31/05/2026
እ.ኤ.አ ከጁን 1 እስከ 10/2026 (ግንቦት 24 እስከ ሰኔ 3/2018 ዓ.ም) የሚኖረው የአየር ሁኔታ በውሃ ዘርፍ ላይ ሊያሳድር የሚችለው ተፅዕኖ
//////////
በሚቀትሉት የጁን የመጀመሪያዎቹ አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገሪቱ ተፋሰሶች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው የገጸምድር የውሃ ፍሰት እንደሚኖራቸው ይጠበቃል። በመሆኑም ከሚጠበቀው የአየር ሁኔታ ጋር ተያይዞ የሚኖሩ መልካም አጋጣሚዎችን ለመጠቀምና የሚጠበቁ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ለመቀነስ ከታች የቀረቡትን ቦታ ተኮር የውሃ ሚቲዎሮሎጂ ምክረ ሀሳብ ከወዲሁ ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