በጉራጌ ዞን የእኖር ኤነር መገር ወረዳ መንግስት ኮምንኬሽን ጉ/ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • በጉራጌ ዞን የእኖር ኤነር መገር ወረዳ መንግስት ኮምንኬሽን ጉ/ጽ/ቤት

በጉራጌ ዞን የእኖር ኤነር መገር ወረዳ መንግስት ኮምንኬሽን ጉ/ጽ/ቤት ዓላማችን የመንግስት ፖሊሲ እና ስትራቴጂዎችን ለህብረተሰቡ ማሳወቅ፣ ወቅታዊ አቋሞችን መግለጽ፣

ነሀሴ 24/2018 ዓ.ምበእኖር ኤነር መገር ወረዳ "አንድም ተማሪ በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ከትምህርት ገበታው ውጭ አይሆንም!" በሚል መሪ ቃል በክረምት በጎ ፈቃድ የተሰበሰበውን የተማሪዎች...
30/08/2026

ነሀሴ 24/2018 ዓ.ም
በእኖር ኤነር መገር ወረዳ "አንድም ተማሪ በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ከትምህርት ገበታው ውጭ አይሆንም!" በሚል መሪ ቃል በክረምት በጎ ፈቃድ የተሰበሰበውን የተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።

በወረዳው ለጓረባ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለ40 አቅመ ውስንነት ያለባቸው ተማሪዎች የአካባቢው ተወላጅ በሆኑት በአቶ ግርማ ተክሌ እና በወይዘሮ ውድነሽ ታደሰ እንዲሁም በቤተሰቦቻቸው 40 ደርዘን ደብተር ፣ እስክሪብቶ እርሳስ ፣ ላፒስ፣ መቅረጫ እና የስዕል ደብተር ተበርክቶላቸዋል።

በድጋፍ ርክክቡ ላይ የተገኙት የእኖር ኤነር መገር ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ኤሊያስ ሸምሱ የትምህርት ቁሳቁስ እርዳታው ህፃናትን በትምህርት ቁሳቁስ ችግር ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው እንዳይስተጓጎሉ እና ትምህርታቸውን በእኩልነት መከታተል እንዲችሉ በማሰብ ነው ብለዋል።

የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በማህበረሰቡ የድጋፍ መስክ አገልግሎት የተማሪዎች የመማሪያ ቁቁሳቁስ የደብተር እስክሪብቶ አሰባሰብ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ አቶ ኤሊያስ ተናግረዋል።

የተደረጉት የትምህርት ቁሳቁሶቹ ለተማሪዎች በወቅቱ እንዲደርሱና በትምህርት ጉዟቸው የሚያጋጥማቸውን የመማሪያ ቁሳቁስ እጥረት ለማቃለል የሚያግዙ ናቸው ብለዋል።

እንደዚህ ያሉ የበጎ አድራጎት ተግባራት በማህበረሰቡ ውስጥ የእርዳታ ባህልን ለማጎልበት እና ተማሪዎችን ለትምህርት ለማበረታታት ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለው ገልፀዋል።

በመሆኑም ‎ይህ በጎ ተግባር ሊበረታታ የሚገባና ትልቅ የህሊና እርካታን የሚሰጥ በመሆኑ ለዚህ ሰናይ ተግባር ላበረከቱ አካላት በትምህርት ጽ/ቤት ስም አቶ ኤሊያስ አመስግነዋል።

 #የሳምንቱ  #አበይት  #ዜናዎቻችንነሀሴ 24/2018 ዓ.ምየትምህርት ጥራትንና የተማሪዎችን የትምህርት ውጤት ለማሻሻል በክረምት ወራት የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት በትኩረት እየተሰጠ መሆ...
30/08/2026

#የሳምንቱ #አበይት #ዜናዎቻችን
ነሀሴ 24/2018 ዓ.ም

የትምህርት ጥራትንና የተማሪዎችን የትምህርት ውጤት ለማሻሻል በክረምት ወራት የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት በትኩረት እየተሰጠ መሆኑ ተገለጸ።

