የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት Addis Ababa City Council

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት Addis Ababa City Council የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የከተማው ህግ አውጪ ተቋም ነው!
(1)

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ቡዜና አልከድር በየካ ምርጫ ጣቢያ በመገኘት ድምጽ ሰጥተዋል::የተከበሩ አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ቡዜና ከምርጫው በኃላ እንደተናገሩት የምመር...
01/06/2026

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ቡዜና አልከድር በየካ ምርጫ ጣቢያ በመገኘት ድምጽ ሰጥተዋል::

የተከበሩ አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ቡዜና ከምርጫው በኃላ እንደተናገሩት የምመርጠው ለራሴ ብቻ ሳይሆን ለሀገርና ለትውልድ ግንባታ አዎንታዊ ሚና መጫወት ስላለብኝ ነው ብለዋል::

!

24/05/2026
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል በምስል፦
23/05/2026

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል በምስል፦

"የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታና የወጣቶች ሚና" በሚል ርዕሰ ጉዳይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ከየካ ክፍለ ከተማ ምክርቤት ጋር በመሆን "የዲሞክራሲ ስርዓት...
16/05/2026

"የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታና የወጣቶች ሚና" በሚል ርዕሰ ጉዳይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ከየካ ክፍለ ከተማ ምክርቤት ጋር በመሆን "የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታና የወጣቶች ሚና በሚል ለየካ ክፍለ ከተማ ወጣቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።

በመድረክ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ምክርቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ቡዜና አልከድር ሀገር የምትገነባው በወጣቶች መሆኑን እና የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሂደት ውስጥ ወጣቶች የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው መንግስት ወጣቶች በተለያዩ ዘርፎች ተጠቃሚ የሚሆኑበት በርካታ ተግባራትን በመከወን ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

"የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታና የወጣቶች ሚና" በሚል ርዕሰ ጉዳይ በደ/ር ዋጋሪ ነገሪ ሰፋ ያለ የግንዛቤ ማስጨበጫ ፅሁፍ ቀርቦ ውይይት ተደርጏል ።

ምክር ቤቱ የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እና የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ የሥራ አመራር  ቦርድ አባላት  ዕጩዎች  ሹመትን  አጸደቀ።የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉ...
08/05/2026

ምክር ቤቱ የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እና የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት ዕጩዎች ሹመትን አጸደቀ።

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ የምክር ቤቱን የፍትሕና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እና የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ የሥራ አመራር ቦርድ አባላትን ዕጩዎች ሹመት አጽድቋል፡፡

የተከበሩ አቶ በላይ ደጀን በምክር ቤቱ የፍትሕና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆነዉ ተሹመዋል፡፡

የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክን አቅም እና ተደራሽነት ይበልጥ ለማጠናከር በቀረበዉ ሹመት መሰረት፡

1ኛ. ክቡር አቶ ሞገስ ባልቻ - የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ

2ኛ. የተከበሩ ረ/ፕ ነብዩ ባዬ - የሥራ አመራር ቦርድ አባል

3ኛ. አቶ ሠለሞን ካሳ - የሥራ አመራር ቦርድ አባል

4ኛ. የተከበሩ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ - የሥራ አመራር ቦርድ አባል

5ኛ. ሚኤሳ ኤሌማ (ዶ/ር) - የሥራ አመራር ቦርድ አባል

6 ኛ. ወ/ሮ ዘሃራ መሃመድ - የሥራ አመራር ቦርድ አባል ሆነዉ ተሹመዋል፡፡

3ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባዔ የተለያዩ አጀንዳዎችን እና ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቀቀ። በዚህም መሰረት:-- አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ - በምክትል...
08/05/2026

3ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባዔ የተለያዩ አጀንዳዎችን እና ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቀቀ።

በዚህም መሰረት:-
- አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ - በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ
- አቶ አሰግደዉ ኃ/ጊዮርጊስ - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፓርት ቢሮ ኃላፊ
- አቶ ሰለሞን ዲባባ - የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሹመዋል::

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉብኤውን    ማከናወን ጀምሯል። ምክር ቤቱ  በዛሬ ውሎው የከተማ  አስተዳደሩ ከንቲባ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥ...
08/05/2026

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉብኤውን ማከናወን ጀምሯል።

ምክር ቤቱ በዛሬ ውሎው የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡ ሲሆን እንዲሁም በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ የሚያጸድቅ ይሆናል።

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባላት በመዲናዋ የተገነቡ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የምክር ቤት አባላት አዲስ አበባን እንደ ስሟ አዲስ እና ውብ ለማድ...
08/05/2026

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባላት በመዲናዋ የተገነቡ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የምክር ቤት አባላት አዲስ አበባን እንደ ስሟ አዲስ እና ውብ ለማድረግ የተሰራው ስራ እጅግ እንዳስደሰታቸው ገልጸው በዚህም መዲናዋን ለነዋሪዎቿ ምቹ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል::

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባላት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ ከመጀመሩ በፊት በከተማዋ  የተገነቡ የልማት ስራዎች በመጎብኘት ላይ ይገኛሉ::
08/05/2026

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባላት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ ከመጀመሩ በፊት በከተማዋ የተገነቡ የልማት ስራዎች በመጎብኘት ላይ ይገኛሉ::

Address

ካዛንቺስ ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ወደ ውስጥ ገባ ብሎ ECA ጎን
Addis Ababa
55698

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት Addis Ababa City Council posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት Addis Ababa City Council:

Share