በከተማ ደረጃ የፖለቲካ ልዩነት ወደ ፖሊሲ አማራጭ በማሳደግ በዚህ ምርጫ ላይ ተፎካክራችሁ በህዝብ ይሁንታ ወንበር በማግኘት የአዲስ አበባ ምክርቤት አባል ለመሆን የበቃችሁ የ11 ፖለቲካ ፓርቲዎች ወኪሎችና አንድ የግል ተወዳዳሪ በሰላማዊ መንገድ ህዝባችሁን ለማገልገል ዕድል በማግኘታችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንወዳለን ።

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና በልጽጋ ለዘላለም ትኑር! እንኳን ደስ አላችሁ

የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓ

በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል የ2018 የአረንጓዴ አሻራ የጉድጓድ ቁፋሮ መርሀግብር ተጀመረ።በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 አስተዳደር የክረምቱን የአረንጓዴ...
22/06/2026

በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል የ2018 የአረንጓዴ አሻራ የጉድጓድ ቁፋሮ መርሀግብር ተጀመረ።

በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 አስተዳደር የክረምቱን የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀግብር በስኬት ለመወጣት የሚያስችል የጉድጓድ ቁፋሮ ማስጀመሪያ መርሃግብር በዛሬው ዕለት በታላቅ ንቅናቄ ተካሂዷል።

መርሃግብሩ "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል የተመራ ሲሆን፥ የወረዳው አመራሮች፣ የወረዳዉ ነዋሪዎች፣ ወጣቶችና የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።

ወረዳ 09 አስተዳደር በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር በርካታ ችግኞችን ለመትከል ያቀደ ሲሆን፥ የዛሬው የጉድጓድ ቁፋሮ ማስጀመሪያ መርሃግብርም ለቀጣዮቹ ተከታታይ የአረንጓዴ ልማት ስራዎች ስኬት ትልቅ መነቃቃትን የፈጠረ መሆኑ ተመላክቷል።

የካ ወረዳ 09 ኮሙኒኬሽን፣ሰኔ 15/2018

Address

Addis Ababa
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yeka werda 09 Communication/የካ ወረዳ 09 ኮሙኒኬሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share