በእኖር ኤነር መገር ወረዳ የ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት በጎ ፍቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካማ ቤት ግንባታ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በእኖር ኤነር መገር ወረዳ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገርና የሚገጥሙ ችግሮችን በራስ አቅም ለመወጣት እየተሰራ መሆኑን ተገለጸ።

በዘንድሮ የክረምት ወራት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ላይ አመርቂ ሥራዎች መከናወናቸውን የጉራጌ ዞን የበጎ ፍቃድ ቴክኒክ ኮሚቴ አስታወቀ።

አመራሩ የውጤታማነት አቅሙን በማላቅ የመንግስትና የፓርቲ ተግባራት ውጤታማነትን ይበልጥ ማረጋገጥ እንዳለበት ተገለጸ።

የእኖር ኤነር መገር ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት የላቀ አፈፃፀም ውጤት ላስመዘገቡት ተቋማት፤ ቀበሌያትና ፈፃሚ አካላት የእውቅናና ሽልማት መርሃ ግብር አካሄደ።

በየደረጃው የሚገኙ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ለተገልጋዮች የሚሰጡትን አገልግሎት በማሻሻል በወረዳም ሆነ በሀገር ደረጃ የሚጠበቁ ትልልቅ ስኬቶችን በተጨባጭ ለማስመዝገብ በትኩረት መስራት እንደሚገባቸው ተገለፀ።

በእኖር ኤነር መገር ወረዳ በኤነር ገዳም ቀበሌ በአርሶ አደሮች ማሳ እየለማ የሚገኘው የበርበሬ ምርት የተሻለ ውጤት እንዳለው ተገለፀ።

በእኖር ኤነር መገር ወረዳ በ2018/19 ምርት ዘመን በኧገንዳ ታርቤ ቀበሌ በመስመር የለማ የስንዴ ማሳ በጥሩ ቁመና እንደሚገኝ ተገለፀ።

ነሀሴ 23/2018ዓ.ም=========በጉራጌ ዞን እኖር ኤነር መገር ወረዳ ውስጥ ከሚገኙና እስካሁን ተረስተው ይሁን ተደብቀው ከቆዩት አዳዲስና ማራኪ መስህቦች መሀከል በጥቂቱ ☞ ጊችን ፏፏቴ ...
29/08/2026

ነሀሴ 23/2018ዓ.ም
=========በጉራጌ ዞን እኖር ኤነር መገር ወረዳ ውስጥ ከሚገኙና እስካሁን ተረስተው ይሁን ተደብቀው ከቆዩት አዳዲስና ማራኪ መስህቦች መሀከል በጥቂቱ

☞ ጊችን ፏፏቴ

ፏፏቴው በእኖር ኤነር መገር ወረዳ በላንካ ቶሬ ቀበሌ በጊችን መንደር ውስጥ በዚኪር ወንዝ ላይ የተንጣለለ የሚገኝ ሲሆን እስካሁን ትኩረት ተሰጥቶት የለማ ባይሆንም ተፈጥሮ ያደለውን በርካታ ፀጋዎች በመጎናፀፍ እራሱ ለራሱ ትኩረት በመስጠት የተፈጥሮ ምንነቱን ጠብቆ በመንጎማለል ላይ የሚገኝ ቅርስ ነው፡፡

ፏፏቴው ልዩ ከሚያደርጉት መካከል፡-
ፏፏቴው በተፈጥሮ ድንጋይ የተከበበ መሆኑንና በፏፏቴው ዙሪያ የሚገኙ የተፈጥሮ ደኖች ለፏፏቴዉ ልዩ ድምቀት የሰጡ መሆናቸው፡፡

ፏፏቴው በተፈጥሮደን የተከበበ መሆኑና በደኑ ውስጥ ደግሞ የተለያዩ ዕድሜ ጠገብ የሆኑ አገር በቀል ዛፎች ይገኙበታል፡፡

ፏፏቴው የወረደው ውሀ ታች መሬት ላይ ተንሳፎ ሲታይ እጅግ ማራኪ መሆኑና እጅግ ጥልቅ እንደሆነ ይታወቃል፡፡

ከፏፏቴዉ ለመጎብኘት የንቅፍት የሚሆኑ ነገሮች ፏፏቴው እጅግ በጣም ገደላማ መሆኑን ፣በተለያዩ የጫካ ቁጥቋጦዎች የተሸፈነ መሆኑንና ይህ ቦታ የጫካ ቁጥቋውን ክፍት ቢደረግ ለወረዳች ትልቅ የቱሪስት መስህብ መሆን ይችላል!!

