19/03/2026
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል አደረሳችሁ ፡፡
/ምክር ቤት ኮሚኒኬሽን 10/07/2018 ዓ.ም/
በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ሀይማኖታዊ ስነ - ስርዓት የሚከበረው የዒድ አልፈጥር በዓል የሠላም ፣ የፍቅር ፣ የደስታና የመረዳዳት በዓል እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡
ሕዝበ ሙስሊሙ በታላቁ የረመዳን ጾም ወቅት ያሳየውን የመረዳዳትና የመተዛዘን ኢትዮጵያዊ እሴት በማስቀጠል ለተቸገሩና የኢኮኖሚ አቅማቸው ዝቅተኛ ለሆኑ የሕብረተሰብ ክፍሎች ያለዉን በማካፈል በዓሉን በአንድነት መንፈስ በደስታና በፍቅር ልናከብር ይገባል ።
ዒድ ሙባረክ !
የተከበሩ አቶ መኩሪያ ጉርሙ
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