30/05/2026
የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ በዞኑ ከ1 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ የካፒታል ወጪ እየተገነባ ያለውን የዞኑ የአስተዳደር ህንፃ ያለበት ደረጃን ምልከታ አደረጉ!!
ግንቦት 22/2018 ዓ/ም
በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ በ2000 ሺህ ካሬ ሜትር ላይ ያረፈውና (B+G+9) የሆነው ግዙፍ ህንፃ በተያዘው በጀት ዓመት ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል!!
የመስክ ምልከታው ዋና ዓላማ ህንፃው እንዲጠናቀቅ ከተያዘለት ጊዜ አንፃር የደረሰበትን ደረጃን ከመከታተል ባሻገር በባለፉት ጊዜያት የተሰጡ አስተያየቶች ስለመታረማቸው ማረጋገጥ ላይ ያተኮረ መሆኑ ተመላክቷል።
ህንፃው የዘመኑ የህንፃ ቴክኖሎጂ በደረሰበት ደረጃና መጪውን ጊዜ ባለመ መልኩ እየተገነባ ያለ ሲሆን እስካሁን 85 በመቶ የሚሆነው ዋናው ስራ መጠናቀቁን እና 74 በመቶ ክፍያ መፈፀሙን ተጠቁሟል!!
ህንፃው ሲጠናቀቅ የዞኑ አብዛኛው መስሪያ ቤቶችን መያዝ የሚችል ሲሆን፣ የተገልጋዮችን እንግልት ከመቀነስና የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ከማዘመን አንፃር ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል!!
ህንፃው በውስጡ ከ160 ቢሮዎች ባሻገር 8 ደረጃቸውን የጠበቁ የስብሰባ አዳራሾች፣ዲጂታል የእሳት አደጋ መከላከያ፣ሁለት ዘመናዊ ሊፍቶች፣ግሪነሪዎች፣የዳታ ማዕከል፣ ካፊቴሪያዎች፣ የህፃናት ማቆያና ሌሎችም አገልግሎቶች የሚኖሩት ሲሆን የሊፍት አገግሎትም የሚገጠምለት እንደሆነ ተመላክቷል!!
ከዋናው ህንፃም በተጨማሪ በሁለተኛ ፌዝ ዘማናዊ ቴክኖሎጂዎች የተገጠሙለትና ከአንድ ሺህ ባላይ ሰዎችን የሚይዝ አዳራሽም እንደሚሰራ ተማላክቷል።
የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በጉብኝቱ ወቅት እንዳሉት በበጀት ዓመቱ የዞኑ መንግስት ከሚያስፈፅማቸው ከፍተኛ ፕሮጀክቶች አንዱና ቀዳሚው ነው!!
የዞኑ አብዛኛው አገልግሎት መስጫ ቢሮዎች ደረጃቸውን ያልጠበቁ፣ላአገልጋይም ሆነ ተገልጋይ ምቹ ያልሆኑ፣ ተበታትነው ያሉ፣ ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር የማይሄዱና ጉራጌን የማይመጥኑ መሆናቸውን የገለፁት አቶ ላጫ እየተሰራ ያለው ህንፃ ግን እነዚህን ችግር የሚቀርፍ መሆኑን አስገንዝበዋል!!
የዞናችን የፕሮጀክቶች የማስፈፀም አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል ያሉት ክቡር አስተዳዳሪው ለዚህም የአመራሩ ተከታታይነት ያለው የአካል ምልከታና ግብረ መልስ አስተዋፅዎ ማበርከቱን ገልፀዋል!!
ግንባታዎች በፍጥነት ማለቃቸው ብቻ ሳይሆን ጥራትና የሚመጣውን ዘመን ቴክኖሎጂን ሊሸከሙ የሚችሉ ስለመሆናቸው ልዩ ትኩረት ይሻሉ ያሉት አቶ ላጫ ችግሮች እንዳይገጥሙ ከመነሻው ጀምሮ መከታተል ትርጉም አለው ብለዋል።
በመስክ ምልከታው የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ እና የጉራጌ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ናስር ሀሰን ጨምሮ ሌሎች የዞኑ ከፍተኛ አመሮች ተሳትፈዋል!!