የተፈጥሮ ድንቅ ፀጋ ፏፏቴ!!

መረጃው የወረዳው መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በጉራጌ ዞን በህብረተሰብ ተሳትፎ  ከ37 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የታተሙ መጽሀፍትን ለወረዳዎች አስረከቡ ነሐሴ 23/2018 የማዕከላዊ ኢትዮጵ...
29/08/2026

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በጉራጌ ዞን በህብረተሰብ ተሳትፎ ከ37 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የታተሙ መጽሀፍትን ለወረዳዎች አስረከቡ

ነሐሴ 23/2018 የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) በጉራጌ ዞን በህብረተሰብ ተሳትፎ ከ37 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የታተሙ መጽሀፍትን ለወረዳዎች አስረክበዋል

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት አዲሱ የትምህርት እና ስልጠና ፖሊሲ እና ስርዓተ ትምህርት ከተሻሻለ ወዲህ የአዳዲስ መጽሀፍት ህትመት እየተካሄደ ነው ብለዋል።

በሁለተኛ ደረጃ ባሉት ትምህርት ቤቶች ትምህርት ማኒስቴር ከቅድመ አንደኛ እስከ 8ኛ ክፍል መጽሀፍት የማቅረብ ኃላፊነት የክልሎች ድርሻ ስለመሆኑም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

የመጽሀፍት አቅርቦት ከፍተኛ ሀብት ይጠይቃል ያሉት አቶ አንተነህ በክልሉ መንግስት አቅም ብቻ መሸፈን ስለማይቻል በሁሉም አካባቢዎች ህብረተሰቡን በማሳተፍ እየተሰራ ነው ብለዋል።

አርሶ አደሩን፣የንግዱን ማህበረሰብ፣ዲያስፖራውን፣ክልሉ እና ከክልሉ ውጪ ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ መጽሀፍት የማሟላት ስራ ተግባራዊ መደረጉን ጠቅሰዋል።

በክልሉ በመካከለኛ ደረጃ 1ለ5 የመጽሀፍት ጥምርታ ማዳረስ ተችሏል ያሉት አቶ አንተነህ ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል ደግሞ 1ለ3 መድረሱን አብራርተዋል።

በክልሉ 1መጽሀፍ ለአንድ ተማሪ ንቅናቄ በጉራጌ ዞን ከ227 ሺ በላይ መጽሀፍት የማሰራጨት ስራ ተግባራዊ መደረጉን ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በአብነት ጠቅሰዋል።

በክልሉ በ2018 በጀት ዓመት ከአጋር አካላት ከ 2 ነጥብ 6 ሚሊየን በላይ መጽሀፍት ጥራቱን የጠበቀ የመጽሀፍት ህትመት ማሰራጨት መቻሉን ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል።

የመማር ማስተማሩን ስራ ስኬታማ ለማድረግ የክልሉ መንግስት ለመጽሀፍት ህትመት ከፍተኛ ሀብት መድቦ እየተሰራ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።

የመንግስትን፣የህዝብን ብሎም የአጋር አካላትን አቅም በመጠቀም የመጽሀፍት ተደራሽነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን አቶ አንተነህ አስረድተዋል።

በዘርፉ እየተደረገ ያለው ጥረት የትምህርትን ጥራት እና የተማሪዎችን ውጤት በማሻሻል ረገድ ጉልህ አበርክቶ እንዳለውም ጠቅሰዋል።

በክልሉ በ2019 የትምህርት ዘመን አንድ መጽሀፍ ለአንድ ተማሪ ኢንሼቲቭ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የተናገሩት አቶ አንተነህ ለዚህም መላው ህዝብ የጀመረውን ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። መረጃው የክልሉ መ/ኮ ነው።

ነሀሴ 23/2018 ዓ.ምበየደረጃው የሚገኙ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ለተገልጋዮች የሚሰጡትን አገልግሎት በማሻሻል በወረዳም ሆነ በሀገር ደረጃ የሚጠበቁ ትልልቅ ስኬቶችን በተጨባጭ ለማስመዝገብ ...
29/08/2026

ነሀሴ 23/2018 ዓ.ም
በየደረጃው የሚገኙ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ለተገልጋዮች የሚሰጡትን አገልግሎት በማሻሻል በወረዳም ሆነ በሀገር ደረጃ የሚጠበቁ ትልልቅ ስኬቶችን በተጨባጭ ለማስመዝገብ በትኩረት መስራት እንደሚገባቸው ተገለፀ።

የእኖር ኤነር መገር ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ፅ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት በስራ አፈፃፀማቸው የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ፈፃሚ ተቋማትና ባለሙያዎችን ለማትጋት የተዘጋጀ የዕውቅናና ሽልማት መረሃ-ግብር አካሄዷል።

በመረሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሰበ ካብቱ እንደገለፁት የዚህ ዕውቅናና ሽልማት ዋና ዓላማ የሰራተኞችን የስራ ተነሳሽነት ብሎም ዕውቀታቸውን ማሳደግ ነው ብለዋል።

የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ዋነኛ ዓላማ የህብረተሰቡን የእለት ተእለት ፍላጎት በታማኝነት እና በቀልጣፋ አሰራር ማርካት ነው ሲሉም አቶ አሰበ ተናግረዋል።

በመንግስት የሚቀረጹ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እቅዶች ስኬታማ ሊሆኑ የሚችሉት በየደረጃው ያሉ አስፈጻሚ አካላት ለተገልጋዩ ህዝብ የሚሰጡትን አገልግሎት በቁርጠኝነት ማሻሻል ሲችሉ ብቻ እንደሆነ አብራርተዋል።

ዋና አስተዳዳሪው አክለውም በወረዳችንም ሆነ በሀገር ደረጃ የተያዙ ትልልቅ የልማት ግቦችን በተጨባጭ ለማስመዝገብ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርአታችንን ማዘመን ግድ ይላል ብለዋል።

ተቋማት ለተገልጋዩ ህብረተሰብ የሚሰጡትን አገልግሎት አሰጣጥ ማዘመን እና ማሳለጥ የወቅቱ ቁልፍ ተግባር ሊሆን እንደሚገባ ያሳሰቡት አቶ አሰበ ሽልማቱ በሰራተኞችና በተቋማት መካከል ጤናማ ፉክክር የመፍጠር አቅሙ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።

የለውጥ መሳሪያዎችን በተግባር በማዋል የተጠናከረ ተቋማዊ አደረጃጀት በመፍጠርና በስታንዳርድ መሠረት የተሻለ አገልግሎት በመስጠት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተቋማትና ባለሙያዎች የእውቅናና የሽልማት ፕሮግራምን በማጠናከር ማስቀጠል እንደሚያስፈልግም ዋና አስተዳዳሪው አስገንዝበዋል።

የእኖር ኤነር መገር ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ፅ/ቤት ኃላፊ ቀሲስ ሀብቴ በርጋ በበኩላቸው በወረዳው የሚገኙ የመንግስት ተቋማት የተሰጣቸውን ተልዕኮ በተገቢው እንዲወጡ የሰው ሀብት አስተዳደር ሥራዎች ትኩረት አግኝተው እንዲፈጸሙ እና የለውጥና የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ ፕሮግራሞች በተገቢው እንዲተገበሩ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የወረዳውን የልማት ሥራ ለማፋጠንና ህዝቡ የተሻለ አገልግሎት እንዲያገኝ ተቋማት የሚሰጡት አገልግሎት ቀልጣፋና ውጤታማ መሆን ይኖርበታል ብለዋል።

ሀላፊው አክለውም ለዚህም የሰው ሀብት አመራርን ማጠናከርና የሠራተኞችን አቅም ማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራበት ነው ሲሉም ተናግረዋል።

በተጨማሪም የፐብሊክ ሰርቪስ ሪፎርም ሥራዎች በተቋማት ውስጥ በተግባር እንዲውሉ ተቋማት በቅንጅት እንዲሰሩ እና የመልካም አስተዳደር መርሆች በተገቢው እንዲተገበሩ በቀጣይም ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል ብለዋል።

በ2018 በጀት ዓመትም የለውጥ መሳሪያዎችን ሥራ ላይ በማዋል የተሻለ ተቋማዊ አሰራር በመፍጠርና በስታንዳርድ መሠረት አገልግሎት በመስጠት ውጤታማ ሥራ ላከናወኑ ተቋማትና ባለሙያዎች እውቅናና ሽልማት መሰጠቱን ኃላፊው ጠቁመዋል።

እንዲህ ያሉ ውጤታማ ሥራዎችን ማበረታታት የሠራተኞችን ተነሳሽነት ከማሳደግ ባለፈ በተቋማት የሚሰጠውን አገልግሎት የበለጠ ለማሻሻል ያግዛል ብለዋል።

የተዘረጉ አደረጃጀቶች በሙሉ ተግባራትን በብቃትና በፍጥነት የምናሳልጥባቸው መሆን እንዳለባቸው ጠቁመው ለስራው ስኬታማነት የመረጃ ጥራትና ወቅታዊነትን በየጊዜው መመርመር እንደሚያስፈልግ ቀሲስ ሀብቴ አስረድተዋል።

በመርሃ ግብሩ ከምዘና ስርዓቱ ጋር በተያያዘ ተቋሙ ያከናወናቸው ዋና ዋና ተግባራት መነሻ ሪፓርት የቀረበ ሲሆን የሪፎርም መሳሪያዎች የቲም አደረጃጀት አሰራር ስርዓቱ መሠረት ተግባራዊ ለማድረግ እንዲሁም ሌሎች ተግባራት በትኩረት መሠራታቸው በቀረበው ሰነድ ተመላክቷል።

በመጨረሻም የ2018 በጀት አመት አፈፃፀም መነሻ ጥሩ ውጤት ያስመዘገቡ ተቋማትና ፈፃሚዎች እውቅናና ሽልማት የተበረከተ ሲሆን ከተቋማት 1ኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ገቢዎች ጽ/ቤት 3ኛ አስተዳደር ፅ/ቤት 4ኛ መንገድ ትራንስፖርት ፅ/ቤት 5ኛ ትምህርት ፅ/ቤት መሆናቸውን ተገልጿል።

ነሀሴ 23/2018 ዓ.ምየእኖር ኤነር መገር ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት የላቀ አፈፃፀም ውጤት ላስመዘገቡት ተቋማት፤ ቀበሌያትና ፈፃሚ አካላት የእ...
29/08/2026

ነሀሴ 23/2018 ዓ.ም
የእኖር ኤነር መገር ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት የላቀ አፈፃፀም ውጤት ላስመዘገቡት ተቋማት፤ ቀበሌያትና ፈፃሚ አካላት የእውቅናና ሽልማት መርሃ ግብር አካሄደ።

በ2018 በጀት ዓመት በፐብሊክ አሰራር መሰረት የተሻለ አፈጻጸም ላመጡ ለተቋማት፣ለቀበሌያት፣ ለፐብሊክ ሰርቪስ ባለሙያዎችና ስራ አስኪያጆች የዕውቀና ሰርተፊኬትና የዋንጫ ሽልማት የማበርከት መርሀ ግብር አካሂደዋል።

በመረሃ ግብሩ የእኖር ኤነር መገር ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሰበ ካብቱ እንኳን ደሰ አላችሁ በማለት በበጀት ዓመቱ በተሰጣቸው ኃላፊነት ተግተው በመሥራት የላቀ የሥራ ውጤት ያስመዘገቡ ፈፃሚ ባለሙያዎችንና ተቋማትን እንዲሁም ቀበሌዎች ማበረታታት ለሌሎችም አርአያ እንዲሆኑ ማድረግ እና በሥራ ቦታ የውጤታማነት ባህልን ማጠናከር መሆኑን ገልጸዋል።

ተቋማት ጎልተው እንዲወጡና በዞኑ ካሉ ወረዳዎች ተወዳዳሪና ተሸላሚ እንዲሆኑ አመራሩና ባለሙያው ተቋም ፈጥረው መስራት ይገባቸዋል ያሉ ሲሆን ወረዳው ካለው የሰራተኛ ቁጥር የሚመጥን ሞዴል የሆነ ስራ ሰርቶ ተወዳዳሪ ከመሆን አንፃር ከፍተኛ ጉለት በመሆኖሩ ለቀጣይ የተሻለ ስራ መስራት እንደሚጠበቅ ዋና አስተዳዳሪው አስረድተዋል።

ለውጥ መፍጠር የቻለ ተቋምና ባለሙያ ማበረታታትና እውቅና መስጠት ስላደረገው አበርክቶ ብቻ ሳይሆን ነገን በተሻለ አፈፃፀም ቁመና እንዲገኝ ማጎበዝም ነው ያሉት አቶ አሰበ ለቃለ መሐላችሁ ታምናችሁ ያገለገላችሁ ተሸላሚዎች በድጋሚ እንኳን ደስ አላቸው ብለዋል።

ነሀሴ 23/2018 ዓ.ምየእኖር ኤነር መገር ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማትና ባለሙያዎች የእውቅናና ሽልማት መርሀ ግብር እያካሄደ ይገኛል።...
29/08/2026

ነሀሴ 23/2018 ዓ.ም
የእኖር ኤነር መገር ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማትና ባለሙያዎች የእውቅናና ሽልማት መርሀ ግብር እያካሄደ ይገኛል።

የእኖር ኤነር መገር ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማትና ባለሙያዎች የእውቅናና ሽልማት መርሀ ግብር እያካሄደ ነው።

የእኖር ኤነር መገር ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ ቀሲስ ሀብቴ በርጋ በመክፈቻ ንግግራቸው እንዳሉት ዜጎች በመንግስት ላይ እምነት እንዲኖራቸው ከሚያደርጉ ጉዳዮች ቀልጣፋና ታአማኒነት ያለው አገልግሎት አሰጣጥ አንዱ ነው።

የመርሀ ግብር ዋንኛ ዓላማው በሰራተኞች መካከል የተፎካካሪነት መንፈስ በመፍጠር ለበለጠ ዉጤት ማነሳሳት እና ለተገልጋዮች ቀልጣፋና ስታንዳርድን መሠረት ያደረገ አገልግሎት ለመስጠት ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

በመርሃ ግብሩ በተጨማሪም የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀም ልምዶች የሚጋሩበት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የተከናወኑ ተግባራት የሚገመገሙበትና በቀጣይ የሚሻሻሉ ጉዳዮች ላይ የዕውቀት ልውውጥ የሚደረግበት መድረክ መሆኑን ተመላክቷል።

በመርሀ ግብሩ ላይ የጉራጌ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ ጥላሁን ሽምንሻ
የእኖር ኤነር መገር ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሰበ ካብቱ፣የእኖር ኤነር መገር ወረዳ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ማአሩፍ አብድል ሽኩር ጨምሮ ሌሎችም አስተባባሪ አካላት፣ መላው አመራሮች እንዲሁም የሁሉም ሴክተር መስሪያ ቤት የማኔጅመንት አባላት፣ የቀበሌ ሥራ አስኪያጆች፣የየተቋሙ የሕዝብ ክንፍ አባላት እና ተሸላሚ ፈፃሚዎች ተገኝተዋል።

ነሀሴ 22/2018 ዓ.ምአመራሩ የውጤታማነት አቅሙን በማላቅ የመንግስትና የፓርቲ ተግባራት ውጤታማነትን ይበልጥ ማረጋገጥ እንዳለበት ተገለጸ።‎‎በእኖር ኤነር መገር ወረዳ መደበኛና ወቅታዊ እን...
28/08/2026

ነሀሴ 22/2018 ዓ.ም
አመራሩ የውጤታማነት አቅሙን በማላቅ የመንግስትና የፓርቲ ተግባራት ውጤታማነትን ይበልጥ ማረጋገጥ እንዳለበት ተገለጸ።

‎በእኖር ኤነር መገር ወረዳ መደበኛና ወቅታዊ እንዲሁም በንቅናቄ የሚመሩ የመንግስትና የፓርቲ ተግባራትን በተመለከተ አጠቃላይ አመራር በተገኙበት የመስክ መልስ ግምገማ ተካሂዷል።

በግምገማው የክረምት በጎፍቃድ ስራ፣ከተረጅነት ወደ ምርታማነት እንሸቲቪ ትግበራ፣የተማሪዎች ምዝገባ ቅድመ ዝግጅት እና የመኸር የግብርና ስራ እንቅሰቃሴ ፣የአጎበር አጠቃቀም፣ህገ ወጥ የመሬት ወረራና ወቅታዊ ስራዎች እንዲሁም የፓርቲ አደረጃጀት ተግባራት ዙሪያ በጥልቀት ተገምግሟል።

በመድረኩ የተገኙት የእኖር ኤነር መገር ወረዳ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ማአሩፍ ከብድል ሽኩር እንደገለፁት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማጎልበት እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች በተጨማሪ የፓርቲና የመንግሥት ተግባራትን በውጤት መምራት አደረጃጀቶችን በመጠቀም መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

ዋና ተጠሪው አክለውም አመራሩ የመፈፀም አቅም በማላቅ የመንግስትና የፓርቲ ተግባራት ውጤታማነትን ይበልጥ ማረጋገጥ እንደሚገባ እና የድጋፍና ክትትል ስራውን ማጠናከር እንዳለበት ተናግረዋል።

አመራሮች ለሚያጋጥሙ ችግሮች መፍተሔ በመስጠት የአመራርነት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አቶ ማአሩፍ አንስተው በዚህም ወጥ በሆነ መልኩ የመንግስትና የፓርቲ ስራዎች ላይ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ አብራርተዋል።

በአጠቃላይ መድረኩ ጉድለትን የሚሞላ ጥንካሬን የሚያስቀጥልና ለቀጣይም በቅንጅትና በጥምር ተግባራትን በተሻለ ድጋፍና ክትትል ውጤታማ ስራ መስራት አስፈላጊ እንደሆነና ለቀጣይም የትኩረት አቅጣጫዎችን አቶ ማአሩፍ አስቀምጧል።

የእኖር ኤነር መገር ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽ/ቤት ሀላፊ መላኩ ሳህሌ እንዳሉት አመራሩ ተግባራትን አስተሳስሮ በመምራት እየመጣ ያለው ውጤት በማጠናከር የሚታዩ ክፍተቶችን ፈጥኖ በማረም ለውጥ ማምጣት እና ተግባሮችን አሳልጦ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።

አቶ መላኩ አክለውም አመራር በአመራር ቁርጠኝነት እና ውጤታማ አመራር ሰጪነት ለዜጎች ተጠቃሚነት የተቀመጡ ተግባራትን በተቀመጠላቸዉ የጊዜ ሰለዳ መሠረት ሊከዉን እንደሚገባ ገልጸዋል።

ወቅታዊ ተግባራትን በተቀናጀ መልኩ ተግባራዊ በማድረግ ዘላቂና ሁሉ አቀፍ ልማታዊ ለውጦች መመዝገብ እንዲችሉ በሀላፊነት መስራት እንደሚገባም አቶ መላኩ አመላክተዋል፡፡

በቀጣይ አመራሩ የነበረውን ተነሳሽነትና ቅንጅት በማስቀጠል ውጤት ተኮር ተልዕኮዎችን መፈጸም እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጧል።

በመጨረሻም ተግባራትን በቅንጅት በመስራት የማህበረሰቡን ተጠቀሚነት ማረጋገጥ የአመራር የዘወትር ተግባር በመሆኑ ሁሉም አመራር ያሉ ስኬቶችን በማስቀጠል በክፍተት የታዩ ተግባራት ላይ ርብርብ በማድረግ በሁሉም ተግባራት በውጤት በማጀብ ሊከናወን እንደሚገባ አቅጣጫ በማስቀመጥ መድረኩ ተጠናቋል።

ነሀሴ 22/2018 ዓ.ም===========በእኖር ኤነር መገር ወረዳ በኤነር ገዳም ቀበሌ በአርሶ አደሮች ማሳ እየለማ የሚገኘው የበርበሬ ምርት አሁናዊ በምስል!!
28/08/2026

ነሀሴ 22/2018 ዓ.ም
===========በእኖር ኤነር መገር ወረዳ በኤነር ገዳም ቀበሌ በአርሶ አደሮች ማሳ እየለማ የሚገኘው የበርበሬ ምርት አሁናዊ በምስል!!

ነሀሴ 22/2018 ዓ.ምበእኖር ኤነር መገር ወረዳ የመንግስትና የፓርቲ ወቅታዊ ተግባራት እስካሁን ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነው።ወቅታዊ ነባራዊ ሁኔታዎችን በመፈተሽና በመገም...
28/08/2026

ነሀሴ 22/2018 ዓ.ም
በእኖር ኤነር መገር ወረዳ የመንግስትና የፓርቲ ወቅታዊ ተግባራት እስካሁን ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነው።

ወቅታዊ ነባራዊ ሁኔታዎችን በመፈተሽና በመገምገም ትኩረት የሚሹ ወቅታዊና መደበኛ ተግባራቶችን ማከናወንና ማስኬድ እንደሚገባ ተገልጿል።

በሁሉም የመስክ የተፈጸሙ ተግባራትን በመገምገም በትምህርት በጤና ፣በግብርና የሴቶች ልማት ህብረት፣የክረምት በጎፍቃድ ተግባራት እና ሌሎች የልማት ስራዎች አመራሩ በተሰጠው ተልዕኮ መሠረት ወደ ቀበሌ ተሰማርቶ የፈጻማቸውን ትግባራት በዝርዝር እየተገመገመ ይገኛል።

በወረዳው በመንግስትና ፓርቲ የተከናወኑ ተግባራቶችና ሂደቶችን በመገምገምና በመፈተሽ በቀጣይ ልዩ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ጭምር ተወያይቶ አቅጣጫ ይቀመጣል።

በመድረኩም ወቅታዊና መደበኛ ተግባራቶች የተመሩበት አግባብ፣ የፖለቲካ ነባራዊ ሁኔታዎችና ወቅታዊ የትኩረት መስኮች የተከናወኑበት አገባብ እና ሂደቶችን በመገመገም ለተሻለ ውጤት ለማስቀመጥ ነው ተብሏል።

በመድረኩም የእኖር ኤነር መገር ወረዳ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ማአሩፍ አብድል ሽኩር፣ የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መላኩ ሳህሌ፣ ጨምሮ የወረዳው ረዳት የመንግስት ተጠሪና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘረፍ ሀላፊ አቶ ለገሰ ፋንቱ እና የወረዳው የረዳት የመንግስትና የአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ ሰሚራ መንሱር እንዲሁም የወረዳው ጠቅላላ አመራሮች ተገኝተዋል።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በጉራጌ ዞን የእኖር ኤነር መገር ወረዳ መንግስት ኮምንኬሽን ጉ/ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to በጉራጌ ዞን የእኖር ኤነር መገር ወረዳ መንግስት ኮምንኬሽን ጉ/ጽ/ቤት:

Shortcuts

Share